2 ነገሥት 8 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

2 ነገሥት 8:1-29

የሱነማዪቱ ርስት ተመለሰ

1በዚህ ጊዜ ኤልሳዕ፣ ልጇ ከሞት ያስነሣላትን ሴት፣ “እግዚአብሔር በምድሪቱ ላይ የሰባት ዓመት ራብ ስለ ወሰነ፣ ተነሺና ለጊዜው መቈየት ወደምትችዪበት ቦታ ከቤተ ሰብሽ ጋር ሂጂ” አላት። 2ሴቲቱም ተነሥታ የእግዚአብሔር ሰው እንደ ነገራት አደረገች፤ ከነቤተ ሰቧም ሄዳ፣ በፍልስጥኤም ምድር ሰባት ዓመት ተቀመጠች።

3ከሰባት ዓመት በኋላም፣ ከፍልስጥኤም ምድር ተመልሳ መጣች፤ ስለ ቤቷና ስለ መሬቷ አቤቱታ ለማቅረብም ወደ ንጉሡ ሄደች። 4በዚህ ጊዜ ንጉሡ የእግዚአብሔርን ሰው አገልጋይ ግያዝን፣ “ኤልሳዕ ያደረጋቸውን ታላላቅ ሥራዎች ሁሉ እስቲ ንገረኝ” እያለው ነበር። 5ኤልሳዕ ልጇን ከሞት ያስነሣላት ሴት ስለ ቤቷና ስለ መሬቷ ለማመልከት ወደ ንጉሡ ዘንድ የቀረበችውም፣ ኤልሳዕ የሞተውን ልጅ እንዴት እንዳስነሣ ግያዝ ለንጉሡ በሚነግርበት ወቅት ነበር።

ግያዝም፣ “ንጉሥ ጌታዬ ሆይ፤ ሴቲቱ ይህች ናት፤ ኤልሳዕ ከሞት ያስነሣው ልጇም ይህ ነው” አለ። 6ንጉሡም ስለ ስለዚሁ ጕዳይ ጠየቃትና ነገረችው።

ከዚያም ንጉሡ፣ “የነበራትን ሁሉ እንዲሁም ትታ ከሄደችበት ጊዜ አንሥቶ እስካሁን ድረስ ያለውን የዕርሻዋን ሰብል በሙሉ እንድትመልስላት” ሲል አንድ ሹም አዘዘላት።

አዛሄል ቤን ሃዳድን ገደለ

7ኤልሳዕ ወደ ደማስቆ ሄደ፤ በዚያን ጊዜም የሶርያ ንጉሥ ቤን ሃዳድ ታሞ ነበር፤ ለንጉሡም፣ “የእግዚአብሔር ሰው ወደዚህ መጥቷል” ብለው ነገሩት። 8እርሱም አዛሄልን፣ “ገጸ በረከት ይዘህ ሂድና የእግዚአብሔርን ሰው ተገናኘው። በእርሱም አማካይነት፣ ‘ከዚህ በሽታ እድናለሁን?’ ብለህ እግዚአብሔርን ጠይቅ” አለው።

9አዛሄልም ደማስቆ ካፈራቻቸው ምርጥ ነገሮች ሁሉ የአርባ ግመል ጭነት ገጸ በረከት ይዞ ኤልሳዕን ለመገናኘት ሄደ። ሄዶም ፊቱ ቆመና፣ “የሶርያ ንጉሥ ልጅህ ቤን ሃዳድ፣ ‘ከዚህ በሽታ እድናለሁን?’ ሲል ወደ አንተ ልኮኛል” አለው። 10ኤልሳዕም፣ “ሂድና፣ ‘መዳኑንስ በርግጥ ትድናለህ’ በለው፤ ነገር ግን እንደሚሞት እግዚአብሔር ገልጦልኛል” ሲል መለሰለት። 11እስኪያፍር ድረስም፣ አዛሄልን ትኵር ብሎ ተመለከተው፤ ከዚያም የእግዚአብሔር ሰው እንባውን አፈሰሰ።

12አዛሄልም፣ “ጌታዬ የሚያለቅሰው ለምንድን ነው?” ሲል ጠየቀ።

ኤልሳዕም መልሶ፣ “በእስራኤላውያን ላይ የምታደርሰውን ጕዳት ስለማውቅ ነው፤ ምሽጎቻቸውን በእሳት ታቃጥላለህ፤ ጕልማሶቻቸውን በሰይፍ ትገድላለህ፤ ሕፃናታቸውን በምድር ላይ ትፈጠፍጣለህ፤ ያረገዙ ሴቶቻቸውንም ሆድ ትቀድዳለህ” አለው።

