2 ነገሥት 9 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

2 ነገሥት 9:1-37

ኢዩ ተቀብቶ በእስራኤል ላይ ነገሠ

1ነቢዩ ኤልሳዕ ከነቢያት ማኅበር አንዱን ጠርቶ እንዲህ አለው፤ “ወገብህን ታጥቀህ፣ ይህን የዘይት ማሰሮ በመያዝ በሬማት ወደምትገኘው ገለዓድ ሂድ። 2በዚያም ስትደርስ የናሜሲን የልጅ ልጅ፣ የኢዮሣፍጥን ልጅ ኢዩን ፈልገው። ወደ እርሱም ቀርበህ ከጓደኞቹ ለብቻ ከነጠልኸው በኋላ፣ ወደ እልፍኝ አስገባው። 3ከዚያም ማሰሮውን ይዘህ ዘይቱን በራሱ ላይ አፍስስና፣ ‘እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “እነሆ፤ እኔ በእስራኤል ላይ እንድትነግሥ ቀባሁህ” ’ ብለህ ዐውጅ። ከዚያም በሩን ከፍተህ ሩጥ፤ ፈጽሞ አትዘግይ።”

4ስለዚህ ጕልማሳው ነቢይ በሬማት ወደምትገኘው ገለዓድ ሄደ። 5በዚያ እንደ ደረሰም፣ የሰራዊቱ ጦር መኰንኖች በአንድነት ተቀምጠው ነበር፤ እርሱም “መኰንን ሆይ፤ ወደ አንተ ተልኬአለሁ” አለ።

ኢዩም፣ “ለማንኛችን ነው?” ሲል ጠየቀ።

እርሱም፣ “መኰንን ሆይ፤ ለአንተ ነው” ብሎ መለሰ።

6ኢዩም ተነሥቶ ወደ ቤት ገባ፤ ከዚያም ነቢዩ ዘይቱን በኢዩ ላይ አፈሰሰና እንዲህ አለ፤ “የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘በእግዚአብሔር ሕዝብ በእስራኤል ላይ እንድትነግሥ ቀብቼሃለሁ። 7የአገልጋዮቼን የነቢያትን ደም እንዲሁም የእግዚአብሔርን አገልጋዮች ደም ሁሉ ከኤልዛቤል እጅ እበቀል ዘንድ አንተ የጌታህን የአክዓብን ቤት ትመታለህ። 8የአክዓብ ቤት በሙሉ ይጠፋል፤ ባሪያም ይሁን ተወላጅ፣ በእስራኤል የሚገኘውን9፥8 ወይም ማንኛውም ገዥ ወይም መሪ የመጨረሻ ወንድ ልጅ ሁሉ ከአክዓብ እቈርጣለሁ። 9ከእንግዲህ የአክዓብን ቤት፣ እንደ ናባጥ ልጅ እንደ ኢዮርብዓም ቤት፣ እንደ አኪያም ልጅ እንደ ባኦስ ቤት አደርገዋለሁ። 10ኤልዛቤልን ግን በኢይዝራኤል ዕርሻ ውሾች ይበሏታል፤ የሚቀብራትም አይኖርም።’ ” ይህን ተናግሮም መዝጊያውን ከፍቶ ሮጠ።

11ኢዩ ወጥቶ የጦር አለቆች ወደ ሆኑት ጓደኞቹ እንደ ደረሰ፣ ከመካከላቸው አንዱ “ሁሉም ነገር ሰላም ነው? ይህ እብድ ወደ አንተ የመጣው ለምንድን ነው?” ሲል ጠየቀው።

ኢዩም “ሰውየውንም ሆነ የሚናገረውን እናንተም ታውቃላችሁ” ሲል መለሰ።

12እነርሱም፣ “ይህማ ትክክል አይደለም፤ ይልቅስ እውነቱን ንገረን” አሉት።

ኢዩም እንዲህ አለ፤ “እርሱ የነገረኝማ ይህ ነው፤ ‘እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ የእስራኤል ንጉሥ እንድትሆን ቀብቼሃለሁ።’ ”

