2 ዜና መዋዕል 26 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

2 ዜና መዋዕል 26:1-23

የይሁዳ ንጉሥ ዖዝያን

26፥1-4 ተጓ ምብ – 2ነገ 14፥21-2215፥1-3

26፥21-23 ተጓ ምብ – 2ነገ 15፥5-7

1ከዚህ በኋላ የይሁዳ ሕዝብ በሙሉ ዕድሜው ዐሥራ ስድስት ዓመት የነበረውን ዖዝያንን ወስደው በአባቱ በአሜስያስ ፈንታ አነገሡት። 2አሜስያስ እንደ አባቶቹ ሁሉ ካንቀላፋ በኋላ፣ ኤላትን እንደ ገና የሠራት፣ ወደ ይሁዳም የመለሳት ዖዝያን ነበር።

3ዖዝያን በነገሠ ጊዜ፣ ዕድሜው ዐሥራ ስድስት ዓመት ሲሆን፣ በኢየሩሳሌም ተቀምጦ26፥3 ብዙ የዕብራይስጥ ትርጕሞች፣ የሰብዓ ሊቃናትና የሱርስቱ ቅጅ ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ አንዳንድ የዕብራስጥ ቅጆች ግን እንደ እግዚአብሔር ራእይ ባስተማረው ይላሉ። አምሳ ሁለት ዓመት ገዛ። እናቱ ይኮልያ የተባለች የኢየሩሳሌም ሴት ነበረች። 4እርሱም አባቱ አሜስያስ እንደ አደረገው ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት ቅን ነገር አደረገ። 5እግዚአብሔርን መፍራት ባስተማረው በዘካርያስ ዘመን እግዚአብሔርን ፈለገ፤ እግዚአብሔርን በፈለገ መጠንም አምላክ ነገሮችን አከናወነለት።

6በፍልስጥኤማውያን ላይ ዘምቶ የጌትን፣ የየብናንና የአዛጦንን ቅጥሮች አፈረሰ። ከዚያም በአዛጦን አጠገብና በቀሩትም የፍልስጥኤም ግዛቶች ውስጥ ከተሞችን እንደ ገና ሠራ። 7እግዚአብሔርም በፍልስጥኤማውያን፣ በጉርበኣል በሚኖሩ ዐረቦችና በምዑናውያን ላይ ድልን አቀዳጀው። 8አሞናውያን ለዖዝያን ግብር ገበሩለት፤ ኀይሉ ስለ ገነነም ዝናው እስከ ግብፅ ዳርቻ ወጣ።

9ዖዝያንም በኢየሩሳሌም በማእዘኑ በር፣ በሸለቆው በርና በቅጥሩ ማዕዘን ማማዎች ሠርቶ መሸጋቸው። 10እንዲሁም በየኰረብታው ግርጌና በየሜዳው ላይ ብዙ የቀንድ ከብት ስለ ነበረው፣ በምድረ በዳ የግንብ ማማዎች ሠራ፤ ብዙ የውሃ ጕድጓዶችም ቈፈረ። ግብርና ይወድ ስለ ነበረም በኰረብታዎችና ለም በሆኑ መሬቶች ላይ ዕርሻ የሚያርሱና ወይን የሚተክሉ ሠራተኞች ነበሩት።

11ዖዝያን ከንጉሡ ሹማምት አንዱ በሆነው በሐናንያ መሪነት፣ በጸሓፊው በይዒኤልና በአለቃው በመዕሤያ አማካይነት ተሰብስቦ በተቈጠረው መሠረት በየምድቡ ለጦርነት ዝግጁ ሆኖ የሚወጣ፣ በሚገባ የሠለጠነ ሰራዊት ነበረው። 12በተዋጊዎቹ ላይ የተሾሙት የየቤተ ሰቡ መሪዎች ጠቅላላ ቍጥር ሁለት ሺሕ ስድስት መቶ ነበር። 13በእነዚህም የሚመራ ሦስት መቶ ሰባት ሺሕ አምስት መቶ ሰው ያለው ሰራዊት አለ፤ ይህም ንጉሡ በጠላቶቹ ላይ በሚያደርገው ዘመቻ ለመሰለፍ የሚበቃ ጠንካራ ኀይል ነበር። 14ዖዝያን ለሰራዊቱ ሁሉ ጋሻ፣ ጦር፣ የራስ ቍር፣ ጥሩር፣ የቀስት ማስፈንጠሪያ ደጋንና የሚወነጨፍ ድንጋይ አደለ። 15በኢየሩሳሌምም፣ ንድፎቻቸው በባለሙያዎች የተዘጋጁ፣ በመጠበቂያ የግንብ ማማዎችና በየማእዘኑ መከላከያዎች ላይ ፍላጻ የሚስፈነጠርባቸውንና ትልልቅ ድንጋዮች የሚወረወርባቸውን መሣሪያዎች አሠራ። እስኪበረታም ድረስ በሚያስደንቅ ሁኔታ ስለ ታገዘ፣ ዝናው በርቀትና በስፋት ተሰማ።

