مزمور 30 – NAV & NASV

Ketab El Hayat

مزمور 30:1-12

الْمَزْمُورُ الثَّلاثُونَ

مَزْمُورٌ نَشِيدٌ بِمُنَاسَبَةِ تَدْشِينِ الْبَيْتِ. لِدَاوُدَ

1أُمَجِّدُكَ يَا رَبُّ لأَنَّكَ انْتَشَلْتَنِي وَلَمْ تَجْعَلْ أَعْدَائِي يَشْمَتُونَ بِي. 2يَا رَبُّ إِلَهِي اسْتَغَثْتُ بِكَ فَشَفَيْتَنِي 3يَا رَبُّ، أَنْتَ انْتَشَلْتَ نَفْسِي مِنْ شَفَا الْهَاوِيَةِ. وَأَنْقَذْتَنِي مِنْ بَيْنِ الْمُنْحَدِرِينَ إِلَى عَالَمِ الأَمْوَاتِ. 4يَا أَتْقِيَاءَ الرَّبِّ رَنِّمُوا لَهُ، وَارْفَعُوا الشُّكْرَ لاسْمِهِ الْمُقَدَّسِ، 5فَإِنَّ غَضَبَهُ يَدُومُ لِلَحْظَةٍ، أَمَّا رِضَاهُ فَمَدَى الْحَيَاةِ. يَبْقَى الْبُكَاءُ لِلَيْلَةٍ، أَمَّا فِي الصَّبَاحِ فَيَعُمُّ الابْتِهَاجُ.

6وَأَنَا قُلْتُ فِي أَثْنَاءِ طُمَأْنِينَتِي: لَا أَتَزَعْزَعُ أَبَداً. 7أَنْتَ يَا رَبُّ قَدْ وَطَّدْتَ بِرِضَاكَ قُوَّتِي كَالْجَبَلِ الرَّاسِخِ، لَكِنْ حِينَ حَجَبْتَ وَجْهَكَ عَنِّي ارْتَعَبْتُ. 8يَا رَبُّ إِلَيْكَ صَرَخْتُ، وَإِلَيْكَ يَا سَيِّدِي تَضَرَّعْتُ. 9مَاذَا يُجْدِيكَ مَوْتِي وَنُزُولِي إِلَى الْقَبْرِ؟ أَيَسْتَطِيعُ تُرَابِي أَنْ يَحْمَدَكَ أَوْ يُحَدِّثَ بِأَمَانَتِكَ؟ 10اسْمَعْنِي يَا رَبُّ، وَارْحَمْنِي. كُنْ مُعِيناً لِي. 11حَوَّلْتَ نَوْحِي إِلَى رَقْصٍ. خَلَعْتَ عَنِّي مِسْحَ الْحِدَادِ وَكَسَوْتَنِي رِدَاءَ الْفَرَحِ. 12لِتَتَرَنَّمْ لَكَ نَفْسِي وَلَا تَسْكُتْ، يَا رَبُّ إِلَهِي إِلَى الأَبَدِ أَحْمَدُكَ.

New Amharic Standard Version

መዝሙር 30:1-12

መዝሙር 30

ከክፉ አደጋ የዳነ ሰው ምስጋና

ለቤተ መቅደሱ ምረቃ የተዘመረ፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ ከታች አንሥተኸኛልና፣

ጠላቶቼም በላዬ እንዳይደሰቱ አድርገሃልና፣

ከፍ ከፍ አደርግሃለሁ።

2እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ፤ ትረዳኝ ዘንድ ወደ አንተ ጮኽሁ፤

አንተም ፈወስኸኝ።

3እግዚአብሔር ሆይ ነፍሴን ከሲኦል30፥3 ወይም ከመቃብር አወጣሃት፤

ወደ ጕድጓድ ከመውረድም መልሰህ ሕያው አደረግኸኝ።

4እናንተ ቅዱሳኑ፤ ለእግዚአብሔር ዘምሩ፤

ቅዱስ ስሙንም አወድሱ።

5ቍጣው ለዐጭር ጊዜ ነው፤

ቸርነቱ ግን እስከ ዕድሜ ልክ ነውና፤

ሌሊቱን በልቅሶ ቢታደርም፣

በማለዳ ደስታ ይመጣል።

6እኔም በተረጋጋሁ ጊዜ፣

“ከቶ አልናወጥም” አልሁ።

7እግዚአብሔር ሆይ፤ በአንተ ሞገስ፣

ተራሮቼ30፥7 ወይም ኰረብታማ የሆነች አገሬ ጸኑ፣

ፊትህን በሰወርህ ጊዜ ግን፣

ውስጤ ታወከ።

8እግዚአብሔር ሆይ፤ ወደ አንተ ተጣራሁ፤

ወደ ጌታም እንዲህ ብዬ ጮኽሁ፤

9“በእኔ ወደ ጕድጓድ መውረድ፣

በመሞቴ ምን ጥቅም ይገኛል?30፥9 ወይም ዝም ብል…ይገኛል?

ዐፈር ያመሰግንሃልን?

ታማኝነትህንስ ይናገራልን?

10እግዚአብሔር ሆይ፤ ስማ፤ ማረኝም፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ ረዳት ሁነኝ።”

11ዋይታዬን ወደ ሽብሸባ ለወጥህልኝ፤

ማቄን አውልቀህ ፍሥሓን አለበስኸኝ፤

12እንግዲህ ነፍሴ ታመስግንህ፤ ዝምም አትበል፤

እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ፤ ለዘላለም አመሰግንሃለሁ።