مزمور 125 – NAV & NASV

Ketab El Hayat

مزمور 125:1-5

الْمَزْمُورُ الْمِئَةُ وَالْخَامِسُ وَالْعِشْرُونَ

تَرْنِيمَةُ الْمَصَاعِدِ

1الْوَاثِقُونَ بِالرَّبِّ هُمْ مِثْلُ جَبَلِ صِهْيَوْنَ الرَّاسِخِ الَّذِي لَا يَتَزَعْزَعُ إِلَى الأَبَدِ. 2كَمَا تُحِيطُ الْجِبَالُ بِأُورُشَلِيمَ، كَذَلِكَ يُحِيطُ الرَّبُّ بِشَعْبِهِ مِنَ الآنَ وَإِلَى الأَبَدِ، 3فَلَا يَتَسَلَّطُ الأَشْرَارُ عَلَى نَصِيبِ الأَبْرَارِ لِئَلّا يَمُدَّ الأَبْرَارُ أَيْدِيَهُمْ إِلَى الإِثْمِ. 4أَحْسِنْ يَا رَبُّ إِلَى الأَخْيَارِ وَإِلَى ذَوِي الْقُلُوبِ الْمُسْتَقِيمَةِ. 5أَمَّا الَّذِينَ يَحِيدُونَ إِلَى طُرُقٍ مُلْتَوِيَةٍ، فَإِنَّ الرَّبَّ يَسُوقُهُمْ إِلَى الْهَلاكِ مَعَ فَاعِلِي الإِثْمِ. لِيَكُنِ السَّلامُ لِشَعْبِ إِسْرَائِيلَ.

New Amharic Standard Version

መዝሙር 125:1-5

መዝሙር 125

እግዚአብሔር የሚታመኑበትን ይጠብቃል

መዝሙረ መዓርግ።

1በእግዚአብሔር የሚታመኑ፣

ሳትናወጥ ለዘላለም እንደምትኖር እንደ ጽዮን ተራራ ናቸው።

2ተራሮች ኢየሩሳሌምን እንደ ከበቧት፣

ከአሁን ጀምሮ ለዘላለም፣ እግዚአብሔር በሕዝቡ ዙሪያ ነው።

3ጻድቃን እጃቸውን ለክፋት እንዳያነሡ፣

የክፉዎች በትረ መንግሥት፣

ለጻድቃን በተመደበች ምድር ላይ አያርፍም።

4እግዚአብሔር ሆይ፤ መልካም ለሆኑ፣

ልባቸውም ለቀና መልካም አድርግ።

5ወደ ጠማማ መንገዳቸው የሚመለሱትን ግን፣

እግዚአብሔር ከክፉ አድራጊዎች ጋር ያስወግዳቸዋል።

በእስራኤል ላይ ሰላም ይውረድ።