2 ነገሥት 9 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

2 ነገሥት 9:1-37

ኢዩ ተቀብቶ በእስራኤል ላይ ነገሠ

1ነቢዩ ኤልሳዕ ከነቢያት ማኅበር አንዱን ጠርቶ እንዲህ አለው፤ “ወገብህን ታጥቀህ፣ ይህን የዘይት ማሰሮ በመያዝ በሬማት ወደምትገኘው ገለዓድ ሂድ። 2በዚያም ስትደርስ የናሜሲን የልጅ ልጅ፣ የኢዮሣፍጥን ልጅ ኢዩን ፈልገው። ወደ እርሱም ቀርበህ ከጓደኞቹ ለብቻ ከነጠልኸው በኋላ፣ ወደ እልፍኝ አስገባው። 3ከዚያም ማሰሮውን ይዘህ ዘይቱን በራሱ ላይ አፍስስና፣ ‘እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “እነሆ፤ እኔ በእስራኤል ላይ እንድትነግሥ ቀባሁህ” ’ ብለህ ዐውጅ። ከዚያም በሩን ከፍተህ ሩጥ፤ ፈጽሞ አትዘግይ።”

4ስለዚህ ጕልማሳው ነቢይ በሬማት ወደምትገኘው ገለዓድ ሄደ። 5በዚያ እንደ ደረሰም፣ የሰራዊቱ ጦር መኰንኖች በአንድነት ተቀምጠው ነበር፤ እርሱም “መኰንን ሆይ፤ ወደ አንተ ተልኬአለሁ” አለ።

ኢዩም፣ “ለማንኛችን ነው?” ሲል ጠየቀ።

እርሱም፣ “መኰንን ሆይ፤ ለአንተ ነው” ብሎ መለሰ።

6ኢዩም ተነሥቶ ወደ ቤት ገባ፤ ከዚያም ነቢዩ ዘይቱን በኢዩ ላይ አፈሰሰና እንዲህ አለ፤ “የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘በእግዚአብሔር ሕዝብ በእስራኤል ላይ እንድትነግሥ ቀብቼሃለሁ። 7የአገልጋዮቼን የነቢያትን ደም እንዲሁም የእግዚአብሔርን አገልጋዮች ደም ሁሉ ከኤልዛቤል እጅ እበቀል ዘንድ አንተ የጌታህን የአክዓብን ቤት ትመታለህ። 8የአክዓብ ቤት በሙሉ ይጠፋል፤ ባሪያም ይሁን ተወላጅ፣ በእስራኤል የሚገኘውን9፥8 ወይም ማንኛውም ገዥ ወይም መሪ የመጨረሻ ወንድ ልጅ ሁሉ ከአክዓብ እቈርጣለሁ። 9ከእንግዲህ የአክዓብን ቤት፣ እንደ ናባጥ ልጅ እንደ ኢዮርብዓም ቤት፣ እንደ አኪያም ልጅ እንደ ባኦስ ቤት አደርገዋለሁ። 10ኤልዛቤልን ግን በኢይዝራኤል ዕርሻ ውሾች ይበሏታል፤ የሚቀብራትም አይኖርም።’ ” ይህን ተናግሮም መዝጊያውን ከፍቶ ሮጠ።

11ኢዩ ወጥቶ የጦር አለቆች ወደ ሆኑት ጓደኞቹ እንደ ደረሰ፣ ከመካከላቸው አንዱ “ሁሉም ነገር ሰላም ነው? ይህ እብድ ወደ አንተ የመጣው ለምንድን ነው?” ሲል ጠየቀው።

ኢዩም “ሰውየውንም ሆነ የሚናገረውን እናንተም ታውቃላችሁ” ሲል መለሰ።

12እነርሱም፣ “ይህማ ትክክል አይደለም፤ ይልቅስ እውነቱን ንገረን” አሉት።

ኢዩም እንዲህ አለ፤ “እርሱ የነገረኝማ ይህ ነው፤ ‘እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ የእስራኤል ንጉሥ እንድትሆን ቀብቼሃለሁ።’ ”

