2 ዜና መዋዕል 20 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

2 ዜና መዋዕል 20:1-37

ኢዮሣፍጥ ሞዓብንና አሞንን ድል ማድረጉ

1ከዚህ በኋላ ሞዓባውያንና አሞናውያን ከጥቂት ምዑናውያን20፥1 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ነገር ግን ዕብራይስጡ ምድያማውያን ይላል። ጋር ሆነው ኢዮሣፍጥን ለመውጋት መጡ።

2ሰዎችም መጥተው ኢዮሣፍጥን፣ “ግዙፍ ሰራዊት ሊወጋህ ከሙት20፥2 አንድ የዕብራይስጥ ቅጅ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ ዕብራይስጡ ግን አራም ይላል። ባሕር ወዲያ ካለው ከኤዶም20፥2 ምንም እንኳ የሙት ባሕር መሆኑን ግልጽ ቢሆንም አንዳንድ ቅጆች ሙት የሚለውን ቃል አይጨምሩም። መጥቶብሃል፤ እነሆም፣ ሐሴሶን ታማር በተባለው በዓይንጋዲ ናቸው” አሉት። 3ኢዮሣፍጥም እጅግ ስለ ፈራ እግዚአብሔርን ለመፈለግ ፊቱን አቀና፤ በይሁዳም ሁሉ ጾም ዐወጀ። 4የይሁዳ ሕዝብም የእግዚአብሔርን ርዳታ ይሻ ዘንድ በአንድነት ተሰበሰበ፤ ከይሁዳ ከተሞች ሁሉም እግዚአብሔርን ለመፈለግ መጡ። 5ኢዮሣፍጥም በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ፣ ከአዲሱ አደባባይ ፊት ለፊት በይሁዳና በኢየሩሳሌም ጉባኤ መካከል ቆመ፤ 6እንዲህም አለ፤

“የአባቶቻችን አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ በሰማይ የምትኖር አምላክ አይደለህምን? የምድር ሕዝቦችን መንግሥታት ሁሉ የምትገዛ አንተ ነህ፤ ኀይልና ሥልጣን በእጅህ ነው፤ ሊቋቋምህም የሚችል ማንም የለም። 7አምላካችን ሆይ፤ የዚህችን ምድር ነዋሪዎች ከሕዝብህ ከእስራኤል ፊት አሳድደህ ያስወጣህና ለወዳጅህ ለአብርሃም ዘሮች ለዘላለም የሰጠሃቸው አንተ አይደለህምን? 8እነርሱም ተቀመጡባት፤ ለስምህ መቅደስ ሠሩባት፤ እንዲህም አሉ፤ 9‘የፍርድ ሰይፍም ሆነ የቸነፈር ወይም የራብ መከራ ቢደርስብን፣ ስምህ በተጠራበት በዚህ ቤተ መቅደስ ፊት ለፊት፣ በፊትህ ቆመን በጭንቀታችን ወደ አንተ እንጮሃለን፤ አንተም ትሰማናለህ፤ ታድነናለህም።’

10“እስራኤል ከግብፅ በወጡ ጊዜ፣ ግዛታቸውን እንዳይወርሩባቸው በማድረግህ ከእነርሱ ተመልሰው ሳያጠፏቸው የቀሩት የአሞን፣ የሞዓብና የሴይር ተራራ ሰዎች እነሆ እዚህ አሉ። 11እነሆ፣ አንተ ርስት አድርገህ ከሰጠኸን ምድር እኛን በማፈናቀል ወሮታ ሊመልሱልን መጥተዋል። 12አምላካችን ሆይ፤ አንተ አትፈርድባቸውምን? የመጣብንን ይህን ታላቅ ሰራዊት እንቋቋም ዘንድ ዐቅም የለንምና የምናደርገውን አናውቅም፤ ነገር ግን ዐይኖቻችን ወዳንተ ናቸው።”

13የይሁዳ ሰዎች ሁሉ ከሚስቶቻቸው፣ ከልጆቻቸውና ከሕፃኖቻቸው ጋር በእግዚአብሔር ፊት ቆመው ነበር።

14በዚህ ጊዜ የአሳፍ ዘር በሆነው በሌዋዊው በዘካርያስ ልጅ፣ በየሕዚኤል ላይ የእግዚአብሔር መንፈስ መጣ። ዘካርያስም የበናያስ ልጅ ሲሆን፣ በናያስም የማታን ልጅ የሆነው የይዒኤል ልጅ ነው።

