2 ዜና መዋዕል 23 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

2 ዜና መዋዕል 23:1-21

1በሰባተኛው ዓመት ዮዳሄ በረታ፤ የመቶ አለቆች ከሆኑት ከይሮሐም ልጅ ከዓዛርያስ፣ ከይሆሐናን ልጅ ከይስማኤል፣ ከዖቤድ ልጅ ከዓዛርያስ፣ ከዓዳያ ልጅ ከማዕሤያ፣ ከዝክሪ ልጅ ከኤሊሳፋጥ ጋር ቃል ኪዳን አደረገ። 2እነርሱም ወደ መላው ይሁዳ ሄደው፣ ሌዋውያንንና የእስራኤል ቤት አለቆችን ከየከተማው ሁሉ ሰበሰቡ። ወደ ኢየሩሳሌም በመጡ ጊዜም፣ 3ጉባኤው ሁሉ በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ውስጥ ከንጉሡ ጋር ቃል ኪዳን አደረጉ።

ዮዳሄም እንዲህ አላቸው፤ “እግዚአብሔር ለዳዊት ዘር በሰጠው ተስፋ መሠረት እነሆ፤ የንጉሡ ልጅ ይነግሣል። 4እንግዲህ እናንተ የምታደርጉት ይህ ነው፤ በሰንበት ዕለት ተረኛ ከሆናችሁት ከእናንተ ከካህናቱና ከሌዋውያኑ አንድ ሦስተኛው በሮቹን ጠብቁ፤ 5አንድ ሦስተኛው ቤተ መንግሥቱን፣ አንድ ሦስተኛው ‘የመሠረት ቅጽር በር’ የተባለውን ጠብቁ፤ የቀሩት ሰዎች በሙሉ በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ አደባባይ ይሁኑ። 6ተረኛ ከሆኑት ካህናትና ሌዋውያን በቀር ማንም ሰው ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ አይግባ፤ እነርሱ የተቀደሱ ስለሆኑ ይግቡ፤ የቀሩት ሰዎች በሙሉ ግን፣ ወደ ቤተ መቅደሱ እንዳይገቡ እግዚአብሔር ያዘዘውን ይጠብቁ23፥6 ወይም አይግባ የሚለውን የእግዚአብሔር ትእዛዝ ይጠብቁ7ሌዋውያኑም የጦር መሣሪያቸውን በእጃቸው ይዘው በንጉሡ ዙሪያ ይቁሙ፤ ወደ ቤተ መቅደሱ የሚገባ ማንኛውም ሰው ይገደል፤ ንጉሡ በሚሄድበትም ቦታ ሁሉ አብረውት ይሁኑ።”

8ሌዋውያኑና ይሁዳ ሁሉ ልክ ካህኑ ዮዳሄ እንዳዘዘው አደረጉ፤ ካህኑ ዮዳሄ ከጥበቃ ክፍሎች የትኛውንም አላሰናበተም ነበርና፣ እያንዳንዱ በሰንበት ቀን በሥራ ላይ የሚሰማሩትንና ከሥራ የሚወጡትን የራሱን ሰዎች ወሰደ፤ 9ከዚያም በቤተ መቅደሱ የነበሩትን የንጉሥ ዳዊት ጦሮች፣ ታላላቅና ታናናሽ ጋሻዎች ለመቶ አለቆቹ ሰጣቸው። 10ሰዎቹም ሁሉ እያንዳንዳቸው መሣሪያቸውን በእጃቸው እንደ ያዙ ከቤተ መቅደሱ ደቡብ አንሥቶ እስከ ሰሜን ድረስ በመሠዊያውና በቤተ መቅደሱ አጠገብ በንጉሡ ዙሪያ እንዲቆሙ አደረገ።

11ዮዳሄና ወንዶች ልጆቹ የንጉሡን ልጅ አምጥተው ዘውድ ጫኑለት፤ የኪዳኑንም መጽሐፍ ሰጥተውት አነገሡት፤ ቀብተውትም፣ “ንጉሡ ለዘላለም ይኑር!” እያሉ ጮኹ።

12ጎቶልያም የሚሯሯጠውንና ደስታውን ለንጉሡ የሚገልጠውን ሕዝብ ሁካታ ስትሰማ፣ ሕዝቡ ወዳለበት ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ሄደች። 13ንጉሡ በመግቢያው ላይ ባለው በዐምዱ አጠገብ ቆሞ አየች፣ የጦር መኮንኖችና መለከት ነፊዎችም በንጉሡ አጠገቡ ነበሩ፤ የምድሪቱ ሕዝብ ሁሉ ይደሰቱ፣ መለከትም ይነፉ ነበር፤ መዘምራንም በዜማ ዕቃ ታጅበው የበዓሉን ዝማሬ ይመሩ ነበር፤ ጎቶልያም ልብሷን ቀድዳ፣ “ይህ ዐመፅ ነው! ይህ ዐመፅ ነው!” ብላ ጮኸች።

14ካህኑ ዮዳሄም የወታደር አዛዥ ወደ ሆኑት ወደ መቶ አለቆቹ፣ “በሰልፉ መካከል አውጥታችሁ አምጧት23፥14 ወይም ከቅጥሩ ውስጥ አውጥታችሁ አምጧት፤ የሚከተላት ካለም በሰይፍ ግደሉት” ሲል ላከባቸው። ካህኑም፣ “በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ አትግደሏት” ብሎ ነበርና። 15እርሷም በቤተ መንግሥቱ ግቢ የፈረስ መግቢያ በር ወደ ተባለው ቦታ እንደ ደረሰች ያዟት፤ በዚያም ገደሏት።