13ከዚያ ሁሉም ቶሎ ብለው ልብሳቸውን እያወለቁ በሚራመድበት ደረጃ ላይ አነጠፉ፤ ከዚያም መለከት ነፍተው፣ “ኢዩ ነግሧል” አሉ።

ኢዩ ኢዮራምንና አካዝያስን ገደለ

9፥21-29 ተጓ ምብ – 2ዜና 22፥7-9

14ስለዚህ የናሜሲ የልጅ ልጅ፣ የኢዮሣፍጥ ልጅ ኢዩ በኢዮራም ላይ አሤረ። በዚህ ጊዜ ኢዮራምና እስራኤል ሁሉ በሬማት የምትገኘውን ገለዓድን ከሶርያ ንጉሥ ከአዛሄል ጥቃት ለማዳን ይጠብቁ ነበር። 15ንጉሥ ኢዮራም9፥15 ዕብራይስጡ ይሆራም ተለዋጩ ትርጕም ያሮም ይለዋል። ግን የሶርያን ንጉሥ አዛሄልን ጦርነት በገጠመው ጊዜ፣ ሶርያውያን ካደረሱበት ቍስል ለማገገም ወደ ኢይዝራኤል ተመልሶ ነበር። ኢዩም፣ “እንግዲህ ሐሳባችሁ እንዲህ ከሆነ፣ ይህን ነገር ወደ ኢይዝራኤል ሄዶ እንዳይናገር፣ ማንም ሰው ከዚህች ከተማ ሾልኮ እንዳይወጣ ጠብቁ” አለ። 16ከዚያም በሠረገላው ተቀምጦ ወደ ኢይዝራኤል ገሠገሠ፤ ይህን ያደረገውም ኢዮራም በዚያ ስለ ተኛና የይሁዳ ንጉሥ አካዝያስም እርሱን ለመጠየቅ ወደዚያው ስለ ወረደ ነው።

17በኢይዝራኤል ግንብ ማማ ላይ የቆመው ጠባቂ የኢዩ ወታደሮች መቅረባቸውን አይቶ፣ “ኧረ ወታደሮች መጡ” በማለት ጮኾ ተናገረ።

ኢዮራምም፣ “አንድ ፈረሰኛ ተጠርቶ፤ እንዲገናኛቸው ላኩትና፣ ‘የመጣችሁት በሰላም ነውን?’ ብሎ ይጠይቅ” ሲል አዘዘ።

18ፈረሰኛውም ኢዩን ለመገናኘት ጋልቦ ሄደና፣ “ንጉሡ፣ ‘የመጣችሁት በሰላም ነውን?’ ብሏል” አለው።

ኢዩም፣ “ስለ ሰላም መጨነቅ የአንተ ጕዳይ አይደለም! ይልቅስ ወደ ኋላ ዕለፍና ተከተለኝ” አለው።

ጠባቂውም፣ “መልእክተኛው ከእነርሱ ዘንድ ደርሷል፤ ነገር ግን ተመልሶ አልመጣም” ብሎ አሳወቀ።

19ስለዚህ ንጉሡ ሌላ ፈረሰኛ ላከ፤ ወደ እነርሱ ዘንድ እንደ ደረሰም፣ “ንጉሡ፣ ‘የመጣችሁት በሰላም ነውን?’ ይላል” አለው።

ኢዩም “ስለ ሰላም መጨነቅ የአንተ ጕዳይ አይደለም! ይልቅስ ወደ ኋላ ዕለፍና ተከተለኝ” አለው።

20ጠባቂው፣ “መልእክተኛው ከእነርሱ ዘንድ ደርሷል፤ ነገር ግን ይህም ተመልሶ አልመጣም፤ የወታደሮቹ መሪ ሠረገላ አነዳዱ ልክ እንደ ናሜሲ ልጅ እንደ ኢዩ አነዳድ ነው፤ ሲነዳም እንደ እብድ ነው” ሲል አሳወቀ።

21ኢዮራምም፣ “በሉ ሠረገላዬን አዘጋጁ” ብሎ አዘዘ። ሠረገላው እንደ ተዘጋጀም፣ የእስራኤል ንጉሥ ኢዮራምና የይሁዳ ንጉሥ አካዝያስ በየሠረገሎቻቸው ሆነው ኢዩን ለመገናኘት ሄዱ፤ የኢይዝራኤላዊው የናቡቴ ርስት በነበረው ዕርሻ ላይም ተገናኙት። 22ኢዮራምም ኢዩን ገና ሲያየው፣ “ኢዩ፣ የመጣኸው በሰላም ነውን?” ሲል ጠየቀው።

