2 ነገሥት 7 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

2 ነገሥት 7:1-20

1ኤልሳዕም፣ “እንግዲህ የእግዚአብሔርን ቃል ስማ፤ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘በነገው ዕለት በዚሁ ሰዓት፣ በሰማርያ በር አንድ መስፈሪያ ማለፊያ ዱቄት በአንድ ሰቅል፣ ሁለት መስፈሪያ ገብስም በአንድ ሰቅል ይሸጣል’ ” አለ።

2ንጉሡ በክንዱ ላይ የተደገፈውም የጦር አለቃ፣ የእግዚአብሔርን ሰው፣ “እንዲያው ለመሆኑ፣ እግዚአብሔር የሰማያትን መስኮቶች ቢከፍት እንኳ ይህ ሊሆን ይችላልን?” ሲል ጠየቀው።

ኤልሳዕም፣ “ይህን አንተው ራስህ በዐይንህ ታየዋለህ፤ ይሁን እንጂ ከዚያ አንዳች አትቀምስም” አለው።

ከበባው ተወገደ

3በዚህ ጊዜ የሚያሠቅቅ የቈዳ በሽታ የያዛቸው አራት ሰዎች በከተማዪቱ መግቢያ በር አጠገብ ነበሩ፤ እነርሱም እርስ በርሳቸው እንዲህ ተባባሉ፤ “እስክንሞት ድረስ በዚህ የምንቈየው ለምንድን ነው? 4ታዲያ፣ ‘ወደ ከተማዪቱ እንግባ ብንል’ በዚያም ራብ ስላለ እንሞታለን፤ በዚሁም ብንሆን ያው መሞታችን አይቀርም፤ ስለዚህ ወደ ሶርያውያኑ ሰፈር ዝም ብለን እንሂድ፤ ዝም ካሉን ሕይወታችን ትተርፋለች፤ ከገደሉንም ሞቶ መገላገል ነው።”

5ከዚያም መሸትሸት ሲል ተነሥተው ወደ ሶርያውያን ሰፈር ሄዱ፤ ወደ ሰፈሩ ጥግ ሲደርሱም አንድም ሰው በዚያ አልነበረም። 6ይህ የሆነበትም ምክንያት፣ እግዚአብሔር የሠረገሎችንና የፈረሶችን እንዲሁም የብዙ ሰራዊት ድምፅ ሶርያውያን እንዲሰሙ አድርጎ ስለ ነበር ነው፤ እርስ በእርሳቸውም፣ “እነሆ፣ የእስራኤል ንጉሥ በእኛ ላይ አደጋ ለመጣል፣ የኬጢያውያንንና የግብፃውያንን ነገሥታት ቀጥሮ አምጥቶብናል” ተባባሉ። 7ከዚያም መሸትሸት ሲል ተነሥተው ሸሹ፤ ድንኳኖቻቸውን፣ ፈረሶቻቸውንና አህዮቻቸውንም አልወሰዱም ነፍሳቸውን ብቻ ለማዳን ሲሉ ሰፈሩን እንዲሁ እንዳለ ትተው ሄዱ።

8ለምጽ ያለባቸውም ሰዎች ወደ ሰፈሩ አጠገብ ከደረሱ በኋላ፣ ከድንኳኖቹ ወደ አንዱ ገብተው በሉ፤ ጠጡም፤ ከዚያም ብር፣ ወርቅና ልብስ ይዘው በመሄድ ደበቁት። ተመልሰው በመምጣትም ወደ ሌላው ድንኳን ገብተው ሌሎች ነገሮችን በመውሰድ እንደዚሁ ደበቁ።

9እርስ በርሳቸውም፣ “ያደረግነው ትክክል አይደለም፤ ዕለቱ የምሥራች ቀን ነው፤ እኛ ግን የራሳችን ብቻ አደረግነው፤ እስኪነጋም ከቈየን በደለኞች እንሆናለን፤ ስለዚህ ወደ ቤተ መንግሥት በፍጥነት ሄደን እንንገር” ተባባሉ።

