2 ዜና መዋዕል 20 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

2 ዜና መዋዕል 20:1-37

ኢዮሣፍጥ ሞዓብንና አሞንን ድል ማድረጉ

1ከዚህ በኋላ ሞዓባውያንና አሞናውያን ከጥቂት ምዑናውያን20፥1 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ነገር ግን ዕብራይስጡ ምድያማውያን ይላል። ጋር ሆነው ኢዮሣፍጥን ለመውጋት መጡ።

2ሰዎችም መጥተው ኢዮሣፍጥን፣ “ግዙፍ ሰራዊት ሊወጋህ ከሙት20፥2 አንድ የዕብራይስጥ ቅጅ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ ዕብራይስጡ ግን አራም ይላል። ባሕር ወዲያ ካለው ከኤዶም20፥2 ምንም እንኳ የሙት ባሕር መሆኑን ግልጽ ቢሆንም አንዳንድ ቅጆች ሙት የሚለውን ቃል አይጨምሩም። መጥቶብሃል፤ እነሆም፣ ሐሴሶን ታማር በተባለው በዓይንጋዲ ናቸው” አሉት። 3ኢዮሣፍጥም እጅግ ስለ ፈራ እግዚአብሔርን ለመፈለግ ፊቱን አቀና፤ በይሁዳም ሁሉ ጾም ዐወጀ። 4የይሁዳ ሕዝብም የእግዚአብሔርን ርዳታ ይሻ ዘንድ በአንድነት ተሰበሰበ፤ ከይሁዳ ከተሞች ሁሉም እግዚአብሔርን ለመፈለግ መጡ። 5ኢዮሣፍጥም በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ፣ ከአዲሱ አደባባይ ፊት ለፊት በይሁዳና በኢየሩሳሌም ጉባኤ መካከል ቆመ፤ 6እንዲህም አለ፤

“የአባቶቻችን አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ በሰማይ የምትኖር አምላክ አይደለህምን? የምድር ሕዝቦችን መንግሥታት ሁሉ የምትገዛ አንተ ነህ፤ ኀይልና ሥልጣን በእጅህ ነው፤ ሊቋቋምህም የሚችል ማንም የለም። 7አምላካችን ሆይ፤ የዚህችን ምድር ነዋሪዎች ከሕዝብህ ከእስራኤል ፊት አሳድደህ ያስወጣህና ለወዳጅህ ለአብርሃም ዘሮች ለዘላለም የሰጠሃቸው አንተ አይደለህምን? 8እነርሱም ተቀመጡባት፤ ለስምህ መቅደስ ሠሩባት፤ እንዲህም አሉ፤ 9‘የፍርድ ሰይፍም ሆነ የቸነፈር ወይም የራብ መከራ ቢደርስብን፣ ስምህ በተጠራበት በዚህ ቤተ መቅደስ ፊት ለፊት፣ በፊትህ ቆመን በጭንቀታችን ወደ አንተ እንጮሃለን፤ አንተም ትሰማናለህ፤ ታድነናለህም።’

10“እስራኤል ከግብፅ በወጡ ጊዜ፣ ግዛታቸውን እንዳይወርሩባቸው በማድረግህ ከእነርሱ ተመልሰው ሳያጠፏቸው የቀሩት የአሞን፣ የሞዓብና የሴይር ተራራ ሰዎች እነሆ እዚህ አሉ። 11እነሆ፣ አንተ ርስት አድርገህ ከሰጠኸን ምድር እኛን በማፈናቀል ወሮታ ሊመልሱልን መጥተዋል። 12አምላካችን ሆይ፤ አንተ አትፈርድባቸውምን? የመጣብንን ይህን ታላቅ ሰራዊት እንቋቋም ዘንድ ዐቅም የለንምና የምናደርገውን አናውቅም፤ ነገር ግን ዐይኖቻችን ወዳንተ ናቸው።”

13የይሁዳ ሰዎች ሁሉ ከሚስቶቻቸው፣ ከልጆቻቸውና ከሕፃኖቻቸው ጋር በእግዚአብሔር ፊት ቆመው ነበር።

14በዚህ ጊዜ የአሳፍ ዘር በሆነው በሌዋዊው በዘካርያስ ልጅ፣ በየሕዚኤል ላይ የእግዚአብሔር መንፈስ መጣ። ዘካርያስም የበናያስ ልጅ ሲሆን፣ በናያስም የማታን ልጅ የሆነው የይዒኤል ልጅ ነው።