13ከዚያ ሁሉም ቶሎ ብለው ልብሳቸውን እያወለቁ በሚራመድበት ደረጃ ላይ አነጠፉ፤ ከዚያም መለከት ነፍተው፣ “ኢዩ ነግሧል” አሉ።

ኢዩ ኢዮራምንና አካዝያስን ገደለ

9፥21-29 ተጓ ምብ – 2ዜና 22፥7-9

14ስለዚህ የናሜሲ የልጅ ልጅ፣ የኢዮሣፍጥ ልጅ ኢዩ በኢዮራም ላይ አሤረ። በዚህ ጊዜ ኢዮራምና እስራኤል ሁሉ በሬማት የምትገኘውን ገለዓድን ከሶርያ ንጉሥ ከአዛሄል ጥቃት ለማዳን ይጠብቁ ነበር። 15ንጉሥ ኢዮራም9፥15 ዕብራይስጡ ይሆራም ተለዋጩ ትርጕም ያሮም ይለዋል። ግን የሶርያን ንጉሥ አዛሄልን ጦርነት በገጠመው ጊዜ፣ ሶርያውያን ካደረሱበት ቍስል ለማገገም ወደ ኢይዝራኤል ተመልሶ ነበር። ኢዩም፣ “እንግዲህ ሐሳባችሁ እንዲህ ከሆነ፣ ይህን ነገር ወደ ኢይዝራኤል ሄዶ እንዳይናገር፣ ማንም ሰው ከዚህች ከተማ ሾልኮ እንዳይወጣ ጠብቁ” አለ። 16ከዚያም በሠረገላው ተቀምጦ ወደ ኢይዝራኤል ገሠገሠ፤ ይህን ያደረገውም ኢዮራም በዚያ ስለ ተኛና የይሁዳ ንጉሥ አካዝያስም እርሱን ለመጠየቅ ወደዚያው ስለ ወረደ ነው።

17በኢይዝራኤል ግንብ ማማ ላይ የቆመው ጠባቂ የኢዩ ወታደሮች መቅረባቸውን አይቶ፣ “ኧረ ወታደሮች መጡ” በማለት ጮኾ ተናገረ።

ኢዮራምም፣ “አንድ ፈረሰኛ ተጠርቶ፤ እንዲገናኛቸው ላኩትና፣ ‘የመጣችሁት በሰላም ነውን?’ ብሎ ይጠይቅ” ሲል አዘዘ።

18ፈረሰኛውም ኢዩን ለመገናኘት ጋልቦ ሄደና፣ “ንጉሡ፣ ‘የመጣችሁት በሰላም ነውን?’ ብሏል” አለው።

ኢዩም፣ “ስለ ሰላም መጨነቅ የአንተ ጕዳይ አይደለም! ይልቅስ ወደ ኋላ ዕለፍና ተከተለኝ” አለው።

ጠባቂውም፣ “መልእክተኛው ከእነርሱ ዘንድ ደርሷል፤ ነገር ግን ተመልሶ አልመጣም” ብሎ አሳወቀ።

19ስለዚህ ንጉሡ ሌላ ፈረሰኛ ላከ፤ ወደ እነርሱ ዘንድ እንደ ደረሰም፣ “ንጉሡ፣ ‘የመጣችሁት በሰላም ነውን?’ ይላል” አለው።

ኢዩም “ስለ ሰላም መጨነቅ የአንተ ጕዳይ አይደለም! ይልቅስ ወደ ኋላ ዕለፍና ተከተለኝ” አለው።

20ጠባቂው፣ “መልእክተኛው ከእነርሱ ዘንድ ደርሷል፤ ነገር ግን ይህም ተመልሶ አልመጣም፤ የወታደሮቹ መሪ ሠረገላ አነዳዱ ልክ እንደ ናሜሲ ልጅ እንደ ኢዩ አነዳድ ነው፤ ሲነዳም እንደ እብድ ነው” ሲል አሳወቀ።

21ኢዮራምም፣ “በሉ ሠረገላዬን አዘጋጁ” ብሎ አዘዘ። ሠረገላው እንደ ተዘጋጀም፣ የእስራኤል ንጉሥ ኢዮራምና የይሁዳ ንጉሥ አካዝያስ በየሠረገሎቻቸው ሆነው ኢዩን ለመገናኘት ሄዱ፤ የኢይዝራኤላዊው የናቡቴ ርስት በነበረው ዕርሻ ላይም ተገናኙት። 22ኢዮራምም ኢዩን ገና ሲያየው፣ “ኢዩ፣ የመጣኸው በሰላም ነውን?” ሲል ጠየቀው።

ኢዩም፣ “የእናትህ የኤልዛቤል የጣዖት አምልኮና መተት እንዲህ በዝቶ እያለ ምን ሰላም አለ!” ሲል መለሰ።

23ኢዮራምም ሠረገላውን አዙሮ በመሸሽ፣ “አካዝያስ ሆይ፤ ይህ ክዳት ነው!” አለ።

24ከዚያም ኢዩ ቀስቱን በማስፈንጠር ኢዮራምን በትከሻና ትከሻው መካከል ወጋው፤ ፍላጻውም ዘልቆ ልቡን ስለ ወጋው፣ ሠረገላው ውስጥ ዘፍ ብሎ ወደቀ።