15እርሱም እንዲህ አለ፤ “ንጉሥ ኢዮሣፍጥ፣ እናንተም በይሁዳና በኢየሩሳሌም የምትኖሩ ሁሉ አድምጡ! እግዚአብሔር እንዲህ ይላችኋል፤ ‘ውጊያው የእግዚአብሔር እንጂ የእናንተ አይደለምና፣ ከዚህ ታላቅ ሰራዊት የተነሣ አትፍሩ፣ አትደንግጡ፣ 16ነገ በእነርሱ ላይ ውረዱ፤ እነርሱ በጺጽ መተላለፊያ ሽቅብ ይወጣሉ፣ እናንተም በይሩኤል ምድረ በዳ ውስጥ በሸለቆው መጨረሻ ላይ ታገኟቸዋላችሁ። 17ይህን ጦርነት የምትዋጉት እናንተ አይደላችሁም፤ ይሁዳና ኢየሩሳሌም ሆይ፤ ቦታ ቦታችሁን ያዙ፤ ጸንታችሁ ቁሙ፤ እግዚአብሔር የሚሰጣችሁንም ማዳን እዩ። አትፍሩ፤ አትደንግጡም፤ ነገውኑ ውጡና ግጠሟቸው፤ እግዚአብሔርም ከእናንተ ጋር ይሆናል።’ ”

18ኢዮሣፍጥ በግንባሩ ወደ መሬት ተደፋ፤ የይሁዳና የኢየሩሳሌምም ሕዝብ ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት ወደቁ፤ ሰገዱም። 19ከቀዓትና ከቆሬ ወገኖች ጥቂት ሌዋውያንም ቆመው፣ እጅግ ከፍ ባለ ድምፅ የእስራኤልን አምላክ እግዚአብሔርን አመሰገኑ።

20በማግስቱም ጧት በማለዳ ተነሥተው ወደ ቴቁሔ ምድረ በዳ ሄዱ። መንገድ እንደ ጀመሩም ኢዮሣፍጥ ቆሞ፣ “ይሁዳና የኢየሩሳሌም ሕዝብ ሆይ፣ አድምጡኝ! በአምላካችሁ በእግዚአብሔር እመኑ፤ ትጸኑማላችሁ። በነቢያቱም እመኑ፤ ይሳካላችሁማል” አላቸው። 21ከሕዝቡም ጋር ከተመካከረ በኋላ ከሰራዊቱ ፊት ቀድመው በመሄድ፣

እግዚአብሔርን አመስግኑ፣

ፍቅሩ ለዘላለም ጸንቶ ይኖራልና”

እያሉ ለእግዚአብሔር የሚዘምሩና ስለ ቅድስናውም ክብር የሚያወድሱ ሰዎችን መደበ።

22መዘመርና ማወደስ እንደ ጀመሩም፣ እግዚአብሔር ይሁዳን በወረሩት በአሞን፣ በሞዓብና በሴይር ተራራ ሰዎች ላይ ድብቅ ጦር አመጣባቸው፤ ተሸነፉም። 23የአሞንና የሞዓብ ሰዎችም የሴይርን ተራራ ሰዎች ለማጥፋትና ለመደምሰስ ተነሡባቸው። ከሴይር የመጡትን ሰዎች ካጠፉ በኋላም፣ እርስ በርስ ተጠፋፉ።

24የይሁዳ ሰዎች ምድረ በዳውን ቍልቍል ወደሚያሳየው ቦታ መጥተው ግዙፉን ሰራዊት ሲመለከቱ፣ መሬቱ ሬሳ በሬሳ ሆኖ አዩ፤ አንድም ሰው አላመለጠም። 25ኢዮሣፍጥና ሰዎቹም ምርኳቸውን ለማጋዝ ሄዱ፤ በዚያም መካከል እጅግ ብዙ መሣሪያና ልብስ፣20፥25 አንዳንድ የዕብራይስጥና የቩልጌት ቅጆች ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ነገር ግን አብዛኞቹ የዕብራይስጥ ቅጆች ሬሳ ይላል። ሊሸከሙ ከሚችሉትም በላይ ውድ ዕቃዎችን አገኙ። ምርኮውም ከመብዛቱ የተነሣ ለመሰብሰብ ሦስት ቀን ፈጀ። 26በአራተኛውም ቀን እግዚአብሔርን ባመሰገኑበት በበረከት20፥26 በዕብራይስጡ፣ በራካ ማለት በረከት ማለት ነው። ሸለቆ ተሰበሰቡ፤ ያም ስፍራ እስከ ዛሬ ድረስ የበረከት ሸለቆ ተብሎ የተጠራው ከዚህ የተነሣ ነው።

27እግዚአብሔር በጠላቶቻቸው ላይ እንዲደሰቱ ስላደረጋቸው፣ የይሁዳና የኢየሩሳሌም ሰዎች ሁሉ በኢዮሣፍጥ እየተመሩ፣ በታላቅ ደስታ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ። 28ወደ ኢየሩሳሌም ከተማ እንደ ገቡም በበገና፣ በመሰንቆና በመለከት ድምፅ ታጅበው ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ አመሩ።

