2 ዜና መዋዕል 23 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

2 ዜና መዋዕል 23:1-21

1በሰባተኛው ዓመት ዮዳሄ በረታ፤ የመቶ አለቆች ከሆኑት ከይሮሐም ልጅ ከዓዛርያስ፣ ከይሆሐናን ልጅ ከይስማኤል፣ ከዖቤድ ልጅ ከዓዛርያስ፣ ከዓዳያ ልጅ ከማዕሤያ፣ ከዝክሪ ልጅ ከኤሊሳፋጥ ጋር ቃል ኪዳን አደረገ። 2እነርሱም ወደ መላው ይሁዳ ሄደው፣ ሌዋውያንንና የእስራኤል ቤት አለቆችን ከየከተማው ሁሉ ሰበሰቡ። ወደ ኢየሩሳሌም በመጡ ጊዜም፣ 3ጉባኤው ሁሉ በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ውስጥ ከንጉሡ ጋር ቃል ኪዳን አደረጉ።

ዮዳሄም እንዲህ አላቸው፤ “እግዚአብሔር ለዳዊት ዘር በሰጠው ተስፋ መሠረት እነሆ፤ የንጉሡ ልጅ ይነግሣል። 4እንግዲህ እናንተ የምታደርጉት ይህ ነው፤ በሰንበት ዕለት ተረኛ ከሆናችሁት ከእናንተ ከካህናቱና ከሌዋውያኑ አንድ ሦስተኛው በሮቹን ጠብቁ፤ 5አንድ ሦስተኛው ቤተ መንግሥቱን፣ አንድ ሦስተኛው ‘የመሠረት ቅጽር በር’ የተባለውን ጠብቁ፤ የቀሩት ሰዎች በሙሉ በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ አደባባይ ይሁኑ። 6ተረኛ ከሆኑት ካህናትና ሌዋውያን በቀር ማንም ሰው ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ አይግባ፤ እነርሱ የተቀደሱ ስለሆኑ ይግቡ፤ የቀሩት ሰዎች በሙሉ ግን፣ ወደ ቤተ መቅደሱ እንዳይገቡ እግዚአብሔር ያዘዘውን ይጠብቁ23፥6 ወይም አይግባ የሚለውን የእግዚአብሔር ትእዛዝ ይጠብቁ7ሌዋውያኑም የጦር መሣሪያቸውን በእጃቸው ይዘው በንጉሡ ዙሪያ ይቁሙ፤ ወደ ቤተ መቅደሱ የሚገባ ማንኛውም ሰው ይገደል፤ ንጉሡ በሚሄድበትም ቦታ ሁሉ አብረውት ይሁኑ።”

8ሌዋውያኑና ይሁዳ ሁሉ ልክ ካህኑ ዮዳሄ እንዳዘዘው አደረጉ፤ ካህኑ ዮዳሄ ከጥበቃ ክፍሎች የትኛውንም አላሰናበተም ነበርና፣ እያንዳንዱ በሰንበት ቀን በሥራ ላይ የሚሰማሩትንና ከሥራ የሚወጡትን የራሱን ሰዎች ወሰደ፤ 9ከዚያም በቤተ መቅደሱ የነበሩትን የንጉሥ ዳዊት ጦሮች፣ ታላላቅና ታናናሽ ጋሻዎች ለመቶ አለቆቹ ሰጣቸው። 10ሰዎቹም ሁሉ እያንዳንዳቸው መሣሪያቸውን በእጃቸው እንደ ያዙ ከቤተ መቅደሱ ደቡብ አንሥቶ እስከ ሰሜን ድረስ በመሠዊያውና በቤተ መቅደሱ አጠገብ በንጉሡ ዙሪያ እንዲቆሙ አደረገ።

11ዮዳሄና ወንዶች ልጆቹ የንጉሡን ልጅ አምጥተው ዘውድ ጫኑለት፤ የኪዳኑንም መጽሐፍ ሰጥተውት አነገሡት፤ ቀብተውትም፣ “ንጉሡ ለዘላለም ይኑር!” እያሉ ጮኹ።

12ጎቶልያም የሚሯሯጠውንና ደስታውን ለንጉሡ የሚገልጠውን ሕዝብ ሁካታ ስትሰማ፣ ሕዝቡ ወዳለበት ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ሄደች። 13ንጉሡ በመግቢያው ላይ ባለው በዐምዱ አጠገብ ቆሞ አየች፣ የጦር መኮንኖችና መለከት ነፊዎችም በንጉሡ አጠገቡ ነበሩ፤ የምድሪቱ ሕዝብ ሁሉ ይደሰቱ፣ መለከትም ይነፉ ነበር፤ መዘምራንም በዜማ ዕቃ ታጅበው የበዓሉን ዝማሬ ይመሩ ነበር፤ ጎቶልያም ልብሷን ቀድዳ፣ “ይህ ዐመፅ ነው! ይህ ዐመፅ ነው!” ብላ ጮኸች።

