2 ዜና መዋዕል 29 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

2 ዜና መዋዕል 29:1-36

ሕዝቅያስ ቤተ መቅደሱን አነጻ

29፥1-2 ተጓ ምብ – 1ነገ 18፥2-3

1ሕዝቅያስ በነገሠ ጊዜ፣ ዕድሜው ሃያ አምስት ዓመት ነበር፤ በኢየሩሳሌም ተቀምጦም ሃያ ዘጠኝ ዓመት ገዛ። እናቱም አቡ የተባለች፤ የዘካርያስ ልጅ ነበረች። 2አባቱ ዳዊት እንዳደረገው ሁሉ፣ እርሱም በእግዚአብሔር ፊት ቅን ነገር አደረገ።

3በዘመነ መንግሥቱ በመጀመሪያው ዓመት፣ በመጀመሪያው ወር የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ በሮች ከፈተ፤ አደሳቸው። 4ካህናቱንና ሌዋውያኑን አስገብቶ በምሥራቅ በኩል ባለው አደባባይ ላይ በመሰብሰብ፣ 5እንዲህ አላቸው፤ “እናንት ሌዋውያን፤ ስሙኝ! ራሳችሁን አሁኑኑ ቀድሱ፤ የአባቶቻችሁን አምላክ የእግዚአብሔርንም ቤተ መቅደስ ቀድሱ። ርኩስ ነገርንም ሁሉ ከመቅደሱ አስወግዱ። 6አባቶቻችን ታማኞች አልነበሩም፣ በአምላካችን በእግዚአብሔር ፊት ክፉ ድርጊት ፈጸሙ፤ ተዉትም። ከእግዚአብሔር ማደሪያ ፊታቸውን መለሱ፤ ጀርባቸውንም አዞሩበት። 7የሰበሰቡንም በሮች ዘጉ፤ መብራቶቹንም አጠፉ። ለእስራኤል አምላክ ለእግዚአብሔር ዕጣን አላጠኑም፤ በመቅደሱም የሚቃጠል መሥዋዕት አላቀረቡም። 8ስለዚህ የእግዚአብሔር ቍጣ በይሁዳና በኢየሩሳሌም ላይ ወርዷል፤ እናንተ በገዛ ዐይናችሁ እንደምታዩት ለድንጋጤ፣ ለመደነቂያና ለመዘበቻ አሳልፎ ሰጣቸው። 9በዚህ ምክንያት አባቶቻችን በሰይፍ ወደቁ፣ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችን፣ ሚስቶቻችንም ተማረኩ። 10አሁንም አስፈሪ ቍጣው ከእኛ እንዲመለስ፣ ከእስራኤል አምላክ ከእግዚአብሔር ጋር ቃል ኪዳን ለመግባት አስቤአለሁ። 11ልጆቼ ሆይ፤ እንግዲህ ቸል አትበሉ፤ በፊቱ እንድትቆሙና እንድታገለግሉት፣ በፊቱም አገልጋዮቹ እንድትሆኑና ዕጣን እንድታጥኑለት እግዚአብሔር መርጧችኋልና።”

12ከዚያም እነዚሁ ሌዋውያን በሥራው ላይ ተሰማሩ፤

ከቀዓት ዘሮች የአማሢ ልጅ መሐትና የዓዛርያስ ልጅ ኢዮኤል፤

ከሜራሪ ዘሮች፣

የአብዲ ልጅ ቂስና የይሃሌልኤል ልጅ ዓዛርያስ፤

ከጌድሶን ዘሮች፣

የዛማት ልጅ ዮአክና የዮአክ ልጅ ዔድን፤

13ከኤሊጻፋን ዘሮች፣

ሺምሪና ይዒኤል፤

ከአሳፍ ዘሮች፣

ዘካርያስና መታንያ፤

14ከኤማን ዘሮች፣

ይሒኤልና ሰሜኢ፣

ከኤዶታም ዘሮች፣

ሸማያና ዑዝኤል።

15ወንድሞቻቸውን ከሰበሰቡና ራሳቸውን ከቀደሱ በኋላ፣ ንጉሡ የእግዚአብሔርን ቃል ተከትሎ ባዘዘው መሠረት የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ለማንጻት ገቡ። 16ካህናቱ የእግዚአብሔርን መቅደስ ለማንጻት ወደ ውስጡ ገቡ። በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ውስጥ ያገኙትንም ማናቸውንም የረከሰ ነገር ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ አደባባይ አወጡት። ሌዋውያኑም ተሸክመው በመውሰድ በቄድሮን ሸለቆ ውስጥ ጣሉት። 17ማንጻቱንም በመጀመሪያው ወር፣ በመጀመሪያው ቀን ጀምረው በዚያኑ ወር በስምንተኛው ቀን እስከ መቅደስ ሰበሰብ ደረሱ፤ በሚቀጥሉትም ስምንት ቀናት የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቀደሱ፤ የመቀደሱም ሥራ በመጀመሪያው ወር በዐሥራ ስድስተኛው ቀን ተጠናቀቀ።

