2 ዜና መዋዕል 6 – NASV & BPH

New Amharic Standard Version

2 ዜና መዋዕል 6:1-42

1ከዚያም ሰሎሞን እንዲህ አለ፤ “እግዚአብሔር ጥቅጥቅ ባለ ደመና ውስጥ እንደሚኖር ተናግሯል፤ 2እኔም አንተ ለዘላለም ትኖርበት ዘንድ፣ ይህን ታላቅና ድንቅ ቤተ መቅደስ ሠራሁልህ።”

3መላው የእስራኤል ጉባኤ እዚያው ቆመው ሳሉ፣ ንጉሡ ዘወር ብሎ ባረካቸው። 4እንዲህም አለ፤

“ለአባቴ ለዳዊት በቃሉ የሰጠውን ተስፋ በእጁ የፈጸመ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ይመስገን፤ እንዲህ ብሏልና፤ 5‘ሕዝቤን ከግብፅ ካወጣሁበት ጊዜ ጀምሮ፣ ስሜ የሚጠራበት ቤተ መቅደስ ይሠራበት ዘንድ ከማናቸውም የእስራኤል ነገድ ከተሞች አንድም አልመረጥሁም፤ ወይም የሕዝቤ የእስራኤል መሪ ይሆን ዘንድ ማንንም አልመረጥሁም። 6አሁን ግን ስሜ በዚያ እንዲሆን ኢየሩሳሌምን፣ ሕዝቤን እስራኤልን እንዲገዛም ዳዊትን መርጫለሁ።’

7“አባቴ ዳዊት፣ ለእስራኤል አምላክ ለእግዚአብሔር ስም ቤተ መቅደስ ለመሥራት በልቡ አስቦ ነበር፤ 8እግዚአብሔር ግን፣ ለአባቴ ለዳዊት እንዲህ አለው፤ ‘ለስሜ ቤተ መቅደስ ለመሥራት በልብህ አስበህ ነበር፤ ይህን በልብህ በማሰብህ መልካም አድርገሃል፤ 9ይሁን እንጂ ቤተ መቅደሱን የምትሠራው አንተ አይደለህም፤ ለስሜ ቤተ መቅደስ የሚሠራልኝ ከአብራክህ የሚከፈለው፣ የገዛ ልጅህ ነው።’

10እግዚአብሔርም የተናገረውን ቃል ፈጽሟል፤ እኔም እግዚአብሔር በሰጠው ተስፋ መሠረት በአባቴ በዳዊት እግር ተተክቼ፣ በእስራኤል ዙፋን ላይ ተቀምጫለሁ፤ ለእስራኤል አምላክ ለእግዚአብሔርም ስም ቤተ መቅደስ ሠርቻለሁ። 11በዚያም እግዚአብሔር ከእስራኤል ሕዝብ ጋር ያደረገው ኪዳን ያለበትን ታቦት አኑሬአለሁ።”

ሰሎሞን በምረቃው ጊዜ ያቀረበው ጸሎት

6፥12-40 ተጓ ምብ – 1ነገ 8፥22-53

6፥41-42 ተጓ ምብ – መዝ 132፥8-10

12ከዚህ በኋላ ሰሎሞን መላው የእስራኤል ጉባኤ ባሉበት በእግዚአብሔር መሠዊያ ፊት እጆቹን ዘርግቶ ቆመ። 13ሰሎሞንም ርዝመቱ አምስት ክንድ፣6፥13 2.3 ሜትር ይህል ነው። ወርዱ አምስት ክንድ፣ ከፍታውም ሦስት ክንድ6፥13 1.3 ሜትር ይህል ነው። የሆነ የናስ መድረክ በውጭው አደባባይ መካከል አሠርቶ ነበር፤ በመድረኩም ላይ ወጥቶ በመቆም በመላው የእስራኤል ጉባኤ ፊት ተንበርክኮ እጆቹን ወደ ሰማይ ዘረጋ፤ 14እንዲህም አለ፤

“የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፤ በፍጹም ልባቸው በመንገድህ ከሚሄዱት ባሪያዎችህ ጋር የፍቅር ኪዳንህን የምትጠብቅ፣ በሰማይም ሆነ በምድር እንደ አንተ ያለ አምላክ የለም፤ 15ለባሪያህ ለአባቴ ለዳዊት የሰጠኸውን ተስፋ አጽንተሃል፤ በአፍህ የተናገርኸውን ዛሬም እንደ ሆነው በእጅህ ፈጸምኸው።

16“አሁንም የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፤ ለባሪያህ ለአባቴ ለዳዊት፣ ‘ልጆችህ አንተ እንደ አደረግኸው ሁሉ በሚያደርጉት ሁሉ ሕጌን በመጠበቅ በፊቴ ቢመላለሱ፣ በእራኤል ዙፋን ላይ በፊቴ የሚቀመጥ ሰው ከቶ አታጣም’ ብለህ የሰጠኸውን ተስፋ አጽናለት። 17እንግዲህ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፣ ለባሪያህ ለዳዊት የሰጠኸው የተስፋ ቃል ይፈጸም።

