2 ዜና መዋዕል 22 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

2 ዜና መዋዕል 22:1-12

የይሁዳ ንጉሥ አካዝያስ

22፥1-6 ተጓ ምብ – 2ነገ 8፥25-29

22፥7-9 ተጓ ምብ – 2ነገ 9፥21-29

1ከዐረቦች ጋር ወደ ሰፈር የመጡት ወራሪዎች፣ ታላላቅ ወንድሞቹን ሁሉ ገድለዋቸው ስለ ነበር፣ የኢየሩሳሌም ሕዝብ የኢዮሆራምን የመጨረሻ ልጅ አካዝያስን በአባቱ ምትክ አነገሡት። ስለዚህ የይሁዳ ንጉሥ የኢዮሆራም ልጅ አካዝያስ መግዛት ጀመረ። 2አካዝያስ በነገሠ ጊዜ ዕድሜው ሃያ ሁለት22፥2 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናትና የሱርስቱ ቅጆች (እንዲሁም 2ነገ 8፥26 ይመ) ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ዕብራይስጡ ግን አርባ አራት ይላል። ዓመት ነበር፤ በኢየሩሳሌም ተቀምጦም አንድ ዓመት ገዛ። እናቱም ጎቶልያ የተባለች የዘንበሪ የልጅ ልጅ ነበረች።

3እናቱ ክፋትን እንዲያደርግ ትመክረው ስለ ነበር፣ እርሱም በአክዓብ ቤት መንገድ ሄደ። 4ከአባቱ ሞት በኋላ የአክዓብ ቤት አማካሪዎቹ በመሆን ወደ ጥፋት ስለ መሩት፣ የአክዓብ ቤት እንዳደረገው ሁሉ እርሱም በእግዚአብሔር ፊት ክፉ ነገር አደረገ። 5እንዲሁም የእስራኤል ንጉሥ የአክዓብ ልጅ ኢዮራም የሶርያን ንጉሥ አዛሄልን ለመውጋት ወደ ሬማት ገለዓድ በሄደ ጊዜ፣ የእነዚህኑ ሰዎች ምክር ተከትሎ ከኢዮራም ጋር አብሮት ሄደ፣ ሶርያውያንም ኢዮራምን አቈሰሉት።

6ስለዚህ ከሶርያ ንጉሥ ከአዛሄል ጋር ባደረገው ጦርነት ሬማት22፥6 ጥቂት የዕብራይስጥ ቅጆች የሰብዓ ሊቃናት፣ የቩልጌትና የሱርስቱ ትርጕም (2ነገ 8፥29) ከዚህ ጋር ይስማማሉ አብዛኞቹ የዕብራይስጥ ቅጆች ግን፣ አዛርያ ይላሉ። ላይ ከደረሰበት ቍስል ለመዳን ወደ ኢይዝራኤል ተመለሰ።

የአክዓብ ልጅ ኢዮራም በመቍሰሉም የይሁዳ ንጉሥ የኢዮሆራም ልጅ አካዝያስ ሊጠይቀው ወደ ኢይዝራኤል ወረደ።

7አካዝያስ ኢዮራምን ለመጠየቅ መሄዱን፣ እግዚአብሔር ለአካዝያስ መውደቅ ምክንያት አደረገው፤ አካዝያስ እንደ ደረሰም የናሜሲን ልጅ ኢዩን ለመቀበል ከኢዮራም ጋር ወጣ፤ ኢዩም የአክዓብን ቤት እንዲያጠፋ እግዚአብሔር የቀባው ሰው ነበር። 8ኢዩ በአክዓብ ቤት ላይ ፍርድ በሚፈጽምበት ጊዜ፣ አካዝያስን ያጅቡ የነበሩትን የይሁዳን መሳፍንትና የዘመዶቹን ወንዶች ልጆች አግኝቶ ገደላቸው። 9ከዚያም አካዝያስን ለመፈለግ ሄደ፤ የእርሱም ሰዎች አካዝያስን በሰማርያ ከተደበቀበት አግኝተው ያዙት፤ ወደ ኢዩም አምጥተው ገደሉት። “እግዚአብሔርን በፍጹም ልቡ የፈለገው የኢዮሣፍጥ ልጅ ነው” በማለት ቀበሩት። ስለዚህ ከአካዝያስ ቤት የመንግሥቱን ሥልጣን ይይዝ ዘንድ የሚችል ሰው አልነበረም።

ጎቶልያና ኢዮአስ

22፥10–23፥21 ተጓ ምብ – 2ነገ 11፥1-21

10የአካዝያስ እናት ጎቶልያ ልጇ መሞቱን ባየች ጊዜ፣ የይሁዳን ንጉሣውያን ቤተ ሰብ በሙሉ አጠፋች፤ 11የንጉሥ ኢዮሆራም ልጅ ዮሳቤት ግን፣ ከሚገደሉት መሳፍንት መካከል ኢዮአስን ደብቃ ወሰደችው፣ ከሞግዚቱም ጋር በእልፍኝ ሸሸገችው። የኢዮሆራም ልጅ የካህኑ የዮዳሄ ሚስት ዮሳቤት፣ የአካዝያስ እኅት በመሆኗ፣ ሕፃኑን የደበቀችው ጎቶልያ እንዳትገድለው ነበር። 12እርሱም ጎቶልያ ምድሪቱን በገዛችበት ጊዜ ሁሉ፣ በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ተደብቆ ስድስት ዓመት አብሯቸው ኖረ።

