2 ዜና መዋዕል 4 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

2 ዜና መዋዕል 4:1-22

የቤተ መቅደሱ ዕቃዎች መሟላት

4፥2-6፡10–5፥1 ተጓ ምብ – 1ነገ 7፥23-2638-51

1ርዝመቱ ሃያ ክንድ፣ ወርዱ ሃያ ክንድ፣ ቁመቱ ዐሥር ክንድ4፥1 ርዝመቱና ወርዱ 9 ሜትር ቍመቱ 4.5 ሜትር ያህል ነው። የሆነ የናስ መሠዊያ ሠራ። 2እንዲሁም የጐኑ ስፋት ከጠርዝ እስከ ጠርዝ ዐሥር ክንድ፣ ቁመቱ አምስት4፥2 2.3 ሜትር ያህል ነው። ክንድ የሆነ ክብ በርሜል ቀልጦ ከፈሰሰ ብረት ሠራ፤ ዙሪያውም ሲለካ ሠላሳ ክንድ4፥2 13.5 ሜትር ይህል ነው። ሆነ። 3ከበርሜሉ ከንፈር በታችም በእያንዳንዱ ክንድ ርቀት ላይ ዙሪያውን ዐሥር የኮርማ ቅርጾች4፥3 0.5 ሜትር ያህል ነው። ነበሩበት፤ ኮርማዎቹም ከበርሜሉ ጋር አንድ ወጥ ሆነው በሁለት ረድፍ ቀልጠው ተሠርተው ነበር።

4በርሜሉ በዐሥራ ሁለት ኮርማዎች ላይ የቆመ ሲሆን፣ ኮርማዎቹም ሦስቱ ወደ ሰሜን፣ ሦስቱ ወደ ምዕራብ፣ ሦስቱ ወደ ደቡብ፣ ሦስቱ ወደ ምሥራቅ ይመለከቱ ነበር። በርሜሉ በእነዚህ ላይ ያረፈ ሲሆን፣ የሁሉም ጀርባ ወደ መካከል የዞረ ነበር። 5የበርሜሉ ውፍረት አንድ ስንዝር፣4፥5 8 ሳንቲ ሜትር ያህል ነው። ከንፈሩ ደግሞ የጽዋ ከንፈር ወይም የሱፍ አበባ ይመስል ነበር፤ ይህም ሦስት ሺሕ የባዶስ መስፈሪያ4፥5 66 ኪሎ ሊትር ያህል ነው። የሚይዝ ነበር።

6እንዲሁም ዐሥር የመታጠቢያ ገንዳዎች አሠርቶ አምስቱን በደቡብ፣ አምስቱን ደግሞ በሰሜን በኩል አስቀመጠ፤ ገንዳዎቹ ለሚቃጠል መሥዋዕት የሚቀርቡት ነገሮች የሚታጠቡባቸው ሲሆኑ፣ በርሜሉ ግን ለካህናት መታጠቢያ የሚያገለግል ነበር።

7በተሰጠው የአሠራር መመሪያ መሠረት፣ ዐሥር የወርቅ መቅረዞች ሠርቶ ወደ ቤተ መቅደሱ በማስገባት፣ አምስቱን በስተ ደቡብ፣ አምስቱን በስተ ሰሜን አኖራቸው።

8ዐሥር ጠረጴዛ ሠርቶም ወደ ቤተ መቅደሱ በማስገባት አምስቱን በስተ ደቡብ፣ አምስቱን ደግሞ በስተ ሰሜን በኩል አኖራቸው፤ ደግሞም አንድ መቶ ጐድጓዳ የወርቅ ሳሕኖች ሠራ።

9የካህናቱንም አደባባይ ሠራ፤ እንዲሁም ታላቁን አደባባይና በሮቹን ከሠራ በኋላ በናስ ለበጣቸው። 10በርሜሉንም ከቤተ መቅደሱ በስተ ደቡብ ምሥራቅ ባለው ማእዘን በቀኝ በኩል አኖረው።