18“በውኑ እግዚአብሔር ከሰው ጋር በምድር ላይ ይኖራልን? እነሆ፤ ሰማያትና ሰማየ ሰማያት እንኳ አንተን ሊይዙህ አይችሉም፤ ታዲያ እኔ የሠራሁት ይህ ቤተ መቅደስማ ምንኛ ያንስ! 19ይሁን እንጂ እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ፤ የባሪያህን ጸሎትና ስለ ምሕረት ያቀረበውን ልመና አድምጥ፤ ባሪያህ በፊትህ የሚያቀርበውን ጩኸትና ጸሎት ስማ። 20ስምህ እንደሚጠራበት ወደ ተናገርኸው ወደዚህ ቤተ መቅደስ ዐይኖችህ በቀንም በሌሊትም የተገለጡ ይሁኑ፤ ባሪያህ ወደዚህ ስፍራ የሚጸልየውንም ጸሎት ስማ። 21ባሪያህና ሕዝብህ እስራኤል ወደዚህ ስፍራ በሚጸልዩበትም ጊዜ ልመናቸውን ስማ፤ ከማደሪያህ ከሰማይ ስማ፤ ሰምተህም ይቅር በል።

22“አንድ ሰው ባልንጀራውን ቢበድልና እንዲምል ቢጠየቅ፣ እርሱም መጥቶ በቤተ መቅደሱ በመሠዊያህ ፊት ቢምል፣ 23ከሰማይ ሆነህ ስማ፤ አድርግም። በደለኛውን፣ በደሉን በራሱ ላይ አድርገህ እንደ ሥራው በመክፈል በባሪያዎችህ መካከል ፍረድ። ንጹሑም በደለኛ አለመሆኑን አስታውቅ፤ እንደ ንጽሕናውም ክፈለው።

24“ሕዝብህ እስራኤል አንተን ከመበደላቸው የተነሣ በጠላቶቻቸው ፊት ድል ቢሆኑ፣ ወደ አንተ ተመልሰውም በዚህ ቤተ መቅደስ ውስጥ በፊትህ በመጸለይና ልመናቸውን በማቅረብ ስምህን ቢጠሩ፣ 25በሰማይ ሆነህ ስማ፤ የሕዝብህን የእስራኤልን ኀጢአት ይቅር በል፤ ለእነርሱና ለአባቶቻቸው ወደ ሰጠሃቸውም ምድር መልሳቸው።

26“ሕዝብህ አንተን ከመበደላቸው የተነሣ፣ ሰማያት ተዘግተው ዝናብ ባይዘንብ፣ አንተ ስለ አስጨነቅሃቸው ወደዚህ ስፍራ ቢጸልዩ፣ ስምህን ቢጠሩና ከኀጢአታቸው ቢመለሱ፣ 27በሰማይ ሆነህ ስማ፤ የባሪያዎችህን የሕዝብህን የእስራኤልን ኀጢአት ይቅር በል፤ የሚኖሩበትን ቀናውን መንገድ አስተምራቸው፤ ለሕዝብህ ርስት አድርገህ በሰጠኸውም ምድር ላይ ዝናብን ላክ።

28“በምድሪቱ ላይ ራብ ወይም ቸነፈር ወይም ዋግ ወይም አረማሞ ወይም አንበጣ ወይም ኵብኵባ በሚወርድባት ጊዜ፣ ወይም ደግሞ በየትኛውም ከተማቸው ሳሉ ጠላት በሚከብባቸው ጊዜ፣ ወይም ማናቸውም አደጋ ወይም ደዌ በሚደርስባቸው ጊዜ፣ 29ከሕዝብህ ከእስራኤል ማንም ሰው ጭንቀቱና ሕመሙ ተሰምቶት፣ እጁን ወደዚህ ቤተ መቅደስ በመዘርጋት ጸሎትና ልመና ቢያቀርብ፣ 30በሰማይ በማደሪያህ ሆነህ ስማ፤ ይቅርም በል፤ የሰውን ልብ የምታውቅ አንተ ብቻ ስለ ሆንህ፣ ለእያንዳንዱ እንደ ሥራው መጠን ክፈለው፤ 31ይህም ለአባቶቻችን በሰጠሃቸው ምድር በሚኖሩበት ጊዜ ሁሉ አንተን እንዲፈሩህና በመንገዶችህ እንዲሄዱ ነው።

