2 ጴጥሮስ 2 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

2 ጴጥሮስ 2:1-22

ሐሰተኛ መምህራንና መጨረሻቸው

1ነገር ግን ሐሰተኞች ነቢያት በሕዝቡ መካከል እንደ ነበሩ፣ እንዲሁም በእናንተ መካከል ሐሰተኞች መምህራን ይነሣሉ፤ እነርሱም የዋጃቸውን ጌታ እንኳ ክደው፣ ጥፋት የሚያስከትል የስሕተት ትምህርት በስውር ያስገባሉ፤ በዚህም በራሳቸው ላይ ድንገተኛ ጥፋት ያመጣሉ። 2ብዙዎች አስነዋሪ ድርጊቶቻቸውን ይከተላሉ፤ በእነርሱም ምክንያት የእውነት መንገድ ይሰደባል። 3እነዚህ ሐሰተኞች መምህራን እየተስገበገቡ በፈጠራ ታሪካቸው ይበዘብዟችኋል። ፍርዳቸው ከጥንት ጀምሮ ዝግጁ ነው፤ መጥፊያቸውም አያንቀላፋም።

4እግዚአብሔር ኀጢአት የሠሩትን መላእክት ሳይራራላቸው ወደ ገሃነም2፥4 በግሪኩ ታርታሩስ ይለዋል። ከጣላቸውና በጨለማ ጕድጓድ ውስጥ ለፍርድ ካስቀመጣቸው፣ 5የጽድቅ ሰባኪ የነበረውንም ኖኅን ከሌሎች ሰባት ሰዎች ጋር አድኖ፣ ለቀድሞው ዓለም ሳይራራ በኀጢአተኞች ላይ የጥፋት ውሃ ካመጣ፣ 6ደግሞም ኀጢአት ለሚያደርጉ ሁሉ ምሳሌ እንዲሆኑ፣ የሰዶምንና የገሞራን ከተሞች ዐመድ እስኪሆኑ ድረስ አቃጥሎ ከፈረደባቸው፣ 7ጻድቅ የሆነውንና በዐመፀኞች ሴሰኛ ድርጊት እየተሣቀቀ የኖረውን ሎጥን ካዳነ፣ 8ያ ጻድቅ ሰው በእነርሱ መካከል ሲኖር በሚያየውና በሚሰማው ነገር ነፍሱ ዕለት ዕለት በዐመፀኛ ድርጊታቸው ብትጨነቅም፣ 9ጌታ፣ በእውነት እያመለኩት የሚኖሩትን ከፈተና እንዴት እንደሚያድናቸውና ዐመፀኞችን እየቀጣ ለፍርድ2፥9 ወይም ዐመፀኞችን ለቅጣት እስከ ፍርድ ቀን ድረስ ቀን እንዴት ጠብቆ እንደሚያቈያቸው ያውቃል። 10በተለይም በርኩስ ምኞት የሥጋ ፍላጎታቸውን2፥10 ወይም የኀጢአተኛ ባሕርያቸውን የሚከተሉትንና ሥልጣንን የሚንቁትን ለፍርድ ጠብቆ ያቈያቸዋል።

እነዚህ ሰዎች ደፋሮችና እብሪተኞች ስለሆኑ ሰማያውያንን ፍጡራን ሲሳደቡ አይፈሩም፤ 11ነገር ግን መላእክት ከእነርሱ ይልቅ ብርቱና ኀያል ሆነው ሳሉ፣ በጌታ ፊት በእነርሱ ላይ የስድብ ቃል አይሰነዝሩም። 12እነዚህ ሰዎች ግን ምንም በማያውቁት ነገር እየገቡ ይሳደባሉ፤ እነርሱም ለመያዝና ለመገደል እንደ ተወለዱ፣ በስሜታቸው ብቻ እንደሚመሩና ልቦናም እንደሌላቸው አራዊት ናቸው፤ የሚጠፉትም እንደ እንስሳት ነው።

13ለዐመፃቸው የሚገባውን የዐመፅ ዋጋ ይቀበላሉ። በጠራራ ፀሓይ ሲፈነጥዙ እንደ ደስታ ይቈጥሩታል፤ በግብዣ ላይ ሳሉ ነውረኞችና ርኩሶች ሆነው ከእናንተም ጋር በፍቅር ግብዣ ላይ2፥13 በአንዳንድ ቅጆች በፍቅር ግብዣቸው ላይ የሚል የለም። ይቀመጣሉ። 14ዐይናቸው ቅንዝር የተሞላ በመሆኑ ኀጢአትን ከመሥራት አይቈጠቡም፤ ጽኑ ያልሆኑትን ነፍሳት ያስታሉ፤ ሥሥትን የለመደ ልብ አላቸው፤ የተረገሙ ናቸው! 15ቀናውን መንገድ ትተው፣ የዐመፅን ደመወዝ የወደደውን የቢዖርን ልጅ የበለዓምን መንገድ ተከትለው ስተዋል፤ 16እርሱ ግን ስለ መተላለፉ ተገሥጿል፤ መናገር የማይችል አህያ በሰው ቋንቋ ተናግሮ የነቢዩን እብደት ገታ።

