2 ዜና መዋዕል 8 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

2 ዜና መዋዕል 8:1-18

ሰሎሞን ያከናወናቸው ሌሎች ሥራዎች

8፥1-18 ተጓ ምብ – 1ነገ 9፥10-28

1ሰሎሞን የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስና የራሱን ቤተ መንግሥት የሠራባቸው ሃያ ዓመት ከተፈጸመ በኋላ፣ 2ኪራም የሰጠውን ከተሞች አድሶ እስራኤላውያን እንዲሰፍሩባቸው አደረገ። 3ከዚያም ሰሎሞን ወደ ሐማት ሱባ ዘመተ፤ ያዛትም። 4በምድረ በዳውም ውስጥ ተድሞርንና ቀድሞ በሐማት ሠርቷቸው የነበሩትን የዕቃ ቤት ከተሞች ሁሉ ሠራ። 5እንዲሁም የላይኛውን ቤት ሖሮንና የታችኛውን ቤትሖሮን የተመሸጉ ከተሞች አድርጎ ከቅጥሮቻቸው፣ ከበሮቻቸውና ከመዝጊያዎቻቸው ጋር ሠራ። 6ደግሞም ባዕላትንና የዕቃ ቤት ከተሞቹን ሁሉ፣ ሠረገሎችና8፥6 ወይም ሠረገለኞች ተብሎ መተርጐም ይችላል። ፈረሶች የሚኖሩባቸውን ከተሞች ሁሉ፣ በአጠቃላይ በኢየሩሳሌም፣ በሊባኖስና በግዛቱ ሁሉ ለመሥራት የፈለጋቸውን ነገሮች ሁሉ ሠራ።

7እስራኤላውያን ያልሆኑ ግን ከኬጢያውያን፣ ከአሞራውያን፣ ከፌርዜያውያን፣ ከኤዊያውያንና ከኢያቡሳውያን የቀሩት ሕዝቦች ሁሉ፣ 8እስራኤላውያን ያላጠፏቸውን፣ በምድሪቱ የቀሩ ዘሮቻቸውን የጕልበት ሥራ ይሠሩ ዘንድ ሰሎሞን መለመላቸው፤ እስከ ዛሬም ይሠራሉ።8፥8 ወይም ከሌቦ ሐማት ተብሎ መተርጐም ይችላል። 9ይሁን እንጂ ሰሎሞን ማንም እስራኤላዊ ባሪያ ሆኖ በግዳጅ ሥራውን እንዲሠራ አላደረገም፤ እነርሱ ተዋጊዎች፣ የሻምበል አዛዦች፣ የሠረገሎችና የሠረገላ ነጂዎች አዛዦች ነበሩና። 10ከእነዚህም ሁለት መቶ አምሳዎቹ የንጉሥ ሰሎሞን ሹማምት ሰዎቹን የሚቈጣጠሩ ነበሩ።

11ሰሎሞንም፣ “የእግዚአብሔር ታቦት የገባበት ቦታ ሁሉ ቅዱስ ስለሆነ፣ ሚስቴ በእስራኤል ንጉሥ በዳዊት ቤተ መንግሥት መኖር አይገባትም” በማለት የፈርዖንን ልጅ ከዳዊት ከተማ እርሱ ወደ ሠራላት ቤተ መንግሥት አመጣት።