15እርሱም እንዲህ አለ፤ “ንጉሥ ኢዮሣፍጥ፣ እናንተም በይሁዳና በኢየሩሳሌም የምትኖሩ ሁሉ አድምጡ! እግዚአብሔር እንዲህ ይላችኋል፤ ‘ውጊያው የእግዚአብሔር እንጂ የእናንተ አይደለምና፣ ከዚህ ታላቅ ሰራዊት የተነሣ አትፍሩ፣ አትደንግጡ፣ 16ነገ በእነርሱ ላይ ውረዱ፤ እነርሱ በጺጽ መተላለፊያ ሽቅብ ይወጣሉ፣ እናንተም በይሩኤል ምድረ በዳ ውስጥ በሸለቆው መጨረሻ ላይ ታገኟቸዋላችሁ። 17ይህን ጦርነት የምትዋጉት እናንተ አይደላችሁም፤ ይሁዳና ኢየሩሳሌም ሆይ፤ ቦታ ቦታችሁን ያዙ፤ ጸንታችሁ ቁሙ፤ እግዚአብሔር የሚሰጣችሁንም ማዳን እዩ። አትፍሩ፤ አትደንግጡም፤ ነገውኑ ውጡና ግጠሟቸው፤ እግዚአብሔርም ከእናንተ ጋር ይሆናል።’ ”

18ኢዮሣፍጥ በግንባሩ ወደ መሬት ተደፋ፤ የይሁዳና የኢየሩሳሌምም ሕዝብ ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት ወደቁ፤ ሰገዱም። 19ከቀዓትና ከቆሬ ወገኖች ጥቂት ሌዋውያንም ቆመው፣ እጅግ ከፍ ባለ ድምፅ የእስራኤልን አምላክ እግዚአብሔርን አመሰገኑ።

20በማግስቱም ጧት በማለዳ ተነሥተው ወደ ቴቁሔ ምድረ በዳ ሄዱ። መንገድ እንደ ጀመሩም ኢዮሣፍጥ ቆሞ፣ “ይሁዳና የኢየሩሳሌም ሕዝብ ሆይ፣ አድምጡኝ! በአምላካችሁ በእግዚአብሔር እመኑ፤ ትጸኑማላችሁ። በነቢያቱም እመኑ፤ ይሳካላችሁማል” አላቸው። 21ከሕዝቡም ጋር ከተመካከረ በኋላ ከሰራዊቱ ፊት ቀድመው በመሄድ፣

እግዚአብሔርን አመስግኑ፣

ፍቅሩ ለዘላለም ጸንቶ ይኖራልና”

እያሉ ለእግዚአብሔር የሚዘምሩና ስለ ቅድስናውም ክብር የሚያወድሱ ሰዎችን መደበ።

22መዘመርና ማወደስ እንደ ጀመሩም፣ እግዚአብሔር ይሁዳን በወረሩት በአሞን፣ በሞዓብና በሴይር ተራራ ሰዎች ላይ ድብቅ ጦር አመጣባቸው፤ ተሸነፉም። 23የአሞንና የሞዓብ ሰዎችም የሴይርን ተራራ ሰዎች ለማጥፋትና ለመደምሰስ ተነሡባቸው። ከሴይር የመጡትን ሰዎች ካጠፉ በኋላም፣ እርስ በርስ ተጠፋፉ።

24የይሁዳ ሰዎች ምድረ በዳውን ቍልቍል ወደሚያሳየው ቦታ መጥተው ግዙፉን ሰራዊት ሲመለከቱ፣ መሬቱ ሬሳ በሬሳ ሆኖ አዩ፤ አንድም ሰው አላመለጠም። 25ኢዮሣፍጥና ሰዎቹም ምርኳቸውን ለማጋዝ ሄዱ፤ በዚያም መካከል እጅግ ብዙ መሣሪያና ልብስ፣20፥25 አንዳንድ የዕብራይስጥና የቩልጌት ቅጆች ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ነገር ግን አብዛኞቹ የዕብራይስጥ ቅጆች ሬሳ ይላል። ሊሸከሙ ከሚችሉትም በላይ ውድ ዕቃዎችን አገኙ። ምርኮውም ከመብዛቱ የተነሣ ለመሰብሰብ ሦስት ቀን ፈጀ። 26በአራተኛውም ቀን እግዚአብሔርን ባመሰገኑበት በበረከት20፥26 በዕብራይስጡ፣ በራካ ማለት በረከት ማለት ነው። ሸለቆ ተሰበሰቡ፤ ያም ስፍራ እስከ ዛሬ ድረስ የበረከት ሸለቆ ተብሎ የተጠራው ከዚህ የተነሣ ነው።