18ከዚያም ወደ ንጉሡ ወደ ሕዝቅያስ ገብተው እንዲህ አሉ፤ “የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ በሙሉ፣ የሚቃጠል መሥዋዕት የሚቀርብበትን መሠዊያ ከነዕቃዎቹ ሁሉ፣ ገጸ ኅብስቱ የሚቀመጥበትን ጠረጴዛ፣ ከነዕቃዎቹ አንጽተናል። 19ንጉሥ አካዝ ነግሦ ሳለ ታማኝነቱን ትቶ፣ ከቦታቸው ያነሣቸውን ዕቃዎች ሁሉ አዘጋጅተን ቀድሰናቸዋል፤ እነሆ፤ ዕቃዎቹ በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ መሠዊያ ፊት ለፊት ናቸው።”

20በማግስቱም ጧት በማለዳ፣ ንጉሥ ሕዝቅያስ የከተማዪቱን ሹማምት በአንድነት ሰብስቦ፣ ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ወጣ፤ 21እነርሱም ስለ መንግሥቱ፣ ስለ መቅደሱና ስለ ይሁዳ ሰባት ወይፈኖች፣ ሰባት አውራ በጎች፣ ሰባት ተባዕት የበግ ጠቦቶችና ሰባት ተባዕት የፍየል ጠቦቶች ለኀጢአት መሥዋዕት አቀረቧቸው፤ ንጉሡም እነዚህን በእግዚአብሔር መሠዊያ ላይ እንዲያቀርቡ የአሮንን ዘሮች ካህናቱን አዘዘ። 22ካህናቱም ወይፈኖቹን ዐርደው ደሙን በመውሰድ በመሠዊያው ላይ ረጩት፤ አውራ በጎቹንም ዐርደው ደሙን በመሠዊያው ላይ ረጩት፤ እንደዚሁም ጠቦቶቹን ዐርደው ደሙን በመሠዊያው ላይ ረጩት። 23ለኀጢአት መሥዋዕት የሚሆኑትን ፍየሎች በንጉሡና በጉባኤው ፊት አቀረቡ፤ እነርሱም እጆቻቸውን ጫኑባቸው። 24ንጉሡ የሚቃጠል መሥዋዕትና የኀጢአት መሥዋዕት ስለ እስራኤል ሁሉ እንዲቀርብ አዝዞ ስለ ነበር፣ ካህናቱ ፍየሎቹን ዐርደው ስለ እስራኤል ሁሉ ማስተስረያ እንዲሆን የኀጢአት መሥዋዕት በማድረግ ደሙን በመሠዊያው ላይ አቀረቡ።

25ንጉሥ ሕዝቅያስም በዳዊት፣ በንጉሡ ባለ ራእይ በጋድና በነቢዩ በናታን በተሰጠው መመሪያ መሠረት ሌዋውያኑን ጸናጽል፣ በገናና መሰንቆ አስይዞ በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ መደባቸው፤ ይህም በነቢያት አማካይነት ከእግዚአብሔር የተሰጠ ትእዛዝ ነበር። 26ስለዚህ ሌዋውያኑ የዳዊትን የዜማ ዕቃዎች፣ ካህናቱም መለከቶቻቸውን ይዘው ዝግጁ በመሆን ቆሙ።

27ከዚህ በኋላ ሕዝቅያስ የሚቃጠለው መሥዋዕት በመሠዊያው ላይ እንዲቀርብ አዘዘ። መሥዋዕቱ ማረግ በጀመረ ጊዜም፣ በእስራኤል ንጉሥ በዳዊት የዜማ ዕቃዎችና በመለከት የታጀበ ዝማሬ ለእግዚአብሔር ማቅረብ ጀመረ። 28መዘምራኑ በሚዘምሩበትና መለከተኞቹም በሚነፉበት ጊዜም መላው ጉባኤ አጐንብሰው ሰገዱ፤ የሚቃጠለው መሥዋዕት እስኪጠናቀቅ ድረስም ይህ ሁሉ ቀጠለ።