10ስለዚህ ሄደው የከተማዪቱን መግቢያ በር ጠባቂዎች ጮኸው በመጥራት፣ “ወደ ሶርያውያን ሰፈር ገባን፤ እዚያም ከታሰሩ ፈረሶችና አህዮች በቀር አንድም ሰው አልነበረም፤ የማንም ድምፅ አልተሰማም፤ ድንኳኖቹም እንዳሉ ናቸው” ብለው ነገሯቸው። 11የበሩ ጠባቂዎችም ይህንኑ አስተጋቡ፤ ዜናውም በቤተ መንግሥቱ ተሰማ።

12ንጉሡም በሌሊት ተነሥቶ ለጦር አለቆቹ እንዲህ አላቸው፤ “ሶርያውያን ያደረጉብንን እነግራችኋለሁ፤ መራባችንን ስለሚያውቁ፣ ‘መቼም መውጣታቸው አይቀርም፤ ከዚያም ከነሕይወታቸው እንማርካቸዋለን፤ እኛም ሰተት ብለን ወደ ከተማዪቱ እንገባለን’ በማለት በገጠር ለመደበቅ ከሰፈራቸው ወጥተዋል።”

13ከጦር አለቆቹም አንዱ እንዲህ አለ፤ “ጥቂት ሰዎች በከተማዪቱ ውስጥ ከተረፉት ፈረሶች አምስቱን ይዘው ይሂዱ፤ ዕጣ ፈንታቸውም በዚህ ከቀሩት እስራኤላውያን ሁሉ ዕድል ጋር አንድ ነው፤ የሚጠብቃቸው ቢኖር በዚህ በሙሉ እንዳለቁት እስራኤላውያን መሆን ብቻ ነው፤ ስለዚህ እንላካቸውና የሆነውን እንይ።”

14ስለዚህ ሁለት ሠረገሎች ከነፈረሶቻቸው መረጡ፤ ንጉሡም፣ “ሂዱና የሆነውን ነገር እዩ” ብሎ ከሶርያውያን ሰራዊት በኋላ እንዲሄዱ ላካቸው። 15እነርሱም እስከ ዮርዳኖስ ድረስ ተከተሏቸው። ሶርያውያን በጥድፊያ ሲሸሹ፣ የጣሉትንም ልብስና ዕቃ በየመንገዱ ላይ ተበታትኖ አገኙ፤ መልክተኞቹም ተመልሰው ይህንኑ ለንጉሡ ነገሩት። 16ከዚያም ሕዝቡ ወጥቶ የሶርያውያንን ሰፈር በዘበዘ፤ ስለዚህ እግዚአብሔር እንደ ተናገረው አንድ መስፈሪያ ማለፊያ ዱቄት በአንድ ሰቅል፣ ሁለት መስፈሪያ ገብስም በአንድ ሰቅል ተሸጠ።

17በዚህ ጊዜ ንጉሡ እጁን ይደግፈው የነበረውን የጦር አለቃ፣ የቅጥሩ በር ኀላፊ አድርጎት ነበርና በበራፉ መተላለፊያ ላይ ሕዝቡ ሲጋፋ ረጋገጠው፤ ያ የእግዚአብሔር ሰው ንጉሡ ወደ እርሱ በመጣ ጊዜ አስቀድሞ እንደ ተናገረውም የጦር አለቃው ሞተ። 18እንዲሁም የእግዚአብሔር ሰው ለንጉሡ፣ “ነገ በዚሁ ሰዓት በሰማርያ በር ላይ አንድ መስፈሪያ ዱቄት በአንድ ሰቅል፣ ሁለት መስፈሪያ ገብስም በአንድ ሰቅል ይሸጣል” ያለውም ተፈጸመ።

