2 ዜና መዋዕል 5 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

2 ዜና መዋዕል 5:1-14

1ሰሎሞን ለእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ የሠራው ሥራ ሁሉ ከተጠናቀቀ በኋላ፣ አባቱ ዳዊት የቀደሰውን ብሩንና ወርቁን፣ ዕቃዎቹንም ሁሉ አምጥቶ በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ግምጃ ቤት አኖራቸው።

ታቦቱ ወደ ቤተ መቅደስ ገባ

5፥2–6፥11 ተጓ ምብ – 1ነገ 8፥1-21

2ከዚያ በኋላ ሰሎሞን የእግዚአብሔርን የኪዳን ታቦት ከዳዊት ከተማ ከጽዮን እንዲያመጡ፣ የእስራኤልን ሽማግሌዎች፣ የየነገዱን መሪዎች ሁሉና የእስራኤላውያንን የቤተ ሰብ አለቆች በኢየሩሳሌም ሰበሰበ። 3የእስራኤልም ሰዎች ሁሉ የሰባተኛው ወር በዓል በሚከበርበት ጊዜ፣ በንጉሡ ፊት ተሰበሰቡ።

4የእስራኤል ሽማግሌዎች በተሰበሰቡም ጊዜ ሌዋውያኑ ታቦቱን አነሡት፤ 5ታቦቱን፣ የመገናኛ ድንኳኑንና በውስጡ ያሉትን የተቀደሱ ዕቃዎች ሁሉ ይዘው ወደ ላይ ወጡ፤ ሌዋውያን የሆኑ ካህናትም ተሸከሟቸው። 6ንጉሥ ሰሎሞንና በአጠገቡ የተሰበሰበው መላው የእስራኤል ጉባኤ ስፍር ቍጥር የሌላቸውን በጎችና በሬዎች በታቦቱ ፊት ሠዉ።

7ካህናቱም የእግዚአብሔርን የኪዳኑን ታቦት የቤተ መቅደሱ ውስጠኛ ክፍል ወደ ሆነው ወደ ቅድስተ ቅዱሳኑ አግብተው ከኪሩቤል ክንፍ በታች ባለው ስፍራው አኖሩት። 8ኪሩቤልም ክንፎቻቸውን ከታቦቱ በላይ ባለው ስፍራ ላይ ዘርግተው፣ ታቦቱንና መሎጊያዎቹን ሸፈኑ። 9መሎጊያዎቹም በጣም ረጃጅም ከመሆናቸው የተነሣ፣ ታቦቱ እስካለበት ድረስ ያሉት ጫፎቻቸው ከቅድስተ ቅዱሳኑ ፊት ለፊት ይታዩ ነበር፤ ከመቅደሱ ውጭ ግን አይታዩም ነበር፤ ዛሬም እዚያው ቦታ ይገኛሉ። 10እስራኤላውያን ከግብፅ ከወጡ በኋላ እግዚአብሔር ከእነርሱ ጋር ኪዳን ባደረገ ጊዜ፣ ሙሴ በኮሬብ ተራራ በውስጡ ካስቀመጣቸው ከሁለቱ ጽላቶች በቀር በታቦቱ ውስጥ ምንም አልነበረም። 11ካህናቱም ከቤተ መቅደሱ ወጡ፤ እዚያ የነበሩት ካህናት በምድባቸው መሠረት ባይሆንም፣ ሁሉም ራሳቸውን ቀድሰው ነበር። 12መዘምራን የነበሩት ሌዋውያን ሁሉ፣ አሳፍ፣ ኤማን፣ ሄማንና ኤዶታም፣ ወንዶች ልጆቻቸውና የሥጋ ዘመዶቻቸው ሁሉ ያማረ ቀጭን በፍታ ለብሰው፣ ከመሠዊያው በስተ ምሥራቅ በኩል ቆመው ጸናጽል ይጸነጽሉ፣ በገና ይደረድሩና መሰንቆ ይመቱ ነበር፤ እነርሱም መለከት በሚነፉ አንድ መቶ ሃያ ካህናት ታጅበው ነበር። 13መለከት ነፊዎችና ዘማሪዎችም በአንድነት አንድ ድምፅ ሆነው ለእግዚአብሔር ውዳሴና ምስጋና አቀረቡ፤ በመለከት፣ በጸናጽልና በሌሎች መሣሪያዎች ታጅበውም ድምፃቸውን ከፍ በማድረግ እግዚአብሔርን እያወደሱ፣

“እርሱ ቸር ነው፣

ፍቅሩም ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል።”

እያሉ ዘመሩ።

ከዚያም የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ በደመና ተሞላ። 14የእግዚአብሔር ክብር የአምላክን ቤተ መቅደስ ሞልቶት ስለ ነበር፣ ከደመናው የተነሣ ካህናቱ አገልግሎታቸውን ማከናወን አልቻሉም።