29መሥዋዕቱ ሁሉ ቀርቦ ካበቃ በኋላ፣ ንጉሡና አብረውት የነበሩት ሁሉ ተንበርክከው ሰገዱ። 30ንጉሥ ሕዝቅያስና ሹማምቱ፣ ሌዋውያኑ በዳዊትና በባለ ራእዩ በአሳፍ ቃል እግዚአብሔርን እንዲያመሰግኑ አዘዙ። እነርሱም ውዳሴውን በደስታ ዘመሩ፤ ራሳቸውንም አጐንብሰው ሰገዱ።

31ከዚያም ሕዝቅያስ፣ “እነሆ፤ ራሳችሁን ለእግዚአብሔር ቀድሳችኋል፤ አሁንም ቅረቡ፤ መሥዋዕትና የምስጋና ስጦታ ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ አምጡ” አላቸው። ስለዚህ ጉባኤው መሥዋዕትና የምስጋና ስጦታ አመጡ፤ ልባቸው የፈቀደ ሁሉም የሚቃጠል መሥዋዕት አመጡ።

32ጉባኤውም ያመጣው የሚቃጠለው መሥዋዕት ብዛት ሰባ ወይፈኖች፣ መቶ አውራ በጎችና ሁለት መቶ ተባዕት የበግ ጠቦቶች ናቸው፤ ሁሉም የሚቃጠል መሥዋዕት ሆነው ለእግዚአብሔር የሚቀርቡ ነበሩ። 33ለመሥዋዕት የተቀደሱት እንስሳት በአጠቃላይ ስድስት መቶ ወይፈን፣ ሦስት ሺሕ በጎችና ፍየሎች ነበሩ። 34ይሁን እንጂ ካህናቱ የሚቃጠለውን መሥዋዕት ቈዳ ሁሉ ለመግፈፍ ቍጥራቸው እጅግ ጥቂት ነበር፤ ስለዚህ ወገኖቻቸው የሆኑት ሌዋውያን ሥራው እስኪያልቅና ሌሎች ካህናት እስኪቀደሱ ድረስ ረዷቸው፤ ሌዋውያኑም ራሳቸውን ለመቀደስ ከካህናቱ ይልቅ ጠንቃቆች ነበሩና። 35ከሚቃጠለው መሥዋዕት ጋር የሚቀርበውን የኅብረት መሥዋዕት29፥35 በትውፊት የሰላም መሥዋዕት ይባላል። ስብና የመጠጡን ቍርባን ጨምሮ የሚቃጠለው መሥዋዕት እጅግ ብዙ ነበር። በዚህ ሁኔታም የእግዚአብሔር ቤት አገልግሎት እንደ ገና ተደራጀ። 36ሕዝቅያስና ሕዝቡ፣ ነገሩ ሁሉ እንዲህ በተፋጠነ ሁኔታ እንዲከናወን እግዚአብሔር ስለ ረዳቸው ሐሴት አደረጉ።

New International Reader’s Version

2 Chronicles 29:1-36

Hezekiah Purifies the Temple

1Hezekiah was 25 years old when he became king. He ruled in Jerusalem for 29 years. His mother’s name was Abijah. She was the daughter of Zechariah. 2Hezekiah did what was right in the eyes of the Lord, just as King David had done.

3In the first month of Hezekiah’s first year as king, he opened the doors of the Lord’s temple. He repaired them. 4He brought the priests and Levites in. He gathered them together in the open area on the east side of the temple. 5He said, “Levites, listen to me! Set yourselves apart to the Lord. Set apart the temple of the Lord. He’s the God of your people who lived long ago. Remove anything ‘unclean’ from the temple. 6Our people weren’t faithful. They did what was evil in the eyes of the Lord our God. They deserted him. They turned their faces away from the place where he lives. They turned their backs on him. 7They also shut the doors of the temple porch. They put the lamps out. They didn’t burn incense at the temple. They didn’t sacrifice burnt offerings there to the God of Israel. 8So the Lord has become angry with Judah and Jerusalem. He has made them look so bad that everyone is shocked when they see them. They laugh at them. You can see it with your own eyes. 9That’s why our fathers have been killed by swords. That’s why our sons and daughters and wives have become prisoners. 10So I’m planning to make a covenant with the Lord, the God of Israel. Then he’ll stop being angry with us. 11My sons, don’t fail to obey the Lord. He has chosen you to stand in front of him and work for him. He wants you to serve him and burn incense to him.”

