مزمور 19 – NAV & NASV

Ketab El Hayat

مزمور 19:1-14

الْمَزْمُورُ التَّاسِعُ عَشَرَ

لِقَائِدِ الْمُنْشِدِينَ. مَزْمُورٌ لِدَاوُدَ

1السَّمَاوَاتُ تُحَدِّثُ بِمَجْدِ اللهِ، وَالْفَلَكُ يُخْبِرُ بِعَمَلِ يَدَيْهِ 2بِذَلِكَ تَتَحَادَثُ الأَيَّامُ أَبْلَغَ حَدِيثٍ، وَتَتَخَاطَبُ بِهِ اللَّيَالِي. 3لَا يَصْدُرُ عَنْهَا كَلامٌ، لَكِنَّ صَوْتَهَا يُسمَعُ وَاضِحاً. 4انْطَلَقَ صَوْتُهُمْ إِلَى الأَرْضِ كُلِّهَا وَكَلامُهُمْ إِلَى أَقَاصِي الْعَالَمِ. جَعَلَ لِلشَّمْسِ مَسْكَناً فِيهَا، 5وَهِيَ مِثْلُ الْعَرِيسِ الْخَارِجِ مِنْ مُخْدَعِهِ، كَالْعَدَّاءِ الْمُبْتَهِجِ لِلسِّبَاقِ فِي الطَّرِيقِ. 6تَنْطَلِقُ مِنْ أَقْصَى السَّمَاوَاتِ، وَتَدُورُ إِلَى أَقَاصِيهَا، وَلَا شَيْءَ يَحْتَجِبُ مِنْ حَرِّهَا.

7شَرِيعَةُ الرَّبِّ كَامِلَةٌ تُنْعِشُ النَّفْسَ. شَهَادَةُ الرَّبِّ صَادِقَةٌ تَجْعَلُ الْجَاهِلَ حَكِيماً. 8وَصَايَا الرَّبِّ مُسْتَقِيمَةٌ تُفَرِّحُ الْقَلْبَ. أَمْرُ الرَّبِّ نَقِيٌّ يُنِيرُ الْعَيْنَيْنِ. 9مَخَافَةُ الرَّبِّ طَاهِرَةٌ ثَابِتَةٌ إِلَى الأَبَدِ، وَأَحْكَامُ الرَّبِّ حَقٌّ وَعَادِلَةٌ كُلُّهَا. 10إِنَّهَا أَشْهَى مِنَ الذَّهَبِ النَّقِيِّ، وَهِيَ أَحْلَى مِنَ الْعَسَلِ بَلِ الْقَطْرِ السَّائِلِ مِنْ أَقْرَاصِ الشَّهْدِ. 11عَبْدُكَ يَهْتَدِي بِها، وَفِي صَوْنِهَا ثَوَابٌ عَظِيمٌ. 12مَنْ يَتَنَبَّهُ إِلَى سَهَوَاتِهِ؟ مِنَ الْخَطَايَا الْخَفِيَّةِ خَلِّصْنِي، 13وَمِنَ الْكَبَائِرِ أَيْضاً احْفَظْ عَبْدَكَ، وَلَا تَدَعْهَا تَتَسَلَّطُ عَلَيَّ. عِنْدَئِذٍ أَكُونُ كَامِلاً وَأَتَبَرَّأُ مِنْ ذَنْبٍ عَظِيمٍ. 14لِتَكُنْ أَقْوَالُ فَمِي وَخَوَاطِرُ قَلْبِي مَقْبُولَةً لَدَيْكَ يَا رَبُّ، يَا صَخْرَتِي وَفَادِيَّ.

New Amharic Standard Version

መዝሙር 19:1-14

መዝሙር 19

እግዚአብሔር የጽድቅ ፀሓይ

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።

1ሰማያት የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ፤

የሰማይም ጠፈር የእጁን ሥራ ያውጃሉ።

2ቀን ለሌላው ቀን ይናገራል፤

ሌሊትም ለሌሊት ዕውቀትን ይገልጣል፤

3ንግግር የለም፤ ቃል የለም፤

ድምፃቸው በጆሮ የሚሰማ አይደለም።19፥3 ወይም የሚናገሩት የላቸውም፤ ቃላት የለም፤ ከእርሱ ምንም ድምፅ አይሰማም

4ያም ሆኖ ድምፃቸው ወደ ምድር ሁሉ፣

ቃላቸውም19፥4 ሰብዓ ሊቃናት የሩምና ሱርስት እንዲሁ ሲሆኑ፣ ዕብራይስጡ ግን ድንበራቸው ይላል። እስከ ዓለም ዳርቻ ይወጣል።

እርሱ በሰማያት ለፀሓይ ድንኳን ተክሏል፤

5ፀሓይም ከእልፍኙ እንደሚወጣ ሙሽራ ይወጣል፤

ወደ ግቡም እንደሚሮጥ ብርቱ ሰው ደስ ይለዋል።

6መውጫው ከሰማያት ዳርቻ ነው፤

ዑደቱም እስከ ሌላኛው ዳርቻ ነው፤

ከትኵሳቱም የሚሰወር የለም።

7የእግዚአብሔር ሕግ ፍጹም ነው፤

ነፍስንም መልሶ ያለመልማል፤

የእግዚአብሔር ሥርዐት የታመነ ነው፤

አላዋቂውን ጥበበኛ ያደርጋል።

8የእግዚአብሔር ሕግጋት ትክክል ናቸው፤

ልብን ደስ ያሰኛሉ።

የእግዚአብሔር ትእዛዝ ብሩህ ነው፤

ዐይንን ያበራል።

9እግዚአብሔርን መፍራት ንጹሕ ነው፤

ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል።

የእግዚአብሔር ፍርድ የታመነ፣

ሁለንተናውም ጻድቅ ነው፤

10ከወርቅ ይልቅ የከበረ፣

እጅግ ከጠራ ወርቅም የተሻለ ነው፤

ከማር ይልቅ ይጣፍጣል፤

ከማር ወለላም ይበልጥ ይጥማል።

11ደግሞም አገልጋይህ በእርሱ ጥንቃቄ ያደርጋል፤

እርሱንም መጠበቅ ወሮታ አለው።

12ስሕተቱን ማን ሊያስተውል ይችላል?

ከተሰወረ በደል አንጻኝ።

13ባሪያህን ከድፍረት ኀጢአት ጠብቅ፤

እንዳይሠለጥንብኝም ርዳኝ፤

ያን ጊዜ ያለ እንከን እሆናለሁ፤

ከታላቅ በደልም እነጻለሁ።

14መጠጊያዬና አዳኜ እግዚአብሔር ሆይ፤

የአፌ ቃልና የልቤ ሐሳብ፣

በፊትህ ያማረ ይሁን።