16ዖዝያን ከበረታ በኋላ ግን ዕብሪቱ ለውድቀት ዳረገው። በዕጣን መሠዊያው ላይ ዕጣን ለማጠን ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ በመግባቱ አምላኩን እግዚአብሔርን በደለ፤ 17ካህኑም ዓዛርያስ ቈራጥ ከሆኑ ከሌሎች ሰማንያ የእግዚአብሔር ካህናት ጋር ተከትሎት ገባ። 18እነርሱም ፊት ለፊት በመጋፈጥ፣ “ዖዝያን ሆይ፤ ለእግዚአብሔር ማጠን ለተለዩትና የአሮን ዘሮች ለሆኑት ለካህናቱ እንጂ ለአንተ የተገባ አይደለም፤ እግዚአብሔርን በድለሃልና ከመቅደሱ ውጣ፤ ከእግዚአብሔር አምላክ ዘንድም ክብር አይሆንልህምና” አሉት።

19ጥና በእጁ ይዞ ዕጣን ለማጠን ዝግጁ የነበረው ዖዝያን ተቈጣ፤ በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ውስጥ በዕጣን መሠዊያው ፊት ሆኖ ካህናቱ ላይ እየተቈጣ ሳለ፣ በግንባሩ ላይ ለምጽ26፥19 የዕብራይስጡ ቃል በዚህም ሆነ በቍጥር 20፡21 እና 23 ላይ ማንኛውንም ዐይነት የቈዳ በሽታ የሚያመለክት ነው። ወጣበት። 20ሊቀ ካህናቱ ዓዛርያስና ሌሎቹ ካህናት ሁሉ በተመለከቱት ጊዜ፣ በግንባሩ ላይ ለምጽ እንደ ወጣበት አዩ። ስለዚህ አጣድፈው አስወጡት፤ በርግጥ እርሱም ራሱ ለመውጣት ቸኵሎ ነበር፤ እግዚአብሔር አስጨንቆታልና።

21ንጉሥ ዖዝያን እስከ ዕለተ ሞቱ ድረስ ለምጻም ነበረ። ለምጻም በመሆኑም ከቤተ መቅደስ ተወግዶ ነበርና በተለየ ቤት ተቀመጠ26፥21 ወይም ከኀላፊነቱ በሚርቅበት ቤት ተብሎ መተርጕም ይችላል።። ከዚያም ልጁ ኢዮአታም የቤተ መንግሥቱን አስተዳደር በኀላፊነት ተረክቦ የአገሩን ሕዝብ ይመራ ጀመር።

22በዖዝያን ዘመነ መንግሥት ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው የተከናወነውን ሌላውን ተግባር ሁሉ የአሞጽ ልጅ ነቢዩ ኢሳይያስ ጽፎታል። 23ዖዝያንም እንደ አባቶቹ ሁሉ አንቀላፋ። ሕዝቡም “ለምጽ አለበት” ብለው የነገሥታቱ በሆነው መቃብር አጠገብ ባለው ቦታ ቀበሩት፤ ልጁም ኢዮአታም በእርሱ ፈንታ ነገሠ።

Persian Contemporary Bible

دوم تواريخ 26:1-23

عزيا، پادشاه يهودا

(دوم پادشاهان 14‏:21‏-22، 15‏:1‏-7)

1مردم يهودا، عزيا را كه شانزده ساله بود به جای پدرش امصيا پادشاه خود ساختند. 2عزيا پس از مرگ پدرش شهر ايلت را برای يهودا پس گرفت و آن را بازسازی كرد. 3او پنجاه و دو سال در اورشليم سلطنت نمود. (مادرش يكليای اورشليمی بود.) 4او مانند پدرش امصيا آنچه در نظر خداوند پسنديده بود انجام می‌داد. 5تا زمانی كه مشاور روحانی او، زكريا زنده بود، او از خدا پيروی می‌كرد و خدا نيز او را موفق می‌ساخت.