25ኢዩም የሠረገላ ኀላፊውን ቢድቃርን እንዲህ አለው፤ “አንሣውና በኢይዝራኤላዊው በናቡቴ ዕርሻ ላይ ጣለው፤ አንተና እኔ አባቱን አክዓብን በየሠረገሎቻችን ሆነን ተከትለነው ስንሄድ፣ እግዚአብሔር ይህን ትንቢት እንዲህ ሲል እንደ ተናገረበት አስታውስ፤ 26‘ትናንት የናቡቴንና የልጆቹን ደም አይቻለሁ፤ ይላል እግዚአብሔር’ ይህንም በዚሁ ዕርሻ ላይ በርግጥ አንተው እንድትከፍል አደርግሃለሁ፤ ይላል እግዚአብሔር9፥26 1ነገ 2፥19 ይመ አሁንም በእግዚአብሔር ቃል በተነገረው መሠረት አንሣውና በዚሁ ዕርሻ ውስጥ ጣለው።”

27የይሁዳ ንጉሥ አካዝያስም ይህን ሲያይ፣ ወደ ቤት ሀጋን በሚያወጣው መንገድ ሸሸ፤9፥27 ወይም በአትክልቱ ስፍራ በሚገኘው በኩል ሸሸ ኢዩም እያሳደደ ድምፁን ከፍ አድርጎ፣ “እርሱንም ግደሉት!” አለ። እነርሱም በይብለዓም ከተማ አጠገብ በጉር ዐቀበት መንገድ ላይ በሠረገላው ውስጥ እንዳለ አቈሰሉት፤ እርሱ ግን ወደ መጊዶ ሸሽቶ፤ እዚያው ሞተ። 28አገልጋዮቹም በሠረገላ አድርገው ወደ ኢየሩሳሌም ወሰዱት፤ በዳዊትም ከተማ ከአባቶቹ ጋር በመቃብሩ ቀበሩት። 29አካዝያስ በይሁዳ የነገሠው፣ የአክዓብ ልጅ ኢዮራም በነገሠ በዐሥራ አንደኛው ዓመት ነበር።

ኤልዛቤል ተገደለች

30ከዚያም ኢዩ ወደ ኢይዝራኤል ሄደ፤ ኤልዛቤልም ይህን በሰማች ጊዜ ዐይኗን ተኳኵላ፣ ጠጕሯንም አሰማምራ በመስኮት ትመለከት ነበር። 31ኢዩ የቅጥሩን በር ዐልፎ ሲገባ፣ “ጌታህን የገደልህ አንተ ዘምሪ የመጣኸው በሰላም ነውን?”9፥31 ወይም፣ ጌታውን የገደለው ዘምሪ ሰላም አለውን? ስትል ጠየቀችው።

32ቀና ብሎ ወደ መስኮቱ ተመለከተና፣ “ማነህ አንተ? ማነው የሚተባበረኝ” ሲል ጮኾ ተጣራ። ሁለት ሦስት ጃንደረቦችም ቍልቍል ወደ እርሱ ተመለከቱ፤ 33ኢዩም፣ “ወደ ታች ወርውሯት!” አለ፤ እነርሱም ወረወሯት፤ ፈረሶቹ ሲረጋግጧትም ደሟ በግንቡና በፈረሶቹ ላይ ተረጨ።

34ኢዩም ገብቶ በላ፤ ጠጣም። ከዚያም፣ “ምንም ቢሆን የንጉሥ ልጅ ናትና ይህችን የተረገመች ሴት በሚገባ ቅበሯት” አለ። 35ሊቀብሯት ሲወጡ ግን ከራስ ቅሏ፣ ከእግሯና ከእጇ በቀር ሌላ ያገኙት አልነበረም። 36ተመልሰውም ይህን ሲነግሩት፣ ኢዩ እንዲህ አለ፤ “እግዚአብሔር ለባሪያው ለቴስቢያዊው ለኤልያስ፣ ‘በኢይዝራኤል ምድር ዕርሻ ውስጥ ውሾች የኤልዛቤልን ሥጋ ይበሉታል፤9፥36 1ነገ 21፥23 ይመ 37ሥጋዋም በኢይዝራኤል ምድር ዕርሻ ውስጥ እንደ ፍግ ስለሚሆን፣ ማንም ሰው፣ “ይህች ኤልዛቤል ናት” ሊል አይችልም’ ብሎ የተናገረው ቃል ይህ ነው።”