11እንዲሁም ምንቸቱን፣ መጫሪያዎችንና ጐድጓዳ ሳሕኖችን ሠራ። ኪራምም ለቤተ መቅደሱ አገልግሎት የሚውሉትን ዕቃዎች ለንጉሥ ሰሎሞን ሠርቶ ጨረሰ፤ እነዚህም፦

12ሁለቱ ዐምዶች፣

በአዕማዱ ጫፍ ላይ ያሉት ሁለት ባለ ሳሕን ቅርጽ ጕልላት በዐምዶቹ ላይ ያሉትን ሁለቱን፣

ባለ ሳሕን ቅርጽ ጕልላት የሚያስጌጡ ሁለት ዙር መርበቦች፤

13በዐምዶቹ ላይ ያሉትን ሁለቱን፣ ባለ ሳሕን ቅርጽ ጕልላት እንዲያስጌጡ ለእያንዳንዱ መርበብ ሁለት ዙር ሮማኖች ለሁለቱም ዙር መርበቦች በድምሩ አራት መቶ ሮማኖች፤

14መቆሚያዎች ከነመታጠቢያ ሳሕኖቻቸው፤

15በርሜሉና እርሱን የተሸከሙት ዐሥራ ሁለት ኮርማዎች፤

16ምንቸቶችና መጫሪያዎች፣ ሜንጦዎችና ከነዚሁም ጋር የተያያዙ ዕቃዎች።

ኪራምአቢ ለእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ መገልገያ እንዲሆን ለሰሎሞን የሠራቸው ዕቃዎች በሙሉ ከተወለወለ ናስ የተሠሩ ነበሩ። 17ንጉሡም እነዚህ ዕቃዎች በዮርዳኖስ ሸለቆ፣ በሱኮትና በጽሬዳ መካከል ባለው በሸክላ ዐፈር ቦታ ቀልጠው በሸክላ ቅርጽ ተሠርተው እንዲወጡ አደረገ። 18እነዚህ ሰሎሞን ያሠራቸው ነገሮች ሁሉ እጅግ ብዙዎች ስለሆኑ የናሱ ክብደት ምን ያህል እንደ ሆነ አልታወቀም ነበር።

19እንደዚሁም ሰሎሞን ለእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ መገልገያ የሚሆኑትን ዕቃዎች ሠራ፤ እነዚህም፦

የወርቅ መሠዊያ፣

የገጸ ኅብስቱ ጠረጴዛ፣

20በተሰጠው መመሪያ መሠረት፣ በቅድስተ ቅዱሳኑ ፊት ለፊት እንዲነድዱ፣ ከንጹሕ ወርቅ የተሠሩ መቅረዞች ከነቀንዲሎቻቸው፣

21የወርቅ አበባ ቅርጽ ሥራዎች፣ ቀንዲሎችና መኰስተሪያዎች ከንጹሕ ወርቅ የተሠሩ ነበሩ።

22ከንጹሕ ወርቅ የተሠሩ የመብራት ማጥፊያዎች፣ ለመርጨት የሚያገለግሉ ጐድጓዳ ሳሕኖች፣ ጭልፋዎችና ጥናዎች፣ እንደዚሁም የቤተ መቅደሱ የወርቅ መዝጊያዎች፣ ይኸውም የቅድስተ ቅዱሳኑ የውስጠኛው መዝጊያዎችና የቤተ መቅደሱ ዋናው አዳራሽ መዝጊያዎች ከንጹሕ ወርቅ የተሠሩ ነበሩ።

Persian Contemporary Bible

دوم تواريخ 4:1-22

اسباب خانهٔ خدا

(اول پادشاهان 7‏:23‏-51)