32“ከሕዝብህ ከእስራኤል ወገን ያልሆነ ባዕድ ሰው ስለ ታላቁ ስምህ፣ ስለ ኀያሉ እጅህና ስለ ተዘረጋው ክንድህ ሰምቶ ከሩቅ አገር በመምጣት ወደዚህ ቤተ መቅደስ በሚጸልይበት ጊዜ፣ 33በሰማይ በማደሪያህ ሆነህ ስማ፤ የምድር ሕዝቦች ሁሉ እንደ ገዛ ሕዝብህ እንደ እስራኤል፣ ስምህን በማወቅ እንዲፈሩህ፣ የሠራሁትም ይህ ቤት ስምህ የሚጠራበት ቤት መሆኑን እንዲያውቁ ባዕዱ ሰው የሚጠይቅህን ሁሉ አድርግ።

34“ሕዝብህ አንተ በምትልካቸው ቦታ ሁሉ ጠላቶቻቸውን ለመውጋት በሚወጡበት ጊዜ፣ አንተ ወደ መረጥሃት ወደዚህች ከተማ፣ እኔም ለስምህ ወደ ሠራሁት ወደዚህ ቤተ መቅደስ ወደ አንተ ቢጸልዩ፣ 35ጸሎታቸውንና ልመናቸውን በሰማይ ስማ፤ የጠየቁህንም አድርግላቸው።

36“መቼም የማይበድል ሰው የለምና፣ አንተን በበደሉህ ጊዜ፣ ተቈጥተሃቸው ሩቅ ወይም ቅርብ ወደ ሆነ አገር በምርኮ ለሚወስዳቸው ጠላት አሳልፈህ ብትሰጣቸው፣ 37በተማረኩበት አገር ሆነው የልብ ጸጸት ተሰምቷቸው ንስሓ ቢገቡና በምርኮ ሳሉ፣ ‘ኀጢአት ሠርተናል፤ በድለናል፤ ክፉ ድርጊትም ፈጽመናል’ ቢሉ፣ 38ተማርከው በሚኖሩበትም ምድር ሆነው በፍጹም ልባቸው፣ በፍጹምም ነፍሳቸው ቢመለሱና ለአባቶቻቸው ወደ ሰጠሃቸው ምድር፣ አንተም ወደ መረጥሃት ከተማና እኔም ለስምህ ወደ ሠራሁት ቤተ መቅደስ ቢጸልዩ፣ 39ጸሎታቸውንና ልመናቸውን በሰማይ በማደሪያህ ስማ፤ የጠየቍህንም አድርግላቸው። የበደሉህንም የሕዝብህን ኀጢአት ይቅር በል።

40“አሁንም አምላኬ ሆይ፤ በዚህ ስፍራ ወደ ቀረበው ጸሎት ዐይኖችህ የተገለጡ፣ ጆሮዎችህም የሚያደምጡ ይሁኑ።

41“አሁንም እግዚአብሔር አምላክ ሆይ ተነሥ፣

ከኀይልህ ታቦት ጋር ወደ ማረፊያ ቦታህ ግባ።

እግዚአብሔር አምላክ ሆይ፤ ካህናትህ ድነትን ይልበሱ፤

ቅዱሳንህም በቸርነትህ ደስ ይበላቸው።

42እግዚአብሔር አምላክ ሆይ፤ የቀባኸውን አትተወው፤

ለባሪያህ ለዳዊት ቃል የገባህለትን ጽኑ ፍቅር ዐስብ።”

Bibelen på hverdagsdansk

2. Krønikebog 6:1-42

1Da udbrød Salomon: 2„Herren har sagt, at han bor i den tætte sky. Herre, nu har jeg bygget dig en prægtig bolig på jorden, et sted, hvor du kan slå dig ned og bo for evigt.”

Salomons tale til folket

1.Kong. 8,14-21

3Derpå vendte kongen sig om og så ud over hele Israels forsamling, og han velsignede dem. Derefter sagde han: 4„Lovet være Herren, Israels Gud, som i dag har opfyldt det løfte, han gav min far, da han sagde: 5‚Fra dengang jeg førte mit folk ud af Egypten, har jeg ikke udvalgt nogen by i Israel, hvor man kunne bygge et hus til mig. Jeg har heller ikke udvalgt nogen til at være konge over mit folk. 6Men i dag udpeger jeg Jerusalem som det sted, hvor min bolig skal være, og jeg har udvalgt dig, David, til at lede mit folk.’ ”

7Salomon fortsatte: „Min far ville så gerne bygge et hus til Herren, Israels Gud, 8men han fik ikke lov til det. ‚Det er godt, at du ønsker at bygge mig et hus,’ sagde Herren til ham, 9‚men det bliver din søn, som kommer til at bygge det.’ 10Herren har nu opfyldt sit løfte, for jeg har efterfulgt min far på Israels trone, og nu står Herrens hus færdigt. 11Dér har jeg anbragt arken, som indeholder den pagt, Herren oprettede med Israels folk.”