6عزيا به جنگ فلسطينی‌ها رفت و شهر جت را گرفت و حصار آن را خراب كرد و با شهرهای يبنه و اشدود نيز به همين طريق عمل نمود. سپس در ناحيهٔ اشدود و قسمتهای ديگر فلسطين شهرهای تازه‌ای ساخت. 7خدا نه فقط او را در جنگ با فلسطينی‌ها ياری نمود، بلكه در نبرد با عربهای جوربعل و معونی‌ها نيز وی را امداد فرمود. 8عمونی‌ها باج و خراج به او می‌پرداختند و نام او تا مصر شهرت يافت زيرا او بسيار نيرومند شده بود.

9عزيا در شهر اورشليم نزد دروازهٔ زاويه، دروازهٔ دره و جايی كه حصار اورشليم می‌پيچيد قلعه‌های محكمی بنا كرد. 10همچنين در صحرا برجها ساخت و چاههای بسيار كند زيرا در دشتها و دره‌ها، گله‌های بسيار داشت. عزيا به كشاورزی علاقمند بود و به همين جهت در دامنهٔ تپه‌ها و دشتهای حاصلخيز، مزرعه‌ها و تاكستانهای فراوانی داشت.

11سپاه عزيا از سربازان جنگ آزموده‌ای تشكيل شده بود. در زمان جنگ، يعی‌ئيل، کاتب و معسيا، معاون حننيا كه يكی از درباريان بود، سپاه را به چند دسته تقسيم كرده، سان می‌ديدند. 12دو هزار و ششصد نفر از سران قبايل، فرماندهی اين دسته‌ها را به عهده داشتند. 13سپاه زير دست آنها از ۳۰۷,۵۰۰ سرباز زبده تشكيل شده بود كه با شجاعت از پادشاه در مقابل دشمن دفاع می‌كردند. 14عزيا برای تمام افراد سپاه سپر، نيزه، كلاهخود، زره، كمان و فلاخن تهيه كرد. 15به دستور او منجنيقهايی بوسيلهٔ صنعتگران ماهر در اورشليم ساخته شد تا با آنها از بالای برجها و باروها تير و سنگ به سوی دشمن پرتاب كنند. به اين ترتيب او بسيار معروف و قوی شد، زيرا خدا وی را كمک می‌كرد.

مجازات عزيا به خاطر غرورش

16اما قدرت عزيا باعث غرور و تباهی او گرديد. او وارد خانهٔ خداوند شد و شخصاً بر قربانگاه آن بخور سوزانيد و به اين وسيله بر ضد خداوند، خدای خود مرتكب گناه شد. 17پشت سر او عزريا، كاهن اعظم با هشتاد كاهن ديگر كه همه مردانی شجاع بودند وارد خانهٔ خداوند شده 18با عزيای پادشاه به مخالفت پرداختند و گفتند: «ای عزيا، سوزاندن بخور برای خداوند كار تو نيست! اين فقط وظيفهٔ كاهنان نسل هارون است كه برای همين منظور تقديس26‏:18 تقديس يعنی جدا کردن، اختصاص دادن و مقدس ساختن.‏ شده‌اند. از اينجا خارج شو، چون گناه كرده‌ای و خداوند از اين عمل تو خشنود نخواهد شد.»

19عزيا كه كنار قربانگاه بخور ايستاده بود غضبناک شد و نخواست ظرف بخوری را كه در دست داشت بر زمين بگذارد. در اين هنگام ناگهان مرض جذام در پيشانی او ظاهر شد! 20عزريا و كاهنان ديگر وقتی اين را ديدند، با شتاب او را بيرون بردند. او خود نيز می‌خواست هر چه زودتر از خانهٔ خدا خارج شود، زيرا خداوند او را مجازات كرده بود.

21عزيای پادشاه تا روز وفاتش جذامی بود و در خانه‌ای، تنها به سر می‌برد و اجازه نداشت به خانهٔ خداوند وارد شود. پسرش يوتام امور مملكت را اداره می‌كرد.

22شرح بقيهٔ رويدادهای دوران سلطنت عزيا، از ابتدا تا انتها، توسط اشعيای نبی (پسر آموص) نوشته شده است. 23وقتی عزيا وفات يافت، با اينكه جذامی بود، او را در آرامگاه سلطنتی به خاک سپردند و پسرش يوتام سلطنت را به دست گرفت.