13አዛሄልም፣ “ለመሆኑ እንደ ውሻ የሚቈጠር አገልጋይህ ይህን ጀብዱ መፈጸም እንዴት ይችላል?” አለ።

ኤልሳዕም መልሶ፣ “መቼም አንተ በሶርያ ላይ እንደምትነግሥ እግዚአብሔር አሳይቶኛል” አለው።

14ከዚያም አዛሄል ከኤልሳዕ ዘንድ ወጥቶ ወደ ጌታው ተመለሰ፤ ቤን ሃዳድም፣ “ለመሆኑ ኤልሳዕ ምን አለህ?” ሲል ጠየቀው፤ አዛሄልም፣ “በርግጥ ከበሽታህ እንደምትድን ነግሮኛል” አለው። 15በማግስቱም ግን ወፍራም ልብስ ወስዶ በውሃ ከነከረ በኋላ የንጉሡን ፊት ሸፈነው፤ ንጉሡም በዚሁ ሞተ፤ ከዚያም አዛሄል በእግሩ ተተክቶ ነገሠ።

የይሁዳ ንጉሥ ኢዮሆራም

8፥17-24 ተጓ ምብ – 2ዜና 21፥5-1020

16የእስራኤል ንጉሥ የአክዓብ ልጅ ኢዮራም በነገሠ በአምስተኛው ዓመት፣ የኢዮሣፍጥ ልጅ ኢዮሆራም በይሁዳ ነገሠ። 17እርሱም ሲነግሥ ዕድሜው ሠላሳ ሁለት ዓመት ነበር፤ በኢየሩሳሌም ተቀምጦም ስምንት ዓመት ገዛ። 18ያገባት የአክዓብ ልጅ ስለ ነበረች የአክዓብ ቤት እንደ አደረገው ሁሉ፣ እርሱም የእስራኤልን ነገሥታት መንገድ ተከተለ፤ በእግዚአብሔርም ፊት ክፉ ድርጊት ፈጸመ። 19ይሁን እንጂ ስለ ባሪያው ስለ ዳዊት ሲል፣ እግዚአብሔር ይሁዳን ሊያጠፋ አልፈለገም፤ ምክንያቱም ለዳዊትና ለዘሩ መብራት እንደማያሳጣ ተስፋ ሰጥቶ ነበርና።

20በኢዮሆራም ዘመነ መንግሥት፣ ኤዶምያስ በይሁዳ ላይ ዐምፆ የራሱን ንጉሥ አነገሠ። 21ስለዚህም ኢዮሆራም ሠረገሎቹን ሁሉ አሰልፎ ወደ ጸዒር ዘመተ። ኤዶማውያንም እርሱንና የሠረገላ አዛዦቹን ከበቡ፤ እርሱና የሠረገላ አዛዦቹ ግን በሌሊት ተነሥተው ከበባውን ጥሰው ወጡ፤ ሰራዊቱም ሸሽቶ ተመለሰ። 22ኤዶምያስም እስከ ዛሬ ድረስ በይሁዳ ላይ እንደ ዐመፀ ነው፤ ልብናም በዚሁ ጊዜ ዐምፆ ነበር። 23በኢዮሆራም ዘመነ መንግሥት የተከናወነው ሌላው ነገር ሁሉ በይሁዳ ነገሥታት ታሪክ ተጽፎ የሚገኝ አይደለምን? 24ኢዮሆራምም ከአባቶቹ ጋር አንቀላፋ፤ እንደ እነርሱም ሁሉ በዳዊት ከተማ ተቀበረ። ልጁ አካዝያስም በእግሩ ተተክቶ ነገሠ።

የይሁዳ ንጉሥ አካዝያስ

8፥25-29 ተጓ ምብ – 2ዜና 22፥1-6

25የእስራኤል ንጉሥ የአክዓብ ልጅ ኢዮራም በነገሠ በዐሥራ ሁለተኛው ዓመት፣ የኢዮሆራም ልጅ አካዝያስ በይሁዳ ነገሠ። 26አካዝያስ ሲነግሥ ዕድሜው ሀያ ሁለት ዓመት ነበር፤ በኢየሩሳሌም ተቀምጦም አንድ ዓመት ገዛ። እናቱ ጎቶልያ ትባላለች፤ እርሷም የእስራኤል ንጉሥ የዖምሪ የልጅ ልጅ ነበረች። 27አካዝያስ ከአክዓብ ቤተ ሰብ ጋር በጋብቻ የተሳሰረ ስለ ነበር፣ የአክዓብ ቤት እንደ አደረገው ሁሉ፣ እርሱም በአክዓብ ቤት መንገድ ሄደ፤ በእግዚአብሔርም ፊት ክፉ ነገር አደረገ።

28አካዝያስም ከአክዓብ ልጅ ከኢዮራም ጋር ሆኖ በሶርያ ንጉሥ በአዛሄል ላይ ለመዝመት ወደ ሬማት ዘገለዓድ ሄደ፤ ሶርያውያንም በዚያ ኢዮራምን አቈሰሉት። 29ስለዚህ ንጉሥ ኢዮራም፣ በሬማት ከአዛሄል ጋር ባደረገው ጦርነት ሶርያውያን ካደረሱበት ቍስል ለማገገም ወደ ኢይዝራኤል ተመለሰ።

ከዚያም የአክዓብ ልጅ ኢዮራም ስለ ታመመ፣ የይሁዳ ንጉሥ የኢዮራሆም ልጅ አካዝያስ ሊጠይቀው ወደ ኢይዝራኤል ወረደ።

New International Reader’s Version

2 Kings 8:1-29

The Woman From Shunem Gets Her Land Back

1Elisha had brought a woman’s son back to life. He had said to her, “Go away with your family. Stay for a while anywhere you can. The Lord has decided that there won’t be enough food in the land. That will be true for seven years.” 2The woman did just as the man of God told her to. She and her family went away. They stayed in the land of the Philistines for seven years.

