2 ጴጥሮስ 3 – NASV & HHH

New Amharic Standard Version

2 ጴጥሮስ 3:1-18

የጌታ ቀን

1ወዳጆች ሆይ፤ ይህ አሁን የምጽፍላችሁ ሁለተኛው መልእክት ነው። ሁለቱንም መልእክቶች የጻፍሁላችሁ ቅን ልቦናችሁን እንድታነቃቁ ለማሳሰብ ነው፤ 2ደግሞም ቀድሞ በቅዱሳን ነቢያት የተነገረውን ቃል፣ እንዲሁም በሐዋርያት አማካይነት በጌታችንና በአዳኛችን የተሰጠውን ትእዛዝ እንድታስቡ ነው።

3ከሁሉ አስቀድሞ ይህን ዕወቁ፤ በመጨረሻው ዘመን የራሳቸውን ክፉ ምኞት የሚከተሉ ዘባቾች እየዘበቱ ይመጣሉ። 4እነርሱም፣ “ ‘እመጣለሁ’ ያለው ታዲያ የት አለ? አባቶች ከሞቱበት ከፍጥረት መጀመሪያ አንሥቶ እስካሁን ድረስ ሁሉም ነገር እንዳለ ይኖራል” ይላሉ። 5ነገር ግን እነዚህ ሰዎች ሰማያት ከጥንት ጀምሮ በእግዚአብሔር ቃል ተፈጥረው እንደሚኖሩ፣ መሬትም በውሃ መካከልና በውሃም እንደ ተሠራች ሆን ብለው ይክዳሉ፤ 6በዚያን ጊዜ የነበረው ዓለም በውሃ ተጥለቅልቆ ጠፋ። 7በዚያው ቃል ደግሞ አሁን ያሉት ሰማያትና ምድር፣ ኀጢአተኞች እስከሚጠፉበት እስከ ፍርድ ቀን ድረስ ለእሳት ተጠብቀዋል።

8ወዳጆች ሆይ፤ በጌታ ዘንድ አንድ ቀን እንደ ሺሕ ዓመት፣ ሺሕ ዓመትም እንደ አንድ ቀን መሆኑን ይህን አንድ ነገር አትርሱ። 9አንዳንድ ሰዎች የዘገየ እንደሚመስላቸው ጌታ የተስፋ ቃሉን ለመፈጸም አይዘገይም፤ ነገር ግን ማንም እንዳይጠፋ ፈልጎ፣ ሁሉ ለንስሓ እንዲበቃ ስለ እናንተ ይታገሣል።

10የጌታ ቀን ግን እንደ ሌባ ይመጣል፤ በዚያች ቀን ሰማያት በታላቅ ድምፅ ያልፋሉ፤ የሰማይም ፍጥረት በእሳት ይጠፋል፤ ምድርና በእርሷም ላይ ያለ ነገር ሁሉ ይቃጠላል።3፥10 በአንዳንድ ቅጆች ምድር ወና ትሆናለች ይላል።

11እንግዲህ ሁሉም ነገር በዚህ ሁኔታ የሚጠፋ ከሆነ፣ እናንተ እንዴት ዐይነት ሰዎች ልትሆኑ ይገባችኋል? አዎን፣ በቅድስናና በእውነተኛ መንፈሳዊነት ልትኖሩ ይገባችኋል፤ 12ደግሞም የእግዚአብሔርን ቀን እየተጠባበቃችሁ መምጫውን3፥12 ወይም የእግዚአብሔርን ቀን መምጣት በናፍቆት ስትጠብቁ ልታፋጥኑ ይገባል። በዚያን ቀን ሰማያት በእሳት ተቃጥለው ይጠፋሉ፤ የሰማይም ፍጥረት በታላቅ ትኵሳት ይቀልጣል። 13እኛ ግን ጽድቅ የሚኖርበትን አዲስ ሰማይና አዲስ ምድር በተስፋ ቃሉ መሠረት እንጠባበቃለን።

14ስለዚህ ወዳጆች ሆይ፤ እነዚህን ሁሉ ነገሮች የምትጠባበቁ ስለ ሆናችሁ፣ ያለ ነውርና ያለ ነቀፋ ከእርሱ ጋር በሰላም እንድትገኙ ትጉ። 15የጌታችን ትዕግሥት እናንተ እንድትድኑ እንደ ሆነ አስቡ፤ እንዲሁም ወንድማችን ጳውሎስ እንደ ተሰጠው ጥበብ መጠን ጻፈላችሁ። 16እርሱ ስለ እነዚህ ነገሮች በመልእክቶቹ ሁሉ ጽፏል፤ በመልእክቶቹም ውስጥ በቀላሉ ለመረዳት የሚያዳግቱ ነገሮች አሉ። ዕውቀት የጐደላቸውና ጽናት የሌላቸው ሰዎች ሌሎችን ቅዱሳት መጻሕፍት እንደሚያጣምሙ፣ እነዚህንም ደግሞ ለገዛ ጥፋታቸው ያጣምማሉ።

