مزمور 126 – NAV & NASV

Ketab El Hayat

مزمور 126:1-6

الْمَزْمُورُ الْمِئَةُ وَالسَّادِسُ وَالْعِشْرُونَ

تَرْنِيمَةُ الْمَصَاعِدِ

1عِنْدَمَا أَرْجَعَ الرَّبُّ أَهْلَ أُورُشَلِيمَ مِنَ السَّبْيِ، صِرْنَا كَمَنْ يَرَى حُلْماً. 2عِنْدَئِذٍ امْتَلأَتْ أَفْوَاهُنَا ضِحْكاً، وَأَلْسِنَتُنَا تَرَنُّماً. عِنْدَئِذٍ قَالَتِ الأُمَمُ: إِنَّ الرَّبَّ قَدْ أَجْرَى أُمُوراً عَظِيمَةً مَعَ هَؤُلاءِ. 3نَعَمْ، إِنَّ الرَّبَّ قَدْ صَنَعَ أُمُوراً عَظِيمَةً لَنَا، فَفَرِحْنَا. 4أَرْجِعْنَا يَا رَبُّ مِنْ سَبْيِنَا، كَمَا تَرْجِعُ السُّيُولُ إِلَى النَّقَبِ. 5فَمَنْ يَزْرَعْ بِالدُّمُوعِ يَحْصُدْ غَلّاتِهِ بِالابْتِهَاجِ. 6وَمَنْ يَذْهَبْ بَاكِياً حَامِلاً بِذَارَهُ يَرْجِعْ مُتَرَنِّماً حَامِلاً حُزَمَ حَصِيدِهِ.

New Amharic Standard Version

መዝሙር 126:1-6

መዝሙር 126

የስደት ተመላሾች መዝሙር

መዝሙረ መዓርግ።

1እግዚአብሔር የጽዮንን ምርኮ126፥1 ወይም እግዚአብሔር ሀብቷን ይመልሳል። በመለሰ ጊዜ፣

ሕልም እንጂ እውን አልመሰለንም።126፥1 ወይም የሰዎቿ ጤንነት ይታደሳል።

2በዚያን ጊዜ አፋችን በሣቅ፣

አንደበታችንም በእልልታ ተሞላ፤

በዚያን ጊዜም በሕዝቦች መካከል፣

እግዚአብሔር ታላቅ ነገር አደረገላቸው” ተባለ።

3እግዚአብሔር ታላቅ ነገር አደረገልን፤

እኛም ደስ አለን።

4እግዚአብሔር ሆይ፤ በኔጌቭ እንዳሉ ጅረቶች፣

ምርኳችንን መልስ።126፥4 ወይም ሀብታችንን መልስ

5በእንባ የሚዘሩ፣

በእልልታ ያጭዳሉ።

6ዘር ቋጥረው፣

እያለቀሱ የተሰማሩ፣

ነዷቸውን ተሸክመው፣

እልል እያሉ ይመለሳሉ።