16ዮዳሄም ራሱ፣ ሕዝቡና ንጉሡ የእግዚአብሔር ሕዝብ እንደሚሆኑ ቃል ኪዳን ገባ23፥16 ወይም በእግዚአብሔር በሕዝቡና በንጉሡ መካከል የተደረገው ቃል ኪዳን (2ነገ 11፥17)17ከዚህ በኋላ ሕዝቡ በሙሉ ሄዶ የበኣልን ቤተ ጣዖት አፈረሰው፤ መሠዊያዎቹንና ጣዖታቱን አደቀቀ፤ የበኣልን ካህን ማታንንም በመሠዊያዎቹ ፊት ለፊት ገደሉት። 18ዮዳሄ በሙሴ ሕግ እንደ ተጻፈውና ዳዊትም እንዳዘዘው፣ በደስታና በመዝሙር የሚቃጠለውን የእግዚአብሔርን መሥዋዕት እንዲያቀርቡ ዳዊት ለመደባቸው ካህናትና ሌዋውያን የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ኀላፊነት ሰጣቸው። 19እንዲሁም በማንኛውም ነገር የረከሰ ሰው እንዳይገባ፣ በቤተ መቅደሱ ቅጥር በሮች ላይ ጠባቆች አቆመ። 20የመቶ አለቆቹን፣ መኳንንቱን፣ የሕዝቡን ገዦችና የአገሩን ሕዝብ ሁሉ ይዞ ንጉሡን ከላይ ከቤተ መቅደሱ ወደ ታች አመጣው። በላይኛውም መግቢያ በኩል ወደ ቤተ መንግሥቱ ገብተው ንጉሡን በመንግሥቱ ዙፋን ላይ አስቀመጡት። 21መላውም የአገሩ ሕዝብ ተደሰተ፤ ጎቶልያ ስለ ተገደለችም ከተማዪቱ ሰላም አግኝታ ነበር።

New International Reader’s Version

2 Chronicles 23:1-21

1When Joash was seven years old, Jehoiada showed how strong he was. He made a covenant with the commanders of groups of 100 men. The commanders were Azariah son of Jeroham, Ishmael son of Jehohanan, Azariah son of Obed, Maaseiah son of Adaiah, and Elishaphat son of Zikri. 2They went all through Judah. They gathered together the Levites and the leaders of Israelite families from all the towns. They came to Jerusalem. 3The whole community made a covenant with the new king at God’s temple.

Jehoiada said to them, “Ahaziah’s son will rule over Judah. That’s what the Lord promised concerning the family line of David. 4Here’s what I want you to do. A third of you priests and Levites who are going on duty on the Sabbath day must guard the doors. 5A third of you must guard the royal palace. And a third of you must guard the Foundation Gate. All the other men must guard the courtyards of the Lord’s temple. 6Don’t let anyone enter the temple except the priests and Levites who are on duty. They can enter because they are set apart to the Lord. But all the other men must obey the Lord’s command not to enter. 7The Levites must station themselves around the new king. Each man must have his weapon in his hand. Anyone else who enters the temple must be put to death. Stay close to the king no matter where he goes.”

8The Levites did just as Jehoiada the priest ordered. So did all the men of Judah. Each commander got his men. Some of the men were going on duty on the Sabbath day. Others were going off duty. Jehoiada didn’t let any of the groups go. 9Then he gave weapons to the commanders of the groups. He gave them spears, large shields and small shields. The weapons had belonged to King David. They had been in God’s temple. 10Jehoiada stationed all the men around the new king. Each man had his weapon in his hand. They were standing near the altar and the temple. They stood from the south side of the temple to its north side.

11Jehoiada and his sons brought Ahaziah’s son out. They put the crown on him. They gave him a copy of the covenant. And they announced that he was king. They anointed him. Then they shouted, “May the king live a long time!”

12Athaliah heard the noise of the people running and cheering the new king. So she went to them at the Lord’s temple. 13She looked, and there was the king! He was standing next to his pillar at the entrance. The officers and trumpet players were standing beside the king. All the people of the land were filled with joy. They were blowing trumpets. Musicians with their musical instruments were leading the songs of praise. Then Athaliah tore her royal robes. She shouted, “Treason! It’s treason!”

14Jehoiada the priest sent out the commanders of the groups of 100 men. They were in charge of the troops. He said to them, “Bring her away from the temple between the line of guards. Use your swords to kill anyone who follows her.” The priest had said, “Don’t put her to death at the Lord’s temple.” 15So they grabbed her as she reached the entrance of the Horse Gate on the palace grounds. There they put her to death.

16Then Jehoiada made a covenant. He promised that he, the people and the king would be the Lord’s people. 17All the people went to Baal’s temple. They tore it down. They smashed the altars and the statues of gods. They killed Mattan in front of the altars. He was the priest of Baal.

18Then Jehoiada put the priests, who were Levites, in charge of the Lord’s temple. David had given them their duties in the temple. He had appointed them to sacrifice burnt offerings to the Lord. He wanted them to do it in keeping with what was written in the Law of Moses. David wanted them to sing and be full of joy. 19Jehoiada stationed guards at the gates of the Lord’s temple. No one who was “unclean” in any way could enter.

20Jehoiada took with him the commanders of hundreds, the nobles, the rulers of the people, and all the people of the land. He brought the new king down from the Lord’s temple. They went into the palace through the Upper Gate. Then they seated the king on the royal throne. 21All the people of the land were filled with joy. And the city was calm. That’s because Athaliah had been killed by a sword.