ኢዩም፣ “የእናትህ የኤልዛቤል የጣዖት አምልኮና መተት እንዲህ በዝቶ እያለ ምን ሰላም አለ!” ሲል መለሰ።

23ኢዮራምም ሠረገላውን አዙሮ በመሸሽ፣ “አካዝያስ ሆይ፤ ይህ ክዳት ነው!” አለ።

24ከዚያም ኢዩ ቀስቱን በማስፈንጠር ኢዮራምን በትከሻና ትከሻው መካከል ወጋው፤ ፍላጻውም ዘልቆ ልቡን ስለ ወጋው፣ ሠረገላው ውስጥ ዘፍ ብሎ ወደቀ።

25ኢዩም የሠረገላ ኀላፊውን ቢድቃርን እንዲህ አለው፤ “አንሣውና በኢይዝራኤላዊው በናቡቴ ዕርሻ ላይ ጣለው፤ አንተና እኔ አባቱን አክዓብን በየሠረገሎቻችን ሆነን ተከትለነው ስንሄድ፣ እግዚአብሔር ይህን ትንቢት እንዲህ ሲል እንደ ተናገረበት አስታውስ፤ 26‘ትናንት የናቡቴንና የልጆቹን ደም አይቻለሁ፤ ይላል እግዚአብሔር’ ይህንም በዚሁ ዕርሻ ላይ በርግጥ አንተው እንድትከፍል አደርግሃለሁ፤ ይላል እግዚአብሔር9፥26 1ነገ 2፥19 ይመ አሁንም በእግዚአብሔር ቃል በተነገረው መሠረት አንሣውና በዚሁ ዕርሻ ውስጥ ጣለው።”

27የይሁዳ ንጉሥ አካዝያስም ይህን ሲያይ፣ ወደ ቤት ሀጋን በሚያወጣው መንገድ ሸሸ፤9፥27 ወይም በአትክልቱ ስፍራ በሚገኘው በኩል ሸሸ ኢዩም እያሳደደ ድምፁን ከፍ አድርጎ፣ “እርሱንም ግደሉት!” አለ። እነርሱም በይብለዓም ከተማ አጠገብ በጉር ዐቀበት መንገድ ላይ በሠረገላው ውስጥ እንዳለ አቈሰሉት፤ እርሱ ግን ወደ መጊዶ ሸሽቶ፤ እዚያው ሞተ። 28አገልጋዮቹም በሠረገላ አድርገው ወደ ኢየሩሳሌም ወሰዱት፤ በዳዊትም ከተማ ከአባቶቹ ጋር በመቃብሩ ቀበሩት። 29አካዝያስ በይሁዳ የነገሠው፣ የአክዓብ ልጅ ኢዮራም በነገሠ በዐሥራ አንደኛው ዓመት ነበር።

ኤልዛቤል ተገደለች

30ከዚያም ኢዩ ወደ ኢይዝራኤል ሄደ፤ ኤልዛቤልም ይህን በሰማች ጊዜ ዐይኗን ተኳኵላ፣ ጠጕሯንም አሰማምራ በመስኮት ትመለከት ነበር። 31ኢዩ የቅጥሩን በር ዐልፎ ሲገባ፣ “ጌታህን የገደልህ አንተ ዘምሪ የመጣኸው በሰላም ነውን?”9፥31 ወይም፣ ጌታውን የገደለው ዘምሪ ሰላም አለውን? ስትል ጠየቀችው።

32ቀና ብሎ ወደ መስኮቱ ተመለከተና፣ “ማነህ አንተ? ማነው የሚተባበረኝ” ሲል ጮኾ ተጣራ። ሁለት ሦስት ጃንደረቦችም ቍልቍል ወደ እርሱ ተመለከቱ፤ 33ኢዩም፣ “ወደ ታች ወርውሯት!” አለ፤ እነርሱም ወረወሯት፤ ፈረሶቹ ሲረጋግጧትም ደሟ በግንቡና በፈረሶቹ ላይ ተረጨ።