17እንግዲህ ወዳጆች ሆይ፤ ይህን አስቀድማችሁ ስላወቃችሁ፣ ጸንታችሁ ከቆማችሁበት መሠረት በዐመፀኞች ስሕተት ተስባችሁ እንዳትወድቁ ተጠንቀቁ። 18ነገር ግን በጌታችንና በአዳኛችን በኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ዕውቀት እደጉ።

ለእርሱ አሁንም፣ ለዘላለምም ክብር ይሁን! አሜን።

Habrit Hakhadasha/Haderekh

אגרתו השנייה של פטרוס השליח 3:1‏-18

1‏-2אחים יקרים, זהו מכתבי השני שאני כותב לכם, ובשניהם השתדלתי לעורר אתכם ולהזכירכם עובדות שכבר למדתם מדברי הנביאים, ומהשליחים שסיפרו לכם את דברי אדוננו ומושיענו.

3תחילה ברצוני להזכירכם כי בימים האחרונים יבואו לצים ורשעים, אשר ילעגו לאמת ויעשו כל מעשה רע העולה על דעתם.

4רשעים אלה יאמרו לכם: ”אם המשיח הבטיח לחזור, היכן הוא? מדוע טרם חזר?“ הם ימשיכו ויאמרו: ”המשיח לא ישוב לעולם! הרי מבריאת העולם ועד עתה לא השתנה דבר – הכול נשאר כשהיה!“

5בכוונה תחילה הם יתעלמו מהעובדה שבראשית ברא אלוהים את השמים ואת הארץ ממים, במוצא־פיו בלבד, 6ובאמצעות המים – באמצעות המבול – השמיד את דור הרשעים. 7ובמוצא־פיו ציווה ה׳ לשמור את השמים והארץ, שקיימים עתה, לאש הגדולה ביום־הדין – כשכל הרשעים יאבדו.

8ידידים יקרים, עלינו לזכור כי לגבי אלוהים יום אחד יכול להימשך אלף שנים, ואלף שנים יום אחד בלבד. 9אלוהים אינו מאחר לשוב אלינו, כפי שרבים חושבים; הוא ממתין בסבלנות לחוטאים רבים שיחזרו בתשובה, כי אינו רוצה שיאבדו. 10יום ה׳ יבוא בזמן בלתי־צפוי, בדומה לגנב בלילה. אז יחלפו השמים ברעש גדול, יסודות העולם יימסו באש, הארץ וכל אשר בה ישרפו.

11הואיל והכול סביבנו יישרף וימס, חישבו מה קדושים צריכים להיות חייכם!

12צפו לביאת יום האלוהים והשתדלו להחישו. ביום זה הוא יבעיר את השמים ואת יסודות הארץ עד שיימסו. 13אולם אנחנו מצפים לקיום הבטחת אלוהים: לשמים חדשים וארץ חדשה שבהם ישכון צדק בלבד.

14ידידים יקרים, בהמתינכם להתרחשותם של דברים אלה ולבואו של המשיח, השתדלו לחיות בלי לחטוא; חיו בשלום עם כולם, כדי שבבוא המשיח הוא ימצא אתכם ללא דופי.

15וזכרו, סבלנותו של האדון נותנת זמן לאנשים להיוושע. פולוס, אחינו החכם והאהוב, דיבר על כך ברבים ממכתביו. 16כמה מדבריו של פולוס אינם קלים להבנה, וחסרי־הדעת והפתאים מסלפים ומעוותים את משמעותם – כפי שעיוותו וסילפו את יתר דברי הכתובים – ובכך יביאו לחורבנם.

17אחים יקרים, אני מזהיר אתכם מראש: אל תלכו אחרי תורת השקר של אותם אנשי־בלייעל, פן תערערו את שיווי משקלכם הנפשי. 18אדרבא, חזקו את אמונתכם והתעמקו בתורת אדוננו ומושיענו ישוע המשיח, שלו הכבוד והתהילה מעתה ולעולמי עולמים. – אמן.