27እግዚአብሔር በጠላቶቻቸው ላይ እንዲደሰቱ ስላደረጋቸው፣ የይሁዳና የኢየሩሳሌም ሰዎች ሁሉ በኢዮሣፍጥ እየተመሩ፣ በታላቅ ደስታ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ። 28ወደ ኢየሩሳሌም ከተማ እንደ ገቡም በበገና፣ በመሰንቆና በመለከት ድምፅ ታጅበው ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ አመሩ።

29እግዚአብሔር የእስራኤልን ጠላቶች እንዴት እንደ ተዋጋቸው በሰሙ መንግሥታት ሁሉ ላይ ከእግዚአብሔር ዘንድ ፍርሀት ወደቀባቸው።

30አምላኩ በየአቅጣጫው ዕረፍት ስለ ሰጠው፣ የኢዮሣፍጥ መንግሥት ሰላም አግኝቶ ነበር።

የኢዮሣፍጥ ዘመነ መንግሥት ፍጻሜ

20፥31–21፥1 ተጓ ምብ – 1ነገ 22፥41-50

31ኢዮሣፍጥ በይሁዳ ላይ ነገሠ። መንገሥ በጀመረ ጊዜም ዕድሜው ሠላሳ አምስት ዓመት ሲሆን፣ በኢየሩሳሌም ተቀሞጦ ሃያ አምስት ዓመት ገዛ። እናቱም የሺልሒ ልጅ ዓዙባ ነበረች። 32እርሱም በአባቱ በአሳ መንገድ ሄደ፤ ከዚያም ፈቀቅ አላለም፤ በእግዚአብሔርም ፊት መልካም የሆነውን ነገር አደረገ። 33ያም ሆኖ ግን ማምለኪያ ኰረብታዎች ሙሉ በሙሉ አልተወገዱም፤ ሕዝቡም ገና ልቡን በአባቶቹ አምላክ ላይ አልጣለም ነበር።

34በኢዮሣፍጥ ዘመነ መንግሥት ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ የተከናወኑት ሌሎች ተግባራት የአናኒ ልጅ ኢዩ በዘገበው የእስራኤል ነገሥታት የታሪክ መጽሐፍ ተመዝግቧል።

35ከዚህ በኋላ የይሁዳ ንጉሥ ኢዮሣፍጥ ሥራው እጅግ ክፉ ከሆነው ከእስራኤል ንጉሥ ከአካዝያስ ጋር የስምምነት ውል አደረገ፤ 36የንግድ መርከብ20፥36 ዕብራይስጡ፣ ወደ ተርሴስ ሊሄዱ የሚችሉ መርከቦች ይላል። ለመሥራትም ተስማሙ፤ መርከቦቹንም በዔጽዮንጋብር አሠሩ። 37የመሪሳ ሰው የሆነው የዶዳያ ልጅ አልዓዛር በኢዮሣፍጥ ላይ፣ “ከአካዝያስ ጋር የስምምነት ውል ስለ አደረግህ፣ እግዚአብሔር ሥራህን ያፈርሰዋል” ሲል ትንቢት ተናገረበት፤ መርከቦቹም ተሰበሩ፤ ለንግዱም ሥራ መንቀሳቀስ አልቻሉም።20፥37 ዕብራይስጡ፣ ወደ ተርሴስ መሄድ አልቻሉም ይላል።

New International Reader’s Version

2 Chronicles 20:1-37

Jehoshaphat Wins the Battle Over Moab and Ammon

1After that, the Moabites, Ammonites and some Meunites went to war against Jehoshaphat.

2Some people came and told him, “A huge army is coming from Edom to fight against you. They have come across the Dead Sea. They are already in Hazezon Tamar.” Hazezon Tamar is also called En Gedi. 3Jehoshaphat was alarmed. So he decided to ask the Lord for advice. He told all the people of Judah to go without eating. 4The people came together to ask the Lord for help. In fact, they came from every town in Judah to pray to him.

5Then Jehoshaphat stood up among the people of Judah and Jerusalem. He was in front of the new courtyard at the Lord’s temple. 6He said,

Lord, you are the God of our people who lived long ago. You are the God who is in heaven. You rule over all the kingdoms of the nations. You are strong and powerful. No one can fight against you and win. 7Our God, you drove out the people who lived in this land. You drove them out to make room for your people Israel. You gave this land forever to those who belong to the family line of your friend Abraham. 8They have lived in this land. They’ve built a temple here for your Name. They have said, 9‘Suppose trouble comes on us. It doesn’t matter whether it’s a punishing sword, or plague or hunger. We’ll serve you. We’ll stand in front of this temple where your Name is. We’ll cry out to you when we’re in trouble. Then you will hear us. You will save us.’