14ካህኑ ዮዳሄም የወታደር አዛዥ ወደ ሆኑት ወደ መቶ አለቆቹ፣ “በሰልፉ መካከል አውጥታችሁ አምጧት23፥14 ወይም ከቅጥሩ ውስጥ አውጥታችሁ አምጧት፤ የሚከተላት ካለም በሰይፍ ግደሉት” ሲል ላከባቸው። ካህኑም፣ “በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ አትግደሏት” ብሎ ነበርና። 15እርሷም በቤተ መንግሥቱ ግቢ የፈረስ መግቢያ በር ወደ ተባለው ቦታ እንደ ደረሰች ያዟት፤ በዚያም ገደሏት።

16ዮዳሄም ራሱ፣ ሕዝቡና ንጉሡ የእግዚአብሔር ሕዝብ እንደሚሆኑ ቃል ኪዳን ገባ23፥16 ወይም በእግዚአብሔር በሕዝቡና በንጉሡ መካከል የተደረገው ቃል ኪዳን (2ነገ 11፥17)17ከዚህ በኋላ ሕዝቡ በሙሉ ሄዶ የበኣልን ቤተ ጣዖት አፈረሰው፤ መሠዊያዎቹንና ጣዖታቱን አደቀቀ፤ የበኣልን ካህን ማታንንም በመሠዊያዎቹ ፊት ለፊት ገደሉት። 18ዮዳሄ በሙሴ ሕግ እንደ ተጻፈውና ዳዊትም እንዳዘዘው፣ በደስታና በመዝሙር የሚቃጠለውን የእግዚአብሔርን መሥዋዕት እንዲያቀርቡ ዳዊት ለመደባቸው ካህናትና ሌዋውያን የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ኀላፊነት ሰጣቸው። 19እንዲሁም በማንኛውም ነገር የረከሰ ሰው እንዳይገባ፣ በቤተ መቅደሱ ቅጥር በሮች ላይ ጠባቆች አቆመ። 20የመቶ አለቆቹን፣ መኳንንቱን፣ የሕዝቡን ገዦችና የአገሩን ሕዝብ ሁሉ ይዞ ንጉሡን ከላይ ከቤተ መቅደሱ ወደ ታች አመጣው። በላይኛውም መግቢያ በኩል ወደ ቤተ መንግሥቱ ገብተው ንጉሡን በመንግሥቱ ዙፋን ላይ አስቀመጡት። 21መላውም የአገሩ ሕዝብ ተደሰተ፤ ጎቶልያ ስለ ተገደለችም ከተማዪቱ ሰላም አግኝታ ነበር።

Thai New Contemporary Bible

2พงศาวดาร 23:1-21

1ในปีที่เจ็ดแห่งรัชกาล ปุโรหิตเยโฮยาดาตัดสินใจอย่างเด็ดเดี่ยว ทำพันธสัญญากับผู้บัญชาการกองร้อยได้แก่ อาซาริยาห์บุตรเยโรฮัม อิชมาเอลบุตรเยโฮฮานัน อาซาริยาห์บุตรโอเบด มาอาเสอาห์บุตรอาดายาห์ และเอลีชาฟัทบุตรศิครี 2คนเหล่านี้เดินทางไปทั่วยูดาห์ เพื่อแจ้งคนเลวีและหัวหน้าครอบครัวต่างๆ ของอิสราเอลจากทุกเมืองให้มาชุมนุมกันที่กรุงเยรูซาเล็ม 3ประชากรทั้งหมดทำพันธสัญญากับกษัตริย์ที่พระวิหารของพระเจ้า

เยโฮยาดากล่าวกับพวกเขาว่า “ราชโอรสจะขึ้นครองราชย์ตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงสัญญาไว้เกี่ยวกับวงศ์วานของดาวิด 4ท่านทั้งหลายจะดำเนินการดังนี้ หนึ่งในสามของพวกท่านที่เป็นปุโรหิตและคนเลวีซึ่งประจำหน้าที่ในวันสะบาโตจะเฝ้าอยู่ที่ประตูต่างๆ 5อีกหนึ่งในสามที่พระราชวัง และอีกหนึ่งในสามที่ประตูฐานราก คนอื่นนอกนั้นให้อยู่ที่ลานพระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้า 6อย่าให้ใครเข้าไปในพระวิหารของ องค์พระผู้เป็นเจ้า นอกจากปุโรหิตกับคนเลวีซึ่งประจำหน้าที่ เนื่องจากพวกเขาได้รับการชำระให้บริสุทธิ์แล้ว ส่วนคนอื่นๆ ให้ปฏิบัติตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงมอบหมาย23:6 หรือให้ถือรักษาพระบัญชาขององค์พระผู้เป็นเจ้า อย่าเข้าไป 7คนเลวีจงอารักขากษัตริย์ ถืออาวุธพร้อม และประหารทุกคนที่ล่วงล้ำเข้ามาในพระวิหาร ขอให้พวกท่านอยู่เคียงข้างองค์กษัตริย์เสมอไม่ว่าพระองค์จะเสด็จไปที่ไหน”