Persian Contemporary Bible

دوم پادشاهان 9:1-37

ييهو برای سلطنت در اسرائيل تدهين می‌شود

1در اين هنگام اليشع يک نفر از گروه انبيا را احضار كرد و به او گفت: «برای رفتن به راموت جلعاد آماده شو. اين ظرف روغن زيتون را نيز بردار و همراه خود ببر. 2وقتی به آنجا رسيدی ييهو را پيدا كن. او پسر يهوشافاط و نوهٔ نمشی است. او را از نزد دوستانش به اتاق خلوتی ببر 3و اين روغن را بر سرش بريز. به او بگو كه خداوند او را به پادشاهی اسرائيل انتخاب كرده است. سپس در را باز كن و به سرعت از آنجا دور شو.»

4وقتی آن نبی جوان به راموت جلعاد رسيد، 5ييهو را ديد كه با ساير سرداران لشكر نشسته است. پس به او گفت: «ای سردار، برای شما پيغامی دارم.»

ييهو پرسيد: «برای كدام يک از ما؟»

جواب داد: «برای شما.»

6بنابراين ييهو بلند شد و به داخل خانه رفت. آن نبی جوان روغن را بر سر ييهو ريخت و گفت كه خداوند، خدای اسرائيل می‌فرمايد: «من تو را به پادشاهی قوم خود، اسرائيل انتخاب كرده‌ام. 7تو بايد خاندان اخاب را نابود كنی و انتقام خون انبيا و ساير خدمتگزاران مرا كه به دست ايزابل، همسر اخاب كشته شده‌اند، بگيری. 8ريشهٔ خاندان اخاب بايد به کلی از زمين كنده شود و تمام مردانش نابود شوند. 9دودمان او را از بين خواهم برد همانطور كه خاندان يربعام (پسر نباط) و بعشا (پسر اخيا) را از بين بردم. 10ايزابل زن اخاب را در يزرعيل سگها خواهند خورد و كسی او را دفن نخواهد كرد.»

سپس آن نبی در را باز كرد و پا به فرار گذاشت.

11وقتی ييهو نزد دوستانش بازگشت، از او پرسيدند: «آن ديوانه از تو چه می‌خواست؟ آيا اتفاقی افتاده است؟»

ييهو جواب داد: «شما كه خوب می‌دانيد او كه بود و چه می‌خواست بگويد.»

12گفتند: «نه، ما نمی‌دانيم. بگو چه گفت.»

جواب داد: «به من گفت كه خداوند مرا به پادشاهی اسرائيل انتخاب كرده است.»

13سرداران فوری پله‌های خانه را با رداهای خود فرش كردند و شيپور زده، اعلان كردند: «ييهو پادشاه است!»

يورام و اخزيا به دست ييهو كشته می‌شوند

14آنگاه ييهو (پسر يهوشافاط و نوهٔ نمشی) بر ضد يورام پادشاه، قيام كرد.

(يورام كه با نيروهای خود در راموت جلعاد از اسرائيل در برابر نيروهای حزائيل، پادشاه سوريه، دفاع می‌كرد، 15در اين هنگام به يزرعيل بازگشته بود تا از جراحاتی كه در جنگ برداشته بود، التيام پيدا كند.)

ييهو به سرداران همراه خود گفت: «اگر شما می‌خواهيد من پادشاه شوم، نگذاريد كسی به يزرعيل فرار كند و اين خبر را به آنجا برساند.»

16سپس ييهو بر عرابه‌ای سوار شد و به يزرعيل رفت. يورام مجروح و در شهر يزرعيل بستری بود. (اخزيا، پادشاه يهودا نيز كه به عيادت او رفته بود، در آنجا به سر می‌برد.) 17دیدبانی كه بر برج شهر يزرعيل بود، وقتی ديد ييهو و همراهانش می‌آيند با صدای بلند خبر داده، گفت: «چند سوار به اين طرف می‌آيند.»

يورام پادشاه گفت: «سواری بفرست تا بپرسد خبر خوشی دارند يا نه.»

18پس سواری به پيشواز ييهو رفت و گفت: «پادشاه می‌خواهد بداند كه خبر خوشی داريد يا نه.»

ييهو پاسخ داد: «تو را چه به خبر خوش؟ به دنبال من بيا!»

دیدبان به پادشاه خبر داده، گفت كه قاصد نزد آن سواران رسيد، ولی باز نگشت. 19پس پادشاه سوار ديگری فرستاد. او نزد ايشان رفت و گفت: «پادشاه می‌خواهد بداند كه خبر خوشی داريد يا نه.»

