2 ዜና መዋዕል 22 – NASV & BPH

New Amharic Standard Version

2 ዜና መዋዕል 22:1-12

የይሁዳ ንጉሥ አካዝያስ

22፥1-6 ተጓ ምብ – 2ነገ 8፥25-29

22፥7-9 ተጓ ምብ – 2ነገ 9፥21-29

1ከዐረቦች ጋር ወደ ሰፈር የመጡት ወራሪዎች፣ ታላላቅ ወንድሞቹን ሁሉ ገድለዋቸው ስለ ነበር፣ የኢየሩሳሌም ሕዝብ የኢዮሆራምን የመጨረሻ ልጅ አካዝያስን በአባቱ ምትክ አነገሡት። ስለዚህ የይሁዳ ንጉሥ የኢዮሆራም ልጅ አካዝያስ መግዛት ጀመረ። 2አካዝያስ በነገሠ ጊዜ ዕድሜው ሃያ ሁለት22፥2 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናትና የሱርስቱ ቅጆች (እንዲሁም 2ነገ 8፥26 ይመ) ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ዕብራይስጡ ግን አርባ አራት ይላል። ዓመት ነበር፤ በኢየሩሳሌም ተቀምጦም አንድ ዓመት ገዛ። እናቱም ጎቶልያ የተባለች የዘንበሪ የልጅ ልጅ ነበረች።

3እናቱ ክፋትን እንዲያደርግ ትመክረው ስለ ነበር፣ እርሱም በአክዓብ ቤት መንገድ ሄደ። 4ከአባቱ ሞት በኋላ የአክዓብ ቤት አማካሪዎቹ በመሆን ወደ ጥፋት ስለ መሩት፣ የአክዓብ ቤት እንዳደረገው ሁሉ እርሱም በእግዚአብሔር ፊት ክፉ ነገር አደረገ። 5እንዲሁም የእስራኤል ንጉሥ የአክዓብ ልጅ ኢዮራም የሶርያን ንጉሥ አዛሄልን ለመውጋት ወደ ሬማት ገለዓድ በሄደ ጊዜ፣ የእነዚህኑ ሰዎች ምክር ተከትሎ ከኢዮራም ጋር አብሮት ሄደ፣ ሶርያውያንም ኢዮራምን አቈሰሉት።

6ስለዚህ ከሶርያ ንጉሥ ከአዛሄል ጋር ባደረገው ጦርነት ሬማት22፥6 ጥቂት የዕብራይስጥ ቅጆች የሰብዓ ሊቃናት፣ የቩልጌትና የሱርስቱ ትርጕም (2ነገ 8፥29) ከዚህ ጋር ይስማማሉ አብዛኞቹ የዕብራይስጥ ቅጆች ግን፣ አዛርያ ይላሉ። ላይ ከደረሰበት ቍስል ለመዳን ወደ ኢይዝራኤል ተመለሰ።

የአክዓብ ልጅ ኢዮራም በመቍሰሉም የይሁዳ ንጉሥ የኢዮሆራም ልጅ አካዝያስ ሊጠይቀው ወደ ኢይዝራኤል ወረደ።

7አካዝያስ ኢዮራምን ለመጠየቅ መሄዱን፣ እግዚአብሔር ለአካዝያስ መውደቅ ምክንያት አደረገው፤ አካዝያስ እንደ ደረሰም የናሜሲን ልጅ ኢዩን ለመቀበል ከኢዮራም ጋር ወጣ፤ ኢዩም የአክዓብን ቤት እንዲያጠፋ እግዚአብሔር የቀባው ሰው ነበር። 8ኢዩ በአክዓብ ቤት ላይ ፍርድ በሚፈጽምበት ጊዜ፣ አካዝያስን ያጅቡ የነበሩትን የይሁዳን መሳፍንትና የዘመዶቹን ወንዶች ልጆች አግኝቶ ገደላቸው። 9ከዚያም አካዝያስን ለመፈለግ ሄደ፤ የእርሱም ሰዎች አካዝያስን በሰማርያ ከተደበቀበት አግኝተው ያዙት፤ ወደ ኢዩም አምጥተው ገደሉት። “እግዚአብሔርን በፍጹም ልቡ የፈለገው የኢዮሣፍጥ ልጅ ነው” በማለት ቀበሩት። ስለዚህ ከአካዝያስ ቤት የመንግሥቱን ሥልጣን ይይዝ ዘንድ የሚችል ሰው አልነበረም።