Thai New Contemporary Bible

2พงศาวดาร 22:1-12

กษัตริย์อาหัสยาห์แห่งยูดาห์

(2พกษ.8:25-29; 9:21-29)

1ชาวเยรูซาเล็มตั้งอาหัสยาห์โอรสองค์สุดท้องของเยโฮรัมขึ้นครองราชย์เพราะกองโจรที่เข้ามาในค่ายกับชาวอาหรับได้สังหารโอรสผู้พี่องค์อื่นๆ หมดแล้ว อาหัสยาห์โอรสกษัตริย์เยโฮรัมแห่งยูดาห์จึงเริ่มครองราชย์

2อาหัสยาห์ทรงมีพระชนมายุ 22 พรรษา22:2 ภาษาฮีบรูว่า42 พรรษา(ดู2พกษ.8:26)เมื่อขึ้นเป็นกษัตริย์ และทรงครองราชย์อยู่เพียงปีเดียวในกรุงเยรูซาเล็ม ราชมารดาคืออาธาลิยาห์หลานสาวของอมรี

3อาหัสยาห์ก็เช่นกัน พระองค์ทรงดำเนินตามอย่างราชวงศ์อาหับ เพราะราชมารดาสนับสนุนให้ทำผิด 4และทรงทำสิ่งที่ชั่วในสายพระเนตรขององค์พระผู้เป็นเจ้าตามอย่างราชวงศ์อาหับ เพราะหลังจากราชบิดาสิ้นพระชนม์ ทรงยึดราชวงศ์อาหับเป็นที่ปรึกษาซึ่งนำพระองค์ไปสู่หายนะ 5พระองค์ทรงทำตามคำแนะนำของพวกเขาโดยเข้าร่วมกับโยรัม22:5 ภาษาฮีบรูว่าเยโฮรัมเป็นอีกรูปหนึ่งของโยรัมเช่นเดียวกับข้อ 6 และ 7โอรสของกษัตริย์อาหับแห่งอิสราเอล ไปรบกับกษัตริย์ฮาซาเอลแห่งอารัมที่เมืองราโมทกิเลอาด โยรัมได้รับบาดเจ็บด้วยน้ำมือของชาวอารัม 6พระองค์จึงเสด็จกลับมาพักฟื้นที่ยิสเรเอลเพราะบาดเจ็บจากสงครามกับกษัตริย์ฮาซาเอลแห่งอารัมที่ราโมท22:6 ภาษาฮีบรูว่ารามาห์ซึ่งเป็นอีกรูปหนึ่งของราโมท

แล้วอาหัสยาห์22:6 สำเนาต้นฉบับภาษาฮีบรูส่วนใหญ่ว่าอาซาริยาห์(ดู2พกษ.8:29)โอรสกษัตริย์เยโฮรัมแห่งยูดาห์ก็เสด็จลงไปเยี่ยมพระอาการของโยรัมโอรสของอาหับที่ยิสเรเอล

7ในการเยี่ยมครั้งนี้พระเจ้าทรงนำจุดจบมาสู่อาหัสยาห์ เมื่ออาหัสยาห์มาถึง พระองค์กับโยรัมก็ออกไปพบเยฮูบุตรนิมชี ซึ่งองค์พระผู้เป็นเจ้าได้ทรงเจิมตั้งให้เป็นผู้ทำลายล้างราชวงศ์อาหับ 8ขณะเยฮูออกกวาดล้างราชวงศ์อาหับ ได้พบกับบรรดาเจ้านายยูดาห์และญาติของอาหัสยาห์ที่รับใช้อาหัสยาห์ เยฮูก็ประหารพวกเขา 9แล้วเยฮูก็ค้นหาอาหัสยาห์ คนของเยฮูพบอาหัสยาห์หลบซ่อนอยู่ในสะมาเรียจึงคุมตัวมาให้เยฮูปลงพระชนม์ พวกเขาฝังพระศพของอาหัสยาห์โดยให้เหตุผลว่า “พระองค์ทรงเป็นลูกหลานของเยโฮชาฟัทผู้แสวงหาองค์พระผู้เป็นเจ้าอย่างสุดใจ” ไม่มีใครในราชวงศ์อาหัสยาห์ที่เข้มแข็งพอจะกู้อาณาจักรให้เป็นปึกแผ่นเช่นเดิมได้เลย

พระนางอาธาลิยาห์กับโยอาช

(2พกษ.11:1-21)

10เมื่อพระนางอาธาลิยาห์ราชมารดาของอาหัสยาห์เห็นว่าโอรสสิ้นพระชนม์แล้ว ก็สังหารเชื้อพระวงศ์ของยูดาห์ทั้งหมด 11แต่เยโฮเชบา22:11 ภาษาฮีบรูว่าเยโฮชาเบอาทเป็นอีกรูปหนึ่งของเยโฮเชบา ธิดาของกษัตริย์เยโฮรัม น้องสาวของอาหัสยาห์และเป็นภรรยาของปุโรหิตเยโฮยาดา นำตัวโยอาชโอรสของอาหัสยาห์มาจากบรรดาเจ้านายที่กำลังจะถูกฆ่า ไปซ่อนไว้ในห้องนอนพร้อมกับพี่เลี้ยง เด็กนั้นจึงพ้นจากมือของพระนางอาธาลิยาห์ 12โยอาชซ่อนพระองค์อยู่กับพวกเขาในพระวิหารของพระเจ้าตลอดหกปีที่พระนางอาธาลิยาห์ครองราชย์