34ኢዩም ገብቶ በላ፤ ጠጣም። ከዚያም፣ “ምንም ቢሆን የንጉሥ ልጅ ናትና ይህችን የተረገመች ሴት በሚገባ ቅበሯት” አለ። 35ሊቀብሯት ሲወጡ ግን ከራስ ቅሏ፣ ከእግሯና ከእጇ በቀር ሌላ ያገኙት አልነበረም። 36ተመልሰውም ይህን ሲነግሩት፣ ኢዩ እንዲህ አለ፤ “እግዚአብሔር ለባሪያው ለቴስቢያዊው ለኤልያስ፣ ‘በኢይዝራኤል ምድር ዕርሻ ውስጥ ውሾች የኤልዛቤልን ሥጋ ይበሉታል፤9፥36 1ነገ 21፥23 ይመ 37ሥጋዋም በኢይዝራኤል ምድር ዕርሻ ውስጥ እንደ ፍግ ስለሚሆን፣ ማንም ሰው፣ “ይህች ኤልዛቤል ናት” ሊል አይችልም’ ብሎ የተናገረው ቃል ይህ ነው።”

Thai New Contemporary Bible

2พงศ์กษัตริย์ 9:1-37

เยฮูได้รับการเจิมตั้งเป็นกษัตริย์อิสราเอล

1เอลีชาเรียกผู้เผยพระวจนะคนหนึ่งมาสั่งว่า “จงคาดเอวทับเสื้อคลุมให้ทะมัดทะแมง ถือน้ำมันขวดนี้ไปราโมทกิเลอาด 2เมื่อไปถึงที่นั่นแล้ว ให้ถามหาเยฮูบุตรเยโฮชาฟัทหลานนิมชี นำเขาออกจากกลุ่มเพื่อนและพาเข้าไปในห้องชั้นใน 3แล้วรินน้ำมันลงบนศีรษะของเขาและประกาศว่า ‘องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสดังนี้ว่า เราเจิมตั้งเจ้าให้เป็นกษัตริย์เหนืออิสราเอล’ จากนั้นเจ้าจงเปิดประตูและวิ่งไป อย่าชักช้า!”

4ฉะนั้นผู้เผยพระวจนะหนุ่มจึงไปที่ราโมทกิเลอาด 5เมื่อเขาไปถึงที่นั่นก็พบนายทัพทั้งหลายนั่งอยู่ด้วยกัน จึงกล่าวว่า “ข้าพเจ้ามีเรื่องจะเรียนท่านแม่ทัพ”

เยฮูถามว่า “แม่ทัพคนไหนล่ะ?”

เขาตอบว่า “ท่านนี่แหละ ท่านแม่ทัพ”

6เยฮูจึงลุกขึ้นเข้าไปในบ้าน แล้วผู้เผยพระวจนะรินน้ำมันลงบนศีรษะของเยฮูและประกาศว่า “พระยาห์เวห์พระเจ้าแห่งอิสราเอลตรัสว่า ‘เราเจิมตั้งเจ้าให้เป็นกษัตริย์เหนืออิสราเอลประชากรขององค์พระผู้เป็นเจ้า 7เจ้าจงทำลายล้างราชวงศ์อาหับนายของเจ้า เราจะแก้แค้นให้กับโลหิตของผู้เผยพระวจนะผู้รับใช้ของเรา และบรรดาผู้รับใช้องค์พระผู้เป็นเจ้าซึ่งถูกเยเซเบลสังหาร 8ทั้งราชวงศ์ของอาหับจะพินาศ เราจะประหารผู้ชายทุกคนในวงศ์วานของอาหับทั้งที่เป็นทาสหรือเป็นไทในอิสราเอล 9เราจะให้วงศ์วานของอาหับเป็นเหมือนวงศ์วานของเยโรโบอัมบุตรเนบัทและเหมือนวงศ์วานของบาอาชาบุตรอาหิยาห์ 10ส่วนเยเซเบลจะถูกสุนัขกัดกินบนที่ดินผืนนั้นในยิสเรเอล และจะไม่มีใครฝังศพพระนาง’ ” แล้วผู้เผยพระวจนะคนนั้นก็เปิดประตูวิ่งออกไป

11เมื่อเยฮูกลับไปหาเพื่อนพ้อง เพื่อนคนหนึ่งถามเขาว่า “ทุกอย่างเรียบร้อยดีหรือ? เจ้าคนบ้านั่นมาหาท่านทำไม?”