ييهو جواب داد: «تو را چه به خبر خوش؟ به دنبال من بيا!»

20دیدبان باز خبر داده، گفت: «او هم باز نگشت! اين سوار بايد ييهو باشد چون ديوانه‌وار می‌راند.»

21يورام پادشاه فرمان داده، گفت: «عرابهٔ مرا فوراً حاضر كنيد!» آنگاه او و اخزيا، پادشاه يهودا، هر يک بر عرابه خود سوار شده، به استقبال ييهو از شهر بيرون رفتند و در مزرعهٔ نابوت يزرعيلی به او رسيدند. 22يورام از او پرسيد: «ای ييهو، آيا خبر خوشی داری؟»

ييهو جواب داد: «مادامی كه بت‌پرستی و جادوگری مادرت ايزابل رواج دارد، چه خبر خوشی می‌توان داشت؟»

23يورام چون اين را شنيد عرابه‌اش را برگردانيد و در حال فرار به اخزيا گفت: «اخزيا، خيانت است! خيانت!» 24آنگاه ييهو كمان خود را با قوت تمام كشيده به وسط شانه‌های يورام نشانه رفت و قلب او را شكافت و او به كف عرابه‌اش افتاد.

25‏-26ييهو به سردار خود، بِدقَر گفت: «جنازهٔ او را بردار و به داخل مزرعهٔ نابوت بينداز، زيرا يكبار كه من و تو سوار بر عرابه، پشت سر پدرش اخاب بوديم، خداوند اين پيغام را به او داد: ”من در اينجا در مزرعهٔ نابوت تو را به سزای عملت خواهم رساند، زيرا نابوت و پسرانش را كشتی و من شاهد بودم.“9‏:25‏و26 نگاه کنيد به اول پادشاهان 21‏:19.‏ پس حال همانطور كه خداوند فرموده است، او را در مزرعهٔ نابوت بينداز.»

27هنگامی كه اخزيا، پادشاه يهودا، اين وضع را ديد به سوی شهر بيت‌هگان فرار كرد. ييهو به تعقيب وی پرداخت و فرياد زد: «او را هم بزنيد.» پس افراد ييهو او را در سربالايی راهی كه به شهر جور می‌رود و نزديک يبلعام است، در عرابه‌اش مجروح كردند. او توانست تا مجدو فرار كند، ولی در آنجا مرد. 28افرادش جنازهٔ او را در عرابه‌ای به اورشليم بردند و در آرامگاه سلطنتی دفن كردند. 29(اخزيا در يازدهمين سال سلطنت يورام، پادشاه اسرائيل، پادشاه يهودا شده بود.)

ملكه ايزابل كشته می‌شود

30ايزابل وقتی شنيد ييهو به يزرعيل آمده است، به چشمانش سرمه كشيد و موهايش را آرايش كرد و كنار پنجره به تماشا نشست. 31وقتی ييهو از دروازه وارد شد، ايزابل او را صدا زده، گفت: «ای قاتل، ای زمری،9‏:31 زمری نام افسری اسرائيلی بود که پادشاه خود را کشت (نگاه کنيد به اول پادشاهان 16‏:8‏-12).‏ چرا اربابت را كشتی؟»

32ييهو به سوی پنجره نگاه كرد و فرياد زد: «در آنجا چه كسی طرفدار من است؟» دو سه نفر از خدمتگزاران دربار از پنجره به او نگاه كردند.

33ييهو به آنها دستور داد كه او را به پايين بيندازند.

آنها ايزابل را از پنجره پايين انداختند و خونش بر ديوار و پيكرهٔ اسبها پاشيد و خود او زير سم اسبها لگدمال شد.

34ييهو وارد كاخ شد و به خوردن و نوشيدن پرداخت. سپس گفت: «يكی برود و آن زن لعنتی را دفن كند، چون به هر حال او شاهزاده‌ای بوده است.»

35ولی وقتی خدمتگزاران برای دفن ايزابل رفتند، فقط كاسهٔ سر و استخوانهای دستها و پاهای او را پيدا كردند. 36پس بازگشتند و به ييهو گزارش دادند. او گفت: «اين درست همان چيزی است كه خداوند به ايليای نبی فرموده بود كه سگها گوشت ايزابل را در مزرعهٔ يزرعيل می‌خورند 37و باقيماندهٔ بدنش مثل فضله پخش می‌شود تا كسی نتواند او را تشخيص دهد.»