Salomons bøn til Herren

1.Kong. 8,22-54

12Salomon stod foran brændofferalteret med hænderne løftet ud mod forsamlingen. 13Han havde fået konstrueret en platform af bronze midt i forgården. Den var 2,25 m lang, 2,25 m bred og 1,35 m høj. Salomon knælede nu ned på platformen med hænderne løftet mod himlen 14og bad følgende bøn: „Herre, Israels Gud, der findes ingen Gud som dig i hele verden! Du er en trofast Gud, der holder fast ved dine pagtsløfter, når blot dine tjenere adlyder dig af hele deres hjerte. 15Du har nu opfyldt løftet til min far, som var din tjener. 16Og nu, Herre, beder jeg dig opfylde resten af dit løfte til ham: At hvis hans efterkommere gør som ham og handler efter din vilje, skal der altid sidde en fra hans slægt på Israels trone. 17Ja Herre, Israels Gud, opfyld også det løfte!

18Er det muligt, at Gud kan tage bolig på jorden? Hvis Himlen er for lille til at rumme dig, Herre, hvordan kan du da bo i det hus, jeg har bygget? 19Min Herre og Gud, lyt til den inderlige bøn, jeg nu beder for dit ansigt: 20Våg over dette hus både dag og nat—det sted, hvor du har lovet at tage bolig—og når jeg vender mig mod din bolig for at bede, lyt da til min bøn og svar mig. 21Ja, hør hver eneste bøn, som dit folk beder til dig, vendt mod dette sted. Hør os i din bolig i Himlen og tilgiv os.

22Når nogen bliver anklaget for at have forbrudt sig mod en anden person, og de foran dit alter her sværger på, at de er uskyldige, 23så hør dem i Himlen. Frikend den uskyldige og døm den skyldige.

24Når dit folk synder og som straf bliver besejret af deres fjender, og de så vender om til dig og beder om din hjælp, vendt mod dette hus, 25så hør dit folks bøn fra din bolig i Himlen, tilgiv dem og lad dem få lov at vende tilbage til deres land, som du har givet dem og deres forfædre.

26Når dit folk synder, og regnen derfor udebliver, og de så vender om fra deres synd, fordi du har straffet dem, og de beder til dig om hjælp, vendt mod dette hus, 27så hør dem fra din bolig i Himlen og tilgiv dit folk, Israel. Lær dem at følge dine veje, og lad igen regnen falde på den jord, du gav dem.

28Når der kommer hungersnød i landet, pest eller plantesygdomme, angreb af græshopper eller andre skadedyr, eller når fjenderne omringer vores byer, ja hvilken som helst epidemi eller katastrofe det nu drejer sig om, 29og dit folk erkender deres synd, rækker hænderne ud mod dette sted og bønfalder dig om hjælp, 30så hør dem i din himmelske bolig og tilgiv dem. Du alene kender menneskets skjulte tanker, og du har ret til at straffe dem for deres handlinger. 31Da vil de lære at vise dig ærefrygt og vandre på dine veje i al den tid, de lever i dette land, som du lovede deres forfædre.

32Og når fremmede folk hører om din storhed og dine mægtige undere, og de kommer langvejsfra for at bede dig om hjælp, vendt mod dette hus, 33så hør dem i Himlen, hvor du bor, og svar på deres bøn. Da skal alle jordens folkeslag høre om dig og have ærefrygt for dig ligesom dit folk, Israel, og hele verden vil forstå, at det hus, som jeg her har bygget, er indviet til dig.

34Når du sender dit folk i krig mod deres fjender, og de beder til dig, vendt mod den by, du har udvalgt til bolig, og det hus, jeg har bygget til dig, 35hør da i din Himmel deres bøn og skaf dem deres ret.

36Hvis de synder imod dig—og hvem kan sige sig fri for den mulighed—og du i din vrede tillader fjenden at føre dem som fanger til et fremmed land, det være sig nært eller fjernt, 37og hvis de så kommer til fornuft i det land, hvor de er i fangenskab, og råber til dig: ‚Vi har handlet ondt og været ulydige mod Gud! Vi har syndet!’ 38-39da hør deres bøn i din bolig i Himlen og hjælp dem, når de ærligt vender sig til dig og beder om hjælp, vendt mod det land, du gav deres forfædre, mod den by, du har udvalgt, og det hus, jeg har bygget til din ære. Tilgiv dit folk deres ulydighed mod dig.

40Min Gud, våg over dette sted og lyt opmærksomt til alle de bønner, der bedes her.

41Herre, rejs dig, træd ind i din bolig,

for at være ved din almagts Ark.

Må dine præster blive klædt i frelsens dragt,

og dine hengivne tjenere fryde sig over din godhed!

42Forkast ikke din udvalgte konge!

Glem ikke din trofasthed mod din tjener David!”