เยฮูตอบว่า “พวกท่านก็รู้ว่าเขาเป็นใครและมาพูดเรื่องอะไร”

12พวกเขาตอบว่า “อย่าบ่ายเบี่ยงเลย! จงบอกมาเถิด”

เยฮูจึงกล่าวว่า “เขาบอกเราว่า ‘องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสดังนี้ว่าเราได้เจิมตั้งเจ้าให้เป็นกษัตริย์เหนืออิสราเอล’ ”

13พวกเขาจึงกุลีกุจอเอาเสื้อคลุมของตนปูบนบันไดให้เยฮูยืน พวกเขาเป่าแตรและร้องประกาศว่า “เยฮูเป็นกษัตริย์!”

เยฮูปลงพระชนม์โยรัมและอาหัสยาห์

(2พศด.22:7-9)

14ฉะนั้นเยฮูบุตรเยโฮชาฟัทหลานนิมชีได้กบฏต่อโยรัม (โยรัมกับกองทัพอิสราเอลสู้รบป้องกันเมืองราโมทกิเลอาดกับกษัตริย์ฮาซาเอลแห่งอารัม 15แต่กษัตริย์โยรัม9:15 ภาษาฮีบรูว่าเยโฮรัมเป็นอีกรูปหนึ่งของโยรัมเช่นเดียวกับข้อ 17 และ 21-24เสด็จกลับมายังยิสเรเอลเพื่อพักฟื้นจากอาการบาดเจ็บเพราะน้ำมือของชาวอารัมในการสู้รบกับกษัตริย์ฮาซาเอลแห่งอารัม) เยฮูกล่าวว่า “ในเมื่อพวกท่านเห็นชอบดังนี้ก็อย่าให้ใครเล็ดลอดไปแจ้งข่าวนี้ที่ยิสเรเอล” 16แล้วเยฮูก็ขับรถม้าศึกมาที่ยิสเรเอลเพราะโยรัมประทับพักฟื้นอยู่ที่นั่น กษัตริย์อาหัสยาห์แห่งยูดาห์ก็ได้เสด็จมาเยี่ยมโยรัมด้วย

17ยามรักษาการณ์บนหอคอยของยิสเรเอลเห็นเยฮูกับกองทหารของเยฮูเข้ามาใกล้ก็ร้องตะโกนว่า “ข้าพเจ้าเห็นกองทหารกำลังตรงมาทางนี้”

โยรัมตรัสสั่งว่า “ส่งพลม้าไปพบพวกเขาและถามว่า ‘ท่านมาอย่างสันติหรือ?’ ”

18พลม้านั้นออกไปพบเยฮูและกล่าวว่า “กษัตริย์ให้มาถามว่า ‘ท่านมาอย่างสันติหรือ?’ ”

เยฮูตอบว่า “ท่านจะมาพูดอะไรเรื่องสันติภาพ? จงตามเรามาเถิด”

ยามรักษาการณ์ทูลกษัตริย์ว่า “ผู้สื่อสารออกไปพบพวกเขาแล้ว แต่ไม่ได้กลับมา”

19กษัตริย์จึงส่งพลม้าออกไปเป็นครั้งที่สอง เมื่อเขามาถึงก็แจ้งว่า “กษัตริย์ให้มาถามว่า ‘ท่านมาอย่างสันติหรือ?’ ”

เยฮูตอบว่า “ท่านจะมาพูดอะไรเรื่องสันติภาพ? จงตามเรามาเถิด”

20ยามรายงานว่า “ผู้สื่อสารไปพบพวกนั้นแล้วก็ไม่กลับมาอีก ดูจากการขับรถน่าจะเป็นเยฮูบุตรนิมชี เขาขับมาเร็วอย่างบ้าคลั่ง”

21โยรัมตรัสสั่งว่า “เตรียมรถม้าศึกของเราให้พร้อม” จากนั้นกษัตริย์โยรัมแห่งอิสราเอลและกษัตริย์อาหัสยาห์แห่งยูดาห์ต่างก็เสด็จขึ้นรถม้าศึกของตนออกมาพบเยฮู และประจันหน้ากันที่ทุ่งนาของนาโบทชาวยิสเรเอล 22เมื่อโยรัมเห็นเยฮูก็ตรัสถามว่า “เจ้ามาอย่างสันติหรือเยฮู?”

เยฮูตอบว่า “จะสันติได้อย่างไรในเมื่อยังมีการกราบไหว้รูปเคารพ และการเล่นคาถาอาคมของเยเซเบลราชมารดาของฝ่าพระบาทอยู่มากมายเช่นนี้?”

23โยรัมทรงหันกลับและหนีไป พลางตรัสบอกอาหัสยาห์ว่า “อาหัสยาห์! พวกนี้เป็นกบฏ!”