8คนเลวีและชายชาวยูดาห์ทั้งหมดก็ทำตามคำสั่งของปุโรหิตเยโฮยาดา แต่ละคนก็นำคนของตนไป ทั้งคนที่จะเข้าเวรในวันสะบาโตและคนที่จะพ้นเวร เพราะปุโรหิตเยโฮยาดาไม่ปล่อยให้ออกเวร 9จากนั้นเยโฮยาดานำหอกพร้อมทั้งโล่ใหญ่และเล็กของกษัตริย์ดาวิดซึ่งเก็บไว้ในคลังพระวิหารออกมาแจกจ่ายแก่นายกองทั้งปวง 10ทหารเหล่านี้ซึ่งมีอาวุธครบครันคอยถวายการอารักขากษัตริย์ที่ใกล้ๆ แท่นบูชา และจากด้านทิศใต้ของพระวิหารไปจดด้านทิศเหนือ

11เยโฮยาดากับบุตรทั้งหลายนำราชโอรสออกมาและสวมมงกุฎให้พระองค์ ถวายหนังสือพันธสัญญา และประกาศว่าพระองค์เป็นกษัตริย์ พวกเขาเจิมพระองค์และโห่ร้องว่า “ขอกษัตริย์จงทรงพระเจริญ!”

12เมื่อพระนางอาธาลิยาห์ได้ยินเสียงอึกทึกของประชาชน และเสียงโห่ร้องต้อนรับกษัตริย์ ก็เสด็จมาพบพวกเขาที่พระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้า 13พระนางทอดพระเนตรเห็นกษัตริย์ประทับยืนอยู่ข้างเสาตรงทางเข้า มีเจ้าหน้าที่กับคนเป่าแตรอยู่ข้างพระองค์ และปวงชนกำลังรื่นเริงยินดีและเป่าแตร นักร้องก็บรรเลงดนตรีนำการสดุดี พระนางอาธาลิยาห์ก็ทรงฉีกฉลองพระองค์และร้องตะโกนว่า “กบฏ! กบฏ!”

14ปุโรหิตเยโฮยาดาส่งบรรดาผู้บังคับกองร้อยซึ่งรับผิดชอบกองทหารออกไปและสั่งว่า “คุมตัวพระนางออกไปจากแถวทหาร23:14 หรือจากบริเวณนี้ อย่าประหารพระนางในพระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้า แต่ให้ฆ่าทุกคนที่พยายามจะเข้ามาช่วยพระนาง” 15พวกเขาจึงคุมตัวพระนางไปยังประตูที่ม้าผ่านเข้าพระราชวังและปลงพระชนม์พระนางที่นั่น

16จากนั้นเยโฮยาดาได้ทำพันธสัญญาร่วมกับประชาชนและกษัตริย์ว่า23:16 หรือทำพันธสัญญาระหว่างองค์พระผู้เป็นเจ้ากับประชาชนและกษัตริย์ว่าพวกเขา(ดู2พกษ.11:17)จะเป็นประชากรขององค์พระผู้เป็นเจ้า 17แล้วทุกคนกรูเข้าไปรื้อทำลายวิหารของพระบาอัล ทุบแท่นบูชาและเทวรูปทั้งหลายทิ้งและประหารมัททานปุโรหิตของพระบาอัลตรงหน้าแท่น

18แล้วเยโฮยาดาแต่งตั้งปุโรหิตซึ่งเป็นชนเลวีให้ดูแลพระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้าตามที่ดาวิดมอบหมายไว้ เพื่อถวายเครื่องเผาบูชาแด่องค์พระผู้เป็นเจ้าตามที่บันทึกไว้ในบทบัญญัติของโมเสสด้วยความชื่นชมยินดีและด้วยการร้องเพลงตามที่ดาวิดตรัสสั่งไว้ 19เยโฮยาดายังได้ตั้งยามประตูพระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้า เพื่อไม่ให้ผู้ที่เป็นมลทินด้วยเหตุหนึ่งเหตุใดเข้าไปได้

20จากนั้นเยโฮยาดาร่วมกับบรรดานายกอง ขุนนาง ผู้ปกครอง และประชาชนทั้งปวง นำเสด็จกษัตริย์จากพระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้า ดำเนินผ่านประตูบนสู่พระราชวัง และอัญเชิญขึ้นประทับบนราชบัลลังก์ 21ประชาชนทั่วแดนพากันชื่นชมยินดีและนครก็สงบสุข เพราะพระนางอาธาลิยาห์ถูกประหารด้วยดาบแล้ว