29እግዚአብሔር የእስራኤልን ጠላቶች እንዴት እንደ ተዋጋቸው በሰሙ መንግሥታት ሁሉ ላይ ከእግዚአብሔር ዘንድ ፍርሀት ወደቀባቸው።

30አምላኩ በየአቅጣጫው ዕረፍት ስለ ሰጠው፣ የኢዮሣፍጥ መንግሥት ሰላም አግኝቶ ነበር።

የኢዮሣፍጥ ዘመነ መንግሥት ፍጻሜ

20፥31–21፥1 ተጓ ምብ – 1ነገ 22፥41-50

31ኢዮሣፍጥ በይሁዳ ላይ ነገሠ። መንገሥ በጀመረ ጊዜም ዕድሜው ሠላሳ አምስት ዓመት ሲሆን፣ በኢየሩሳሌም ተቀሞጦ ሃያ አምስት ዓመት ገዛ። እናቱም የሺልሒ ልጅ ዓዙባ ነበረች። 32እርሱም በአባቱ በአሳ መንገድ ሄደ፤ ከዚያም ፈቀቅ አላለም፤ በእግዚአብሔርም ፊት መልካም የሆነውን ነገር አደረገ። 33ያም ሆኖ ግን ማምለኪያ ኰረብታዎች ሙሉ በሙሉ አልተወገዱም፤ ሕዝቡም ገና ልቡን በአባቶቹ አምላክ ላይ አልጣለም ነበር።

34በኢዮሣፍጥ ዘመነ መንግሥት ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ የተከናወኑት ሌሎች ተግባራት የአናኒ ልጅ ኢዩ በዘገበው የእስራኤል ነገሥታት የታሪክ መጽሐፍ ተመዝግቧል።

35ከዚህ በኋላ የይሁዳ ንጉሥ ኢዮሣፍጥ ሥራው እጅግ ክፉ ከሆነው ከእስራኤል ንጉሥ ከአካዝያስ ጋር የስምምነት ውል አደረገ፤ 36የንግድ መርከብ20፥36 ዕብራይስጡ፣ ወደ ተርሴስ ሊሄዱ የሚችሉ መርከቦች ይላል። ለመሥራትም ተስማሙ፤ መርከቦቹንም በዔጽዮንጋብር አሠሩ። 37የመሪሳ ሰው የሆነው የዶዳያ ልጅ አልዓዛር በኢዮሣፍጥ ላይ፣ “ከአካዝያስ ጋር የስምምነት ውል ስለ አደረግህ፣ እግዚአብሔር ሥራህን ያፈርሰዋል” ሲል ትንቢት ተናገረበት፤ መርከቦቹም ተሰበሩ፤ ለንግዱም ሥራ መንቀሳቀስ አልቻሉም።20፥37 ዕብራይስጡ፣ ወደ ተርሴስ መሄድ አልቻሉም ይላል።

Swedish Contemporary Bible

2 Krönikeboken 20:1-37

Joshafat besegrar Moab och Ammon

1Sedan kom moabiterna och ammoniterna och en del av meuniterna för att strida mot Joshafat. 2Joshafat fick följande rapport: ”En enorm armé marscherar mot dig från landet på andra sidan Döda havet, från Edom. Den befinner sig redan vid Haseson Tamar, dvs. En-Gedi.”

3Joshafat blev rädd och bestämde sig för att rådfråga Herren. Han utlyste en fasta i hela Juda. 4Folket från Juda samlades för att söka hjälp hos Herren, ja, de kom från alla städer i Juda för att söka Herrens hjälp. 5Joshafat ställde sig mitt ibland dem, där de var samlade från Juda och Jerusalem i Herrens hus, framför den nya förgården. 6Han sa:

Herre, våra fäders Gud, är inte du Gud i himlen, härskaren över alla folkens riken? I din hand är makt och styrka, och ingen kan stå emot dig. 7Var det inte du, vår Gud, som drev ut invånarna här i landet för ditt folk Israel? Gav inte du det här landet åt din vän Abrahams ättlingar för evigt? 8De bosatte sig där och byggde en helgedom åt ditt namn och sa: 9’Om olycka, krig, pest eller hungersnöd drabbar oss, kan vi stå här framför detta tempel och inför dig, vars namn templet bär, och ropa till dig i vår förtvivlan. Då ska du höra oss och rädda oss.’