24เยฮูจึงโก่งธนูยิงออกไปเต็มแรง ถูกโยรัมที่กลางหลัง ลูกธนูเสียบทะลุหัวใจโยรัมล้มลงในรถม้าศึก 25เยฮูกล่าวกับบิดคาร์พลรถรบของเขาว่า “เอาศพของโยรัมโยนลงไปบนที่ดินของนาโบทชาวยิสเรเอล จำได้ไหมเมื่อครั้งเราสองคนขี่ม้าติดตามอาหับบิดาของเขา องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงสำแดงคำพยากรณ์แก่เราเกี่ยวกับเขาว่า 26องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงประกาศว่า เมื่อวานนี้เราได้เห็นเลือดของนาโบทกับลูกๆ และเราจะให้เจ้าชดใช้บนที่ดินนี้ องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสดังนั้น’9:26 1พกษ.21:19 บัดนี้จงทิ้งร่างของเขาไว้บนที่ผืนนั้นตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสไว้”

27เมื่อกษัตริย์อาหัสยาห์แห่งยูดาห์เห็นสิ่งที่เกิดขึ้น ก็เสด็จหนีไปตามเส้นทางสู่เบธฮักกาน9:27 หรือหนีไปทางบ้านสวน เยฮูขี่ม้าไล่ตามและร้องตะโกนว่า “ฆ่าคนนี้ด้วย!” พวกทหารจึงทำให้อาหัสยาห์บาดเจ็บอยู่ในรถม้าศึกระหว่างทางขึ้นไปยังกูรใกล้อิบเลอัม แต่อาหัสยาห์หนีไปไกลถึงเมกิดโดและสิ้นพระชนม์ที่นั่น 28ข้าราชบริพารรับพระศพขึ้นรถม้าศึกกลับมายังเยรูซาเล็ม และฝังไว้กับบรรพบุรุษในอุโมงค์ของพระองค์ที่เมืองดาวิด 29(กษัตริย์อาหัสยาห์ขึ้นครองราชย์เหนือยูดาห์ ตรงกับปีที่สิบเอ็ดของรัชกาลกษัตริย์โยรัมโอรสของอาหับ)

เยเซเบลถูกปลงพระชนม์

30เมื่อเยเซเบลได้ยินว่าเยฮูมาที่ยิสเรเอล ก็เขียนตาแต่งผมและมองออกมานอกหน้าต่าง 31เมื่อเยฮูผ่านประตูวังเข้ามา พระนางก็ร้องถามว่า “มาดีหรือเปล่า เจ้าฆาตกรศิมรีผู้ฆ่านายของตัวเอง?”9:31 หรือ “ศิมรีผู้สังหารนายของเขายังเป็นสุขอยู่หรือ?

32เยฮูมองขึ้นไปที่หน้าต่างและร้องตะโกนว่า “มีใครอยู่ฝ่ายเราบ้าง? มีใครบ้าง?” ขันทีสองสามคนก็มองลงมา 33เยฮูจึงกล่าวว่า “โยนนางลงมา!” พวกเขาก็ช่วยกันจับพระนางทิ้งลงมาทางหน้าต่าง โลหิตกระเซ็นเปรอะกำแพงและม้า ขณะที่พระนางถูกม้าเหยียบ

34เยฮูเข้าไปในวังรับประทานอาหารและดื่ม แล้วเขากล่าวว่า “ให้ใครออกไปฝังผู้หญิงที่ถูกสาปแช่งคนนั้นเถิด เพราะนางเป็นธิดากษัตริย์” 35แต่เมื่อพวกเขาออกไปจะฝังศพพระนาง ก็พบแต่หัวกะโหลก กระดูกมือ และกระดูกเท้า 36จึงกลับมาบอกเยฮู เยฮูจึงกล่าวว่า “นี่แหละเป็นไปตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าได้ตรัสไว้ผ่านทางเอลียาห์ชาวทิชบีผู้รับใช้ของพระองค์ว่าสุนัขจะกัดกินเนื้อเยเซเบล9:36 1พกษ.21:23บนที่ดินผืนนั้นในยิสเรเอล 37ร่างของนางจะกระจัดกระจายเหมือนขยะบนท้องทุ่งของยิสเรเอล จนไม่มีใครบอกได้ว่า ‘นี่คือเยเซเบล’ ”