1سليمان پادشاه يک قربانگاه مفرغی ساخت به طول بيست ذراع، عرض بيست ذراع و بلندی ده ذراع. 2سپس يک حوض گرد از مفرغ درست كرد كه عمق آن پنج ذراع، قطرش ده ذراع و محيطش سی ذراع بود. 3بر كناره‌های لبهٔ حوض دو رديف نقشهايی به شکل گاو (در هر ذراع ده نقش) قرار داشتند. اين نقشها با خود حوض قالبگيری شده بود. 4اين حوض بر پشت دوازده مجسمهٔ گاو قرار داشت. سر گاوها به طرف بيرون بود: سه گاو رو به شمال، سه گاو رو به جنوب، سه گاو رو به مغرب و سه گاو رو به مشرق. 5ضخامت ديوارهٔ حوض به پهنای كف دست بود. لبهٔ آن به شكل جام بود و مانند گلبرگ سوسن به طرف بيرون باز می‌شد. گنجايش آن بيش از شصت هزار ليتر بود.

6ده حوضچه نيز ساخته شد پنج عدد در طرف شمال خانهٔ خدا و پنج عدد در طرف جنوب آن. از آب اين حوضچه‌ها برای شستن قطعه‌های بدن حيوان قربانی كه می‌بايست روی قربانگاه سوزانده شود استفاده می‌شد. كاهنان برای شستن خود از آب حوضچه‌ها استفاده نمی‌كردند، بلكه با آب حوض خود را می‌شستند.

7ده چراغدان طلا مطابق طرح، ساخته شد و در خانهٔ خدا قرار گرفت. چراغدانها را در دو دستهٔ پنج‌تايی روبروی هم، به طرف شمال و جنوب، نهادند. 8همچنين ده ميز ساختند و پنج عدد از آنها را در طرف شمال و پنج عدد ديگر را در سمت جنوب خانهٔ خدا قرار دادند. صد كاسهٔ طلا نيز درست كردند. 9سپس يک حياط داخلی برای كاهنان و يک حياط بيرونی ساخته شد و درهای بين آنها را با مفرغ پوشانيدند. 10حوض در گوشهٔ جنوب شرقی خانهٔ خدا بود. 11حورام سطلها، خاک‌اندازها و كاسه‌های مربوط به قربانیها را هم ساخت.

سرانجام حورام اين كارهای مربوط به خانهٔ خدا را كه سليمان پادشاه برای او تعيين كرده بود، به پايان رسانيد. اشيايی كه او ساخت عبارت بودند از:

12‏-16دو ستون،

دو سر ستون كاسه مانند برای ستونها،

دو رشته زنجير روی سر ستونها،

چهارصد انار مفرغی برای دو رشته زنجير (يعنی برای هر رشته زنجير سر ستون، دويست انار كه در دو رديف قرار داشتند)،

ميزها و حوضچه‌های روی آنها،

حوض بزرگ با دوازده گاو مفرغی زير آن،

سطلها، خاک‌اندازها و چنگکهای مخصوصِ آويزان كردن گوشت قربانیها.

حورام، اين صنعتگر ماهر، تمام اشیا خانهٔ خداوند را از مفرغ صيقلی برای سليمان پادشاه ساخت. 17به دستور سليمان اين اشیا در دشت اردن كه بين سوكوت و صرده قرار داشت قالبريزی شده بود. 18مقدار مفرغی كه استعمال شد، بی‌اندازه زياد بود و نمی‌شد آن را وزن كرد!

19در ضمن به دستور سليمان وسايلی از طلای خالص برای خانهٔ خدا ساخته شد. اين وسايل عبارت بودند از: قربانگاه، ميز نان مقدس، 20‏-21چرغدانها با نقشهای گل و چراغهای روی آنها كه مطابق طرح می‌بايست روبروی قدس‌الاقداس قرار می‌گرفت، انبرکها، 22انبرها، كاسه‌ها، قاشقها و آتشدانها. در ضمن درهای خانهٔ خدا يعنی درهای اصلی و درهای قدس‌الاقداس نيز از طلای خالص بود.