10Se nu, folk från Ammon, Moab och Seirs bergsbygd, genom vilkas land du inte lät israeliterna gå när de kom från Egypten, så de gick runt och utrotade dem inte, 11se nu hur de lönar oss! De har kommit för att driva ut oss ur den egendom som du har gett oss. 12O vår Gud, tänker du inte döma dem? Vi står maktlösa mot denna väldiga armé som har kommit emot oss. Vi vet inte vad vi ska göra, men vi har våra ögon riktade på dig.”

13Alla judéer stod där inför Herren med hela sina familjer, sina hustrur och barn. 14Då kom Herrens Ande över Jachasiel, son till Sakarja, son till Benaja, son till Jeiel, son till leviten Mattanja, en ättling till Asaf, där han stod mitt i församlingen.

15”Hör på mig, allt folk i Juda och ni som bor i Jerusalem och du, kung Joshafat!” sa han. ”Så säger Herren till er: ’Var inte rädda och bli inte förskräckta över denna väldiga armé! Striden är inte er utan Guds. 16Gå till anfall mot dem i morgon! De är på väg upp vid Sisbranten, och ni kommer att möta dem vid slutet av bäckravinen invid Jeruels öken. 17Men det är inte ni som ska strida. Inta era ställningar och stå stilla och se hur Herren räddar er, Juda och Jerusalem! Var inte rädda och missmodiga! Gå dit ut i morgon och möt dem, för Herren är med er!’ ”

18Då föll kung Joshafat ner på marken med ansiktet mot jorden, och allt folk i Juda och Jerusalem kastade sig ner och tillbad Herren. 19Sedan reste sig leviterna av Kehats och Korachs släkter upp och prisade och tackade Herren, Israels Gud, med hög röst.

20Tidigt följande morgon drog de ut i Tekoas öken. Inför uppbrottet steg Joshafat fram och talade till dem: ”Lyssna här till mig, Juda och ni som bor i Jerusalem! Tro på Herren, er Gud, så ska ni bestå! Tro på hans profeter, så ska det gå er väl.”

21Efter att ha rådgjort med folket, utsåg han sångare som i helig skrud skulle prisa Herren, medan de drog ut framför armén och sjunga:

”Tacka Herren,

för hans nåd varar för evigt.”

22När de började sjunga och lovprisa, lät Herren ett angrepp komma bakifrån på folket från Ammon, Moab och Seirs bergsbygd, som dragit ut mot Juda, och de blev slagna. 23Ammoniterna och moabiterna vände sig mot män från Seirs bergsbygd för att förinta dem och utplåna dem allesammans, och när de gjort slut på dem, hjälptes de åt med att förgöra varandra.

24När judéerna kom fram till det vakttorn som vette mot öknen och blickade mot den stora armén, såg de bara döda kroppar ligga på marken; inte en enda hade undkommit.

25Joshafat och hans folk gick sedan ut för att ta byte, och de fann där mängder av gods, kläder20:25 Enligt den masoretiska texten döda kroppar. Översättningen följer här andra handskrifter och bl.a. Vulgatas översättning. och värdefulla föremål, mer än de kunde bära. Det var så mycket att det tog dem tre dagar att få med sig allt. 26Den fjärde dagen samlades de i Lovsångsdalen för att prisa Herren. Därför heter platsen än idag Lovsångsdalen.

27Sedan återvände alla män från Juda till Jerusalem, med Joshafat i spetsen, glada, eftersom Herren gett dem glädje över deras fiender. 28De kom till Jerusalem med harpor, lyror och trumpeter och gick fram till Herrens hus.

29Fruktan för Gud kom över alla riken när de hörde att Herren själv hade stridit mot Israels fiender. 30Och nu blev det lugn och ro i Joshafats rike, för Gud hade gett honom fred på alla sidor.

Joshafats regeringstid

(1 Kung 22:41-50)

31Joshafat var så kung över Juda. Han var trettiofem år gammal när han blev kung och regerade tjugofem år i Jerusalem. Hans mor var Asuva, dotter till Shilchi. 32Joshafat följde sin far Asa utan att vika av från den vägen och gjorde det som var rätt inför Herren. 33Dock avskaffade han inte offerplatserna, och folket hade inte vänt sina hjärtan till sina fäders Gud. 34Joshafats historia i övrigt, från början till slut, är nedtecknad i Jehus, Hananis sons, krönika, som ingår i boken om Israels kungar.

35Senare ingick Juda kung Joshafat en allians med Achasja, kungen i Israel, som gjorde mycket ont. 36Joshafat kom överens med honom att bygga fartyg som skulle segla till Tarshish. Dessa byggdes i Esjon-Gever. 37Då profeterade Elieser, Dodias son från Maresha, mot Joshafat och sa till honom: ”Eftersom du har allierat dig med Achasja, ska Herren låta det du gjort bli förstört.” Fartygen råkade ut för missöden och kunde aldrig segla till Tarshish.