17እነዚህ ሰዎች የደረቁ ምንጮችና በዐውሎ ነፋስ የሚነዱ ደመናዎች ናቸው፤ የሚጠብቃቸውም ድቅድቅ ጨለማ ነው፤ 18ከንቱ ቃል እየደረደሩ በስሕተት ከሚኖሩት መካከል አምልጠው የመጡትን ሰዎች በሴሰኛ ሥጋዊ ምኞት በማባበል ያታልላሉና። 19እነርሱ ራሳቸው የጥፋት ባሪያዎች ሆነው ሳሉ፣ ሌሎችን ነጻ ትወጣላችሁ እያሉ ተስፋ ይሰጧቸዋል፤ ሰው ለተገዛለት ለዚያ ነገር ባሪያ ነውና። 20ጌታችንንና አዳኛችንን ኢየሱስ ክርስቶስን በማወቅ ከዓለም ርኩሰት ካመለጡ በኋላ እንደ ገና ተጠላልፈው ቢሸነፉ፣ ከመጀመሪያው ይልቅ የኋለኛው ሁኔታቸው የከፋ ይሆንባቸዋል። 21የጽድቅን መንገድ ካወቁ በኋላ ከተሰጣቸው ቅዱስ ትእዛዝ ወደ ኋላ ከሚመለሱ፣ ቀድሞውኑ የጽድቅን መንገድ ባላወቋት ይሻላቸው ነበር። 22“ውሻ ወደ ትፋቱ ይመለሳል” እንዲሁም “ዐሣማ ቢታጠብም ተመልሶ በጭቃ ላይ ይንከባለላል” የሚለው ምሳሌ እውን ይሆንባቸዋል።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

彼得后书 2:1-22

假教师

1以往曾经有假先知在百姓中出现,将来在你们中间也同样会有假教师出现。他们暗地里引进使人沉沦的异端邪说,甚至否认那位买赎他们的主。这些人正迅速地自招灭亡。 2许多人会效法他们邪恶无耻的行为,致使真理之道被人毁谤。 3他们贪婪成性,想用花言巧语在你们身上谋利。这种人的刑罚自古已经判定,他们很快就会灭亡。

4即使天使犯了罪,上帝也没有容忍他们,而是把他们丢在地狱里,囚在幽暗的深坑等候审判。 5上帝也没有容忍远古的世代,曾用洪水淹灭了世上不敬虔的恶人,只留下传讲上帝公义的挪亚和他的七位家人。 6上帝也审判了所多玛蛾摩拉,将二城毁灭,烧为灰烬,作为以后不敬虔之人的警戒。 7祂只拯救了因恶人的淫乱放荡而忧伤的义人罗得8因为义人罗得住在他们当中,天天耳闻目睹他们一切无法无天的丑行,他正直的心很痛苦。 9上帝知道怎样拯救敬虔的人脱离试炼,把不义的人拘禁在刑罚之下,等候审判的日子, 10尤其是那些放纵污秽的情欲、轻视权柄的人。他们胆大妄为,肆无忌惮地毁谤有尊荣的。 11即使力量和权能更大的天使都不敢在主面前用毁谤的话控告有尊荣的。 12但他们好像没有理性,生下来就是预备让人捉去宰杀的牲畜,连自己不懂的事也随口毁谤。他们在毁坏别人的时候,自己也必灭亡。 13他们多行不义,必自食恶果。他们喜爱在大白天寻欢作乐,是你们中间的败类和渣滓,一面和你们同席,一面以欺骗为乐。 14他们眼中充满淫欲,不停地犯罪,引诱那些信心不坚定的人。他们贪婪成性,实在是该受咒诅! 15他们离弃正道,走入歧途,重蹈比珥之子巴兰先知的覆辙。巴兰贪爱不义之财, 16因自己的罪而受了责备。不能说话的驴竟然像人一样说起话来,制止了他狂妄的行为。

17他们如同枯干的水井和被狂风吹散的雾气,有幽幽黑暗留给他们。 18他们口出狂言,空话连篇,以肉体的邪情私欲为饵,诱惑那些刚刚摆脱了荒谬生活的人。 19他们应许那些人可以得自由,而自己却做罪恶的奴隶,因为人被什么制服,就被什么奴役。

20如果他们借着认识我们的主和救主耶稣基督,已经摆脱了世俗的污秽,但后来又被这些事缠住、俘虏了,他们的处境会比以前更糟糕。 21他们明知道正路,却背弃了传给他们的神圣诫命,这样倒不如不知道的好。 22俗语说得好:“狗转过身来,吃自己所吐的;猪洗干净了,又回到污泥里去打滚。”这些话正好用在他们身上。