12Here are the Levites who went to work.

Mahath and Joel were from the family line of Kohath.

Mahath was the son of Amasai. Joel was the son of Azariah.

Kish and Azariah were from the family line of Merari.

Kish was the son of Abdi. Azariah was the son of Jehallelel.

Joah and Eden were from the family line of Gershon.

Joah was the son of Zimmah. Eden was the son of Joah.

13Shimri and Jeiel were from the family line of Elizaphan.

Zechariah and Mattaniah were from the family line of Asaph.

14Jehiel and Shimei were from the family line of Heman.

Shemaiah and Uzziel were from the family line of Jeduthun.

15All these Levites gathered the other Levites together. They set themselves apart to the Lord. Then they went in to purify the Lord’s temple. That’s what the king had ordered them to do. They did what the Lord told them to. 16The priests went into the Lord’s temple to make it pure. They brought out to the temple courtyard everything that was “unclean.” They had found “unclean” things in the Lord’s temple. The Levites took them and carried them out to the Kidron Valley. 17On the first day of the first month they began to set everything in the temple apart to the Lord. By the eighth day of the month they reached the Lord’s porch. For eight more days they set the Lord’s temple itself apart to him. They finished on the 16th day of the first month.

18Then they went to King Hezekiah. They reported, “We’ve purified the whole temple of the Lord. That includes the altar for burnt offerings and all its tools. It also includes the table for the holy bread and all its objects. 19We’ve prepared all the things King Ahaz had removed. We’ve set them apart to the Lord. Ahaz had removed them while he was king. He wasn’t faithful to the Lord. Those things are now in front of the Lord’s altar.”

20Early the next morning King Hezekiah gathered together the city officials. They all went up to the Lord’s temple. 21They brought seven bulls, seven rams, seven male lambs and seven male goats with them. They sacrificed the animals as a sin offering for the kingdom, for the temple and for Judah. The king commanded the priests to offer them on the Lord’s altar. The priests were from the family line of Aaron. 22They killed the bulls. Then they splashed the blood against the altar. Next they killed the rams and splashed the blood against the altar. Then they killed the lambs and splashed the blood against the altar. 23The goats for the sin offering were brought to the king and the whole community. They placed their hands on them. 24Then the priests killed the goats. They put the blood on the altar as a sin offering. It paid for the sin of the whole nation of Israel. The king had ordered the burnt offering and the sin offering for the whole nation.

25Hezekiah stationed the Levites in the Lord’s temple. They had cymbals, harps and lyres. They did everything in the way King David, his prophet Gad, and Nathan the prophet had required. The Lord had given commands about all these things through his prophets. 26So the Levites stood ready with David’s musical instruments. And the priests had their trumpets ready.

27Hezekiah gave the order to sacrifice the burnt offering on the altar. The offering began. Singing to the Lord also began. The singing was accompanied by the trumpets and by the instruments of David. He had been king of Israel. 28The whole community bowed down. They worshiped the Lord. At the same time the musicians played their musical instruments. The priests blew their trumpets. All of that continued until the burnt offering had been sacrificed.

29So the offerings were finished. King Hezekiah got down on his knees. He worshiped the Lord. So did everyone who was with him. 30The king and his officials ordered the Levites to praise the Lord. They used the words of David and Asaph the prophet. They sang praises with joy. They bowed down and worshiped the Lord.

31Then Hezekiah said, “You have set yourselves apart to the Lord. Come and bring sacrifices and thank offerings to his temple.” So the whole community brought sacrifices and thank offerings. Everyone who wanted to brought burnt offerings.

32The whole community brought 70 bulls, 100 rams and 200 male lambs. They brought all of them as burnt offerings to the Lord. 33The total number of animals set apart as sacrifices to the Lord was 600 bulls and 3,000 sheep and goats. 34But there weren’t enough priests to skin all the burnt offerings. So their relatives, the Levites, helped them. They worked until the task was finished. By that time other priests had been set apart to the Lord. The Levites had been more careful than the priests when they set themselves apart. 35There were large numbers of burnt offerings, along with the drink offerings and the fat from the friendship offerings. They were offered along with the burnt offerings.

So the service of the Lord’s temple was started up again. 36Hezekiah and all the people were filled with joy. That’s because everything had been done so quickly. God had provided for his people in a wonderful way.