12ሰሎሞንም በቤተ መቅደሱ መመላለሻ ፊት ለፊት ባሠራው የእግዚአብሔር መሠዊያ ላይ የሚቃጠል መሥዋዕት ለእግዚአብሔር አቀረበ። 13ሙሴ ስለ መሥዋዕት አቀራረብ ባዘዘው መሠረት በእያንዳንዱ የበዓል ቀን ይኸውም በየሰንበቱ፣ በየወሩ መባቻና በሦስቱ የዓመት በዓላት ማለትም በቂጣ በዓል፣ በመከር በዓልና በዳስ በዓል ጊዜ የሚቃጠለውን መሥዋዕት ለእግዚአብሔር አቀረበ። 14የአባቱን የዳዊትን ሥርዐት በመከተልም፣ ካህናቱን በየአገልግሎት ክፍላቸው ሌዋውያኑንም ምስጋናውን እንዲመሩና በየዕለቱ ሥራቸው ካህናቱን እንዲረዱ መደባቸው። ደግሞም የእግዚአብሔር ሰው ዳዊት ባዘዘው መሠረት፣ የቤተ መቅደሱን በር ጠባቂዎች በልዩ ልዩ በሮች ጥበቃ ላይ በየክፍላቸው መደባቸው። 15እነርሱም ንጉሡ ግምጃ ቤቱን ጨምሮ ስለ ማናቸውም ነገር ለካህናቱና ለሌዋውያኑ የሰጠውን ትእዛዝ አልተላለፉም ነበር።

16የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ መሠረት ከተጣለበት ዕለት አንሥቶ እስከ ፍጻሜው ድረስ ያለው የሰሎሞን ሥራ ሁሉ ተከናወነለት፤ በዚሁ ሁኔታም የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ሥራ ከፍጻሜ ደረሰ።

17ከዚያም ሰሎሞን የኤዶም የባሕር ጠረፍ ወደ ሆኑት ወደ ዔጽዮንጋብርና ወደ ኤሎት ሄደ። 18ኪራምም ባሕሩን በሚያውቁት በራሱ መኰንኖች የሚታዘዙ መርከቦችን ላከለት፤ እነዚህም ከሰሎሞን ሰዎች ጋር በመሆን ወደ ኦፊር ተጓዙ፤ ከዚያም አራት መቶ አምሳ መክሊት8፥18 ዐሥራ ስድስት ሜትሪክ ቶን ያህል ነው። ወርቅ አምጥተው ለንጉሥ ሰሎሞን ሰጡት።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

歷代志下 8:1-18

所羅門的功績

1所羅門用二十年的時間興建了耶和華的殿和他自己的王宮。 2他重修希蘭送給他的城邑,讓以色列人居住。

3所羅門去攻打哈馬瑣巴,並攻取了此城。 4他興建曠野裡的達莫以及哈馬境內所有的儲貨城, 5把上伯·和崙與下伯·和崙建成有牆、有門、有閂的堅城, 6還建造巴拉、所有的儲貨城、屯車城、養馬城和他想在耶路撒冷黎巴嫩及其統治的全境興建的城邑。 7當時國中有人、亞摩利人、比利洗人、希未人和耶布斯人的後裔, 8以色列人沒有滅絕他們。所羅門讓他們服勞役,至今如此。 9所羅門王沒有讓以色列人服勞役,而是讓他們做戰士、將領、戰車長和騎兵長。 10他還任命二百五十名監工負責監管工人。

11所羅門帶法老的女兒離開大衛城,來到為她建造的宮中,因為所羅門說:「我的妻子不可住在以色列大衛的宮裡,因為約櫃所到之處都是聖潔的。」

12所羅門在門廊前他所築的耶和華的壇上向耶和華獻燔祭, 13並照摩西的規定,在安息日、朔日和每年特定的三個節期,即除酵節、七七節和住棚節獻上當獻的祭。

14所羅門照著他父親大衛的吩咐,指派祭司分班供職,讓利未人負責頌讚、輔助祭司盡每天的職責,還指派殿門守衛分班守門。這些都是上帝的僕人大衛規定的。 15他們沒有違背大衛王就庫房等工作對祭司和利未人的吩咐。

16從耶和華的殿奠基直到完工,所羅門所有的計劃都已順利完成。這樣,耶和華的殿落成了。

17之後,所羅門前往以東地區靠海的以旬·迦別以祿18希蘭派懂得航海的僕人乘船隻與所羅門的僕人一同到俄斐,從那裡為所羅門王運回十五噸黃金。