10“But here are men from Ammon, Moab and Mount Seir. You wouldn’t allow Israel to march in and attack their territory when the Israelites came from Egypt. So Israel turned away from them. They didn’t destroy them. 11See how they are paying us back. They are coming to drive us out. They want to take over the land you gave us as our share. 12Our God, won’t you please judge them? We don’t have the power to face this huge army that’s attacking us. We don’t know what to do. But we’re looking to you to help us.”

13All the men of Judah stood there in front of the Lord. Their wives, children and little ones were with them.

14Then the Spirit of the Lord came on Jahaziel. He was standing among the people of Israel. He was the son of Zechariah. Zechariah was the son of Benaiah. Benaiah was the son of Jeiel. Jeiel was the son of Mattaniah. Jahaziel was a Levite. He was from the family line of Asaph.

15Jahaziel said, “King Jehoshaphat, listen! All you who live in Judah and Jerusalem, listen! The Lord says to you, ‘Do not be afraid. Do not lose hope because of this huge army. The battle is not yours. It is God’s. 16Tomorrow march down against them. They will be climbing up by the Pass of Ziz. You will find them at the end of the valley in the Desert of Jeruel. 17You will not have to fight this battle. Take your positions. Stand firm. You will see how the Lord will save you. Judah and Jerusalem, do not be afraid. Do not lose hope. Go out and face them tomorrow. The Lord will be with you.’ ”

18Jehoshaphat bowed down with his face toward the ground. All the people of Judah and Jerusalem also bowed down. They worshiped the Lord. 19Then some Levites from the families of Kohath and Korah stood up. They praised the Lord, the God of Israel. They praised him with very loud voices.

20Early in the morning all the people left for the Desert of Tekoa. As they started out, Jehoshaphat stood up. He said, “Judah, listen to me! People of Jerusalem, listen to me! Have faith in the Lord your God. He’ll take good care of you. Have faith in his prophets. Then you will have success.” 21Jehoshaphat asked the people for advice. Then he appointed men to sing to the Lord. He wanted them to praise the Lord because of his glory and holiness. They marched out in front of the army. They said,

“Give thanks to the Lord.

His faithful love continues forever.”

22They began to sing and praise him. Then the Lord hid some men and told them to wait. He wanted them to attack the people of Ammon, Moab and Mount Seir. They had gone into Judah and attacked it. But they lost the battle. 23The Ammonites and Moabites rose up against the men from Mount Seir. They destroyed them. They put an end to them. When they finished killing the men from Seir, they destroyed one another.

24The men of Judah came to the place that looks out over the desert. They turned to look down at the huge army. But all they saw was dead bodies lying there on the ground. No one had escaped. 25So Jehoshaphat and his men went down there to carry off anything of value. Among the dead bodies they found a large amount of supplies, clothes and other things of value. There was more than they could take away. There was so much it took three days to collect all of it. 26On the fourth day they gathered together in the Valley of Berakah. There they praised the Lord. That’s why it’s called the Valley of Berakah to this day.

27Then all the men of Judah and Jerusalem returned to Jerusalem. They were filled with joy. Jehoshaphat led them. The Lord had made them happy because all their enemies were dead. 28They entered Jerusalem and went to the Lord’s temple. They were playing harps, lyres and trumpets.

29All the surrounding kingdoms began to have respect for God. They had heard how the Lord had fought against Israel’s enemies. 30The kingdom of Jehoshaphat was at peace. His God had given him peace and rest on every side.

Jehoshaphat’s Rule Comes to an End

31So Jehoshaphat ruled over Judah. He was 35 years old when he became Judah’s king. He ruled in Jerusalem for 25 years. His mother’s name was Azubah. She was the daughter of Shilhi. 32Jehoshaphat followed the ways of his father Asa. He didn’t wander away from them. He did what was right in the eyes of the Lord. 33But the high places weren’t removed. The people still hadn’t worshiped the God of Israel with all their hearts.

34The other events of Jehoshaphat’s rule from beginning to end are written down. They are written in the official records of Jehu, the son of Hanani. They are written in the records of the kings of Israel.

35Jehoshaphat king of Judah and Ahaziah king of Israel agreed to be friends. Ahaziah did what was evil. 36Jehoshaphat agreed with him to build a lot of ships. They were built at Ezion Geber. They carried goods that were traded for other goods. 37Eliezer was the son of Dodavahu from Mareshah. Eliezer prophesied against Jehoshaphat. He said, “You have joined forces with Ahaziah. So the Lord will destroy what you have made.” The ships were wrecked. They were never able to sail or trade goods.