مزمور 28 – NAV & NASV

Ketab El Hayat

مزمور 28:1-9

الْمَزْمُورُ الثَّامِنُ وَالْعِشْرُونَ

لِدَاوُدَ

1يَا رَبُّ إِلَيْكَ أَصْرُخُ، فَلَا تَتَصَامَمْ عَنِّي يَا صَخْرَتِي، لِئَلّا أَكُونَ، إِذَا سَكَتَّ عَنِّي، مِثْلَ الْمُنْحَدِرِينَ إِلَى الْهَاوِيَةِ. 2اسْتَمِعْ صَوْتَ تَضَرُّعِي عِنْدَمَا أَسْتَغِيثُ بِكَ، رَافِعاً يَدَيَّ نَحْوَ مِحْرَابِ قَدَاسَتِكَ. 3لَا تَطْرَحْنِي مَعَ الأَشْرَارِ وَفَاعِلِي الإِثْمِ، الَّذِينَ يُظْهِرُونَ الْوُدَّ لأَصْحَابِهِمْ، وَهُمْ يَكُنُّونَ لَهُمُ الشَّرَّ فِي قُلُوبِهِمْ. 4جَازِهِمْ وَفْقاً لِفِعْلِهِمْ وَشَرِّ أَعْمَالِهِمْ. أَعْطِهِمْ مَا يَسْتَحِقُّ صَنِيعُ أَيْدِيهِمْ، وَرُدَّ عَلَيْهِمْ جَزَاءَهُمْ. 5وَلأَنَّهُمْ لَا يُبَالُونَ بِأَفْعَالِ الرَّبِّ وَلَا بِصَنِيعِ يَدَيْهِ، فَإِنَّهُ يُدَمِّرُهُمْ وَلَا يُعِيدُ بِنَاءَهُمْ.

6مُبَارَكٌ الرَّبُّ فَقَدْ سَمِعَ صَوْتَ تَضَرُّعِي. 7الرَّبُّ قُوَّتِي وَتُرْسِي. عَلَيْهِ اتَّكَلَ قَلْبِي، فَنِلْتُ الْغَوْثَ. لِذَلِكَ يَبْتَهِجُ قَلْبِي وَأَحْمَدُهُ بِنَشِيدِي. 8الرَّبُّ قُوَّةُ شَعْبِهِ، وَهُوَ حِصْنُ خَلاصِ مَسِيحِهِ. 9خَلِّصْ يَا رَبُّ شَعْبَكَ وَبَارِكْ مِيرَاثَكَ. كُنْ رَاعِياً لَهُمْ وَاحْمِلْهُمْ إِلَى الأَبَدِ.

New Amharic Standard Version

መዝሙር 28:1-9

መዝሙር 28

ልመናና ምስጋና

የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ ወደ አንተ እጣራለሁ፤

ዐለቴ ሆይ፤ ሰምተህ እንዳልሰማ አትሁንብኝ፤

አንተ ዝም ካልኸኝ፤

ወደ ጕድጓድ እንደሚወርዱ እሆናለሁ።

2ለርዳታ በጮኽሁ ጊዜ፣

ወደ ቅዱስ ማደሪያህ፣

እጆቼን በዘረጋሁ ጊዜ፣

የልመናዬን ቃል ስማ።

3በልባቸው ተንኰል እያለ፣

ከባልንጀሮቻቸው ጋር በሰላም ከሚናገሩ፣

ከክፉ አድራጊዎችና

ከዐመፃ ሰዎች ጋር ጐትተህ አትውሰደኝ።

4እንደ ሥራቸው፣

እንደ ክፉ ተግባራቸው ክፈላቸው፤

እንደ እጃቸው ሥራ ስጣቸው፤

አጸፋውን መልስላቸው።

5ለእግዚአብሔር ሥራ ግድ ስለሌላቸው፣

ለእጆቹም ተግባራት ስፍራ ስላልሰጡ፣

እርሱ ያፈርሳቸዋል፤

መልሶም አይገነባቸውም።

6የልመናዬን ቃል ሰምቷልና፣

እግዚአብሔር የተባረከ ይሁን።

7እግዚአብሔር ብርታቴና ጋሻዬ ነው፤

ልቤ በእርሱ ይታመናል፤ እርሱም ዐግዞኛል፤

ልቤ ሐሤት አደረገ፤

በዝማሬም አመሰግነዋለሁ።

8እግዚአብሔር ለሕዝቡ ብርታታቸው ነው፤

ለቀባውም የመዳን ዐምባ ነው።

9ሕዝብህን አድን፤ ርስትህንም ባርክ፤

እረኛ ሁናቸው፤ ለዘላለሙም ዐቅፈህ ያዛቸው።