مزمور 101 – NAV & NASV

Ketab El Hayat

مزمور 101:1-8

الْمَزْمُورُ الْمِئَةُ وَالْوَاحِدُ

مَزْمُورٌ لِدَاوُدَ

1سَأُشِيدُ بِرَحْمَتِكَ وَعَدْلِكَ يَا رَبُّ، وَلَكَ أُرَنِّمُ. 2أَسْلُكُ بِتَعَقُّلٍ فِي طَرِيقِ الْكَمَالِ. مَتَى تَأْتِي يَا رَبُّ لِمَعُونَتِي؟ أَسْلُكُ فِي وَسَطِ بَيْتِي بِاسْتِقَامَةِ قَلْبِي. 3لَنْ أَضَعَ نُصْبَ عَيْنَيَّ أَمْراً بَاطِلاً، فَإِنِّي أُبْغِضُ عَمَلَ الضَّالِّينَ لِئَلّا يَلْتَصِقَ بِي. 4لِيُفَارِقْنِي الْقَلْبُ الْمُنْحَرِفُ فَلَا أَرْتَكِبَ شَرّاً. 5أُبِيدُ كُلَّ مَنْ يَغْتَابُ قَرِيبَهُ سِرّاً؛ وَذُو الْعَيْنِ الْمُتَشَامِخَةِ وَالْقَلْبِ الْمُتَكَبِّرِ لَا أَحْتَمِلُهُ. 6تَرْعَى عَيْنَايَ الأُمَنَاءَ فِي الأَرْضِ لِيَسْكُنُوا مَعِي. وَخُدَّامِي هُمُ السَّالِكُونَ فِي طَرِيقِ الكَمَالِ. 7لَا يُقِيمُ دَاخِلَ بَيْتِي الْغَشَّاشُونَ، وَالْكَذَبَةُ لَا يَمْثُلُونَ أَمَامِي. 8أَقْضِي فِي كُلِّ صَبَاحٍ عَلَى جَمِيعِ الأَشْرَارِ فِي أَرْضِنَا، حَتَّى أَسْتَأْصِلَ مِنْ مَدِينَةِ الرَّبِّ كُلَّ فَاعِلِي الإِثْمِ.

New Amharic Standard Version

መዝሙር 101:1-8

መዝሙር 101

ትክክለኛ አስተዳደር

የዳዊት መዝሙር።

1ስለ ምሕረትና ስለ ፍትሕ እዘምራለሁ፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ ለአንተ በምስጋና እቀኛለሁ።

2እንከን የማይገኝባትን መንገድ አጥብቄ እይዛለሁ፤

አንተ ወደ እኔ የምትመጣው መቼ ነው?

በቤቴ ውስጥ፣

በንጹሕ ልብ እመላለሳለሁ።

3በዐይኔ ፊት፣

ክፉ ነገር አላኖርም።

የከሓዲዎችን ሥራ እጠላለሁ፤

ከእኔም ጋር አይጣበቅም።

4ጠማማ ልብ ከእኔ ይርቃል፤

ለክፋትም ዕውቅና አልሰጥም።

5ባልንጀራውን በስውር የሚያማውን፣

አጠፋዋለሁ፤

ትዕቢተኛ ዐይንና ኵራተኛ ልብ ያለውን፣

እርሱን አልታገሠውም።

6ከእኔ ጋር ይኖሩ ዘንድ፣

ዐይኖቼ በምድሪቱ ታማኞች ላይ ናቸው፤

በንጽሕና መንገድ የሚሄድ፣

እርሱ ያገለግለኛል።

7አታላይ የሆነ ማንም ሰው፣

በቤቴ ውስጥ አይኖርም፤

ሐሰትን የሚናገር፣

በፊቴ ቀና ብሎ አይቆምም።

8በምድሪቱ ላይ ያሉትን ክፉዎች ሁሉ፣

በየማለዳው አጠፋቸዋለሁ፤

ክፉ አድራጊዎችንም ሁሉ፣

ከእግዚአብሔር ከተማ እደመስሳቸዋለሁ።