ጎቶልያና ኢዮአስ

22፥10–23፥21 ተጓ ምብ – 2ነገ 11፥1-21

10የአካዝያስ እናት ጎቶልያ ልጇ መሞቱን ባየች ጊዜ፣ የይሁዳን ንጉሣውያን ቤተ ሰብ በሙሉ አጠፋች፤ 11የንጉሥ ኢዮሆራም ልጅ ዮሳቤት ግን፣ ከሚገደሉት መሳፍንት መካከል ኢዮአስን ደብቃ ወሰደችው፣ ከሞግዚቱም ጋር በእልፍኝ ሸሸገችው። የኢዮሆራም ልጅ የካህኑ የዮዳሄ ሚስት ዮሳቤት፣ የአካዝያስ እኅት በመሆኗ፣ ሕፃኑን የደበቀችው ጎቶልያ እንዳትገድለው ነበር። 12እርሱም ጎቶልያ ምድሪቱን በገዛችበት ጊዜ ሁሉ፣ በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ተደብቆ ስድስት ዓመት አብሯቸው ኖረ።

Bibelen på hverdagsdansk

2. Krønikebog 22:1-12

Kong Ahazja af Juda

2.Kong. 8,25-29; 9,21-29

1Befolkningen i Jerusalem valgte derefter Ahazja, Jorams yngste søn, til konge, eftersom de arabere, der havde gjort indfald i landet, havde gjort det af med Jorams øvrige sønner. 2Ahazja var 2222,2 MT siger 42, men en del gamle oversættelser siger 22, som der også står i 2.Kong. 8,26. år gammel, da han blev konge, og han regerede i Jerusalem i ét år. Hans mor hed Atalja og var kong Omris barnebarn. 3Ahazja var lige så ond en konge som dem fra Ahabs slægt, for hans mor var en dårlig rådgiver for ham. 4Han gjorde, hvad der var ondt i Herrens øjne, som Ahabs slægt altid havde gjort. Han havde nemlig valgt sine rådgivere fra den slægt efter sin fars død, og det blev hans undergang.

5Ahazja fulgte deres råd og indgik forbund med Israels kong Joram, søn af Ahab. Derfor sluttede han sig til Joram i krigen mod kong Hazael af Aram. Aramæerne vandt slaget ved Ramot-Gilead, og Joram blev såret, 6hvorefter han trak sig tilbage til Jizre’el for at blive rask igen. Ahazja tog derfor til Jizre’el for at se til ham, 7og det blev hans undergang, for Gud ønskede at straffe ham. Mens han var på besøg der, tog han med Joram ud for at møde Jehu, søn af Nimshi, som Herren havde udvalgt til at gøre det af med resten af Ahabs slægt.

8Mens Jehu var i gang med denne opgave, traf han nogle af Judas ledende mænd og nogle af Ahazjas slægtninge, som var med i Ahazjas følge. Dem huggede han også ned. 9Derefter fortsatte Jehus mænd jagten på Ahazja, og de fandt ham i byen Samaria. De førte ham straks til Jehu, der slog ham ihjel. Ahazja fik dog en anstændig begravelse, for han var trods alt barnebarn af kong Joshafat, der af hele sit hjerte havde tjent Herren. Ahazjas sønner var helt små, så ingen af dem kunne overtage tronen.

Atalja overtager magten i Juda

2.Kong. 11,1-3

10Dengang Atalja, som var mor til kong Ahazja af Juda, hørte, at hendes søn var død, satte hun sig for at udrydde samtlige medlemmer af den judæiske kongefamilie.

11Men Ahazjas søster, Josheba,22,11 Også kaldet „Joshabat”. fjernede i al hemmelighed Ahazjas yngste søn, Joash, som kun var et spædbarn, fra de øvrige prinser, som skulle dræbes. Det lykkedes Josheba, som var gift med præsten Jojada, at gemme både Joash og hans amme i et soveværelse. 12Drengen blev derefter holdt skjult på tempelområdet i de seks år, Atalja regerede i Juda.