Thai New Contemporary Bible

2พงศาวดาร 5:1-14

1เมื่องานทั้งสิ้นที่โซโลมอนทรงทำเกี่ยวกับพระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้าเสร็จเรียบร้อยแล้ว โซโลมอนก็ทรงนำของถวายของกษัตริย์ดาวิดราชบิดา อันได้แก่ เงิน ทองคำ เครื่องใช้ไม้สอยทุกอย่างมาเก็บไว้ในคลังพระวิหารของพระเจ้า

อัญเชิญหีบพันธสัญญาเข้าสู่พระวิหาร

(1พกษ.8:1-21)

2จากนั้นโซโลมอนทรงเรียกบรรดาผู้อาวุโสของอิสราเอล หัวหน้าเผ่าต่างๆ และหัวหน้าครอบครัวทั้งหมดของชนอิสราเอลมาเข้าเฝ้าที่กรุงเยรูซาเล็ม เพื่ออัญเชิญหีบพันธสัญญาขององค์พระผู้เป็นเจ้ามาจากศิโยนเมืองดาวิด 3แล้วผู้ชายอิสราเอลทุกคนก็พากันมาเข้าเฝ้ากษัตริย์ในช่วงเทศกาลในเดือนที่เจ็ด

4เมื่อผู้อาวุโสทั้งปวงของอิสราเอลมาถึงแล้ว คนเลวีก็ยกหีบพันธสัญญาขึ้น 5บรรดาปุโรหิตซึ่งเป็นคนเลวีหามหีบมา พร้อมทั้งเต็นท์นัดพบ และภาชนะเครื่องใช้อันศักดิ์สิทธิ์ทั้งปวงในนั้น 6กษัตริย์โซโลมอนและชุมนุมประชากรอิสราเอลทั้งปวงที่มาชุมนุมกันหน้าหีบพันธสัญญาได้ถวายแกะและวัวเป็นเครื่องบูชาจำนวนมากจนนับไม่ถ้วน

7จากนั้นปุโรหิตอัญเชิญหีบพันธสัญญาขององค์พระผู้เป็นเจ้าเข้าสู่สถานนมัสการชั้นในของพระวิหารคืออภิสุทธิสถาน และตั้งไว้ใต้ปีกของเครูบ 8เครูบทั้งสองกางปีกเหนือที่ตั้งหีบพันธสัญญาและปกเหนือหีบกับคานหาม 9คานหามซึ่งยื่นออกมาจากหีบนี้ยาวมากจนมองเห็นปลายได้จากด้านหน้าของสถานนมัสการชั้นใน แต่มองไม่เห็นจากด้านนอกของวิสุทธิสถาน และคานนั้นก็ยังคงอยู่ที่นั่นจนถึงทุกวันนี้ 10ในหีบนั้นไม่มีสิ่งใดนอกจากศิลาสองแผ่นซึ่งโมเสสได้ใส่ไว้เมื่ออยู่ที่ภูเขาโฮเรบ ที่ซึ่งองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงกระทำพันธสัญญากับชนอิสราเอลหลังจากพวกเขาออกมาจากอียิปต์

11ปุโรหิตทั้งหลายจึงออกมาจากวิสุทธิสถาน ปุโรหิตทั้งหมดในที่นั้นได้ชำระตนให้บริสุทธิ์แล้ว ไม่ว่าจะประจำอยู่หมู่เหล่าใด 12คนเลวีทั้งปวงซึ่งเป็นนักดนตรีได้แก่ อาสาฟ เฮมาน เยดูธูนและบุตรกับญาติพี่น้องของพวกเขาแต่งกายด้วยผ้าลินินเนื้อดียืนอยู่ทางทิศตะวันออกของแท่นบูชา พวกเขาตีฉาบ บรรเลงพิณใหญ่และพิณเขาคู่ มีปุโรหิต 120 คนเป่าแตร 13นักแตรและนักร้องได้ประสานกันอย่างกลมกลืนเป็นเสียงเดียวกัน ถวายสรรเสริญและขอบพระคุณองค์พระผู้เป็นเจ้า พร้อมด้วยเสียงแตร ฉาบ และเครื่องดนตรีต่างๆ พวกเขาเปล่งเสียงสรรเสริญองค์พระผู้เป็นเจ้าและร้องเพลงว่า

“พระองค์ประเสริฐ

ความรักมั่นคงของพระองค์ดำรงนิรันดร์”

แล้วมีเมฆมาปกคลุมทั่วพระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้า 14บรรดาปุโรหิตไม่อาจปฏิบัติหน้าที่เพราะเมฆนั้น เนื่องจากพระเกียรติสิริขององค์พระผู้เป็นเจ้าปกคลุมอยู่ทั่วทั้งพระวิหารของพระเจ้า