19የጦር አለቃው ለእግዚአብሔር ሰው፣ “እግዚአብሔር የሰማይን መስኮቶች ቢከፍት እንኳ ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል?” ብሎት ስለ ነበር፣ የእግዚአብሔር ሰው፣ “ይህን አንተው ራስህ ታያለህ፤ ከዚህ ግን አንዳች አትበላም” ሲል መልሶለት ነበር። 20በበሩ መተላለፊያ ላይ ሕዝቡ ረጋግጦት ስለ ሞተም፣ የተነገረበት በትክክል ደረሰ።

Thai New Contemporary Bible

2พงศ์กษัตริย์ 7:1-20

1เอลีชากล่าวว่า “จงฟังพระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้าองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสดังนี้ว่า วันพรุ่งนี้เวลาราวๆ นี้ แป้งประมาณ 7.3 ลิตร7:1 ภาษาฮีบรูว่า1 ซีห์เช่นเดียวกับข้อ 16 และ 18 หรือข้าวบาร์เลย์ประมาณ 15 ลิตร7:1 ภาษาฮีบรูว่า2 ซีห์เช่นเดียวกับข้อ 16 และ 18 จะซื้อขายกันด้วยเงินหนัก 1 เชเขล7:1 1 เชเขล คือเงินหนักประมาณ 11.5 กรัม มีค่าเท่ากับค่าแรงสองเดือน เช่นเดียวกับข้อ 16 และ 18 ที่ประตูเมืองสะมาเรีย”

2นายทหารที่ติดตามกษัตริย์กล่าวกับคนของพระเจ้าว่า “ต่อให้องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงเปิดฟ้าสวรรค์ก็จะเป็นไปได้หรือ?”

เอลีชาตอบว่า “เจ้าจะเห็นกับตา แต่เจ้าจะไม่มีโอกาสได้กิน!”

วงล้อมแตก

3มีคนโรคเรื้อน7:3 คำภาษาฮีบรูอาจหมายถึง โรคผิวหนังต่างๆ ไม่จำเป็นต้องหมายถึงโรคเรื้อนเท่านั้น เช่นเดียวกับข้อ 8สี่คนนั่งอยู่ตรงทางเข้าประตูเมือง พวกเขาพูดกันว่า “ทำไมมานั่งรอความตายอยู่ที่นี่? 4เราอยู่ที่นี่ก็จะอดตาย ถ้ากลับเข้าไปในเมืองก็อดตายกันอยู่ดี เราไปสวามิภักดิ์ต่อพวกอารัมกันเถิด ถ้าเขาไว้ชีวิตเรา เราก็อยู่ ถ้าเขาฆ่าเรา เราก็ตาย”

5ตอนพลบค่ำพวกเขาพากันไปยังค่ายพักอารัม แต่ไม่มีใครอยู่ที่นั่นเลย 6เพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงบันดาลให้กองทัพอารัมได้ยินเสียงรถม้าศึก เสียงควบม้า เสียงกองทัพใหญ่ จึงพูดกันว่า “กษัตริย์อิสราเอลจ้างพวกฮิตไทต์และกษัตริย์อียิปต์มาโจมตีเราแล้ว!” 7พวกเขาจึงเตลิดหนีไปเมื่อพลบค่ำ ทิ้งเต็นท์ ม้า ลา และข้าวของทุกอย่างไว้ แล้วหนีเอาชีวิตรอด

8เมื่อคนโรคเรื้อนเหล่านั้นมาถึงริมค่าย ก็เข้าไปในเต็นท์และกินดื่ม พวกเขาขนเงินทองและเสื้อผ้าออกมาแล้วซ่อนไว้ พวกเขากลับมาอีกและเข้าไปในเต็นท์อื่น แล้วขนของไปเก็บซ่อนไว้

9แล้วพวกเขาพูดกันว่า “ทำอย่างนี้ไม่ถูก นี่เป็นข่าวดี แล้วเราไม่ยอมบอกใคร หากรอจนถึงวันพรุ่งนี้จะต้องมีโทษหนัก เรารีบกลับไปรายงานทางพระราชวังกันดีกว่า”

10ฉะนั้