3The seven years passed. Then she came back from the land of the Philistines. She went to the king of Israel. She wanted to ask him to get her house and land back. 4The king was talking to Gehazi. Gehazi was the servant of the man of God. The king had said, “Tell me about all the great things Elisha has done.” 5Gehazi was telling the king how Elisha had brought a dead boy back to life. Just then the woman came to ask the king to get her house and land back. She was the woman whose son Elisha had brought back to life.

Gehazi said, “King Joram, this is the woman I’ve been telling you about. And this is her son. He’s the one Elisha brought back to life.” 6The king asked the woman about her house and land. And she told him.

Then he appointed an official to look into her case. The king told him, “Give her back everything that belonged to her. That includes all the money that was earned from her land. It was earned from the day she left the country until now.”

Hazael Murders Ben-Hadad

7Elisha went to Damascus. Ben-Hadad was sick. He was king of Aram. The king was told, “The man of God has come all the way up here.” 8Then the king said to Hazael, “Take a gift with you. Go and see the man of God. Ask him for the Lord’s advice. Ask him whether I will get well again.”

9Hazael went to see Elisha. Hazael took 40 camels with him as a gift. The camels were loaded with all the finest goods of Damascus. Hazael went into Elisha’s house and stood in front of him. Hazael said, “Ben-Hadad has sent me. He is the king of Aram. He asks, ‘Will I get well again?’ ”

10Elisha answered, “Go and tell him, ‘Yes. You will get well again.’ But the Lord has shown me that he will in fact die.” 11Elisha stared at him without looking away. He did it until Hazael felt uncomfortable. Then the man of God began to weep.

12“Why are you weeping?” asked Hazael.

“Because I know how much harm you will do to the people of Israel,” Elisha answered. “You will set fire to their cities that have high walls around them. You will kill their young men with your swords. You will smash their little children on the ground. You will rip open their pregnant women.”

13Hazael said, “How could I possibly do a thing like that? I’m nothing but a dog. I don’t have that kind of power.”

“You will become king of Aram,” Elisha answered. “That’s what the Lord has shown me.”

14Then Hazael left Elisha and returned to his master. Ben-Hadad asked, “What did Elisha say to you?” Hazael replied, “He told me you would get well again.” 15But the next day Hazael got a thick cloth. He soaked it in water. He spread it over the king’s face. He held it there until the king died. Then Hazael became the next king after him.

Jehoram King of Judah

16Jehoram began to rule as king over Judah. It was in the fifth year that Joram was king of Israel. Joram was the son of Ahab. Jehoram was the son of Jehoshaphat. 17Jehoram was 32 years old when he became king. He ruled in Jerusalem for eight years. 18He followed the ways of the kings of Israel, just as the royal family of Ahab had done. In fact, he married a daughter of Ahab. Jehoram did what was evil in the sight of the Lord. 19But the Lord didn’t want to destroy Judah. That’s because the Lord had made a covenant with his servant David. The Lord had promised to keep the lamp of David’s kingdom burning brightly. The Lord had promised that for him and his children after him forever.

20When Jehoram was king over Judah, Edom refused to remain under Judah’s control. Edom set up their own king. 21So Jehoram went to Zair. He took all his chariots with him. The men of Edom surrounded him and his chariot commanders. He got up at night and fought his way out. But his army ran back home. 22To this day Edom has refused to remain under Judah’s control. When Jehoram was Judah’s king, Libnah also refused to remain under the control of Judah.

23The other events of Jehoram’s rule are written down. Everything he did is written in the official records of the kings of Judah. 24Jehoram joined the members of his family who had already died. He was buried in the family tomb in the City of David. Jehoram’s son Ahaziah became the next king after him.

Ahaziah King of Judah

25Ahaziah began to rule as king over Judah. It was in the 12th year that Joram was king of Israel. Joram was the son of Ahab. Ahaziah was the son of Jehoram. 26Ahaziah was 22 years old when he became king. He ruled in Jerusalem for one year. His mother’s name was Athaliah. She was a granddaughter of Omri. Omri had been the king of Israel. 27Ahaziah followed the ways of the royal family of Ahab. Ahaziah did what was evil in the sight of the Lord, just as the family of Ahab had done. That’s because he had married into Ahab’s family.

28Ahaziah joined forces with Joram. They went to war against Hazael at Ramoth Gilead. Joram was the son of Ahab. Hazael was king of Aram. The soldiers of Aram wounded King Joram. 29So he returned to Jezreel to give his wounds time to heal. The soldiers of Aram had wounded him at Ramoth in his battle against Hazael, the king of Aram.

Ahaziah, the son of Jehoram, went down to Jezreel. He went there to see Joram. That’s because Joram had been wounded. Ahaziah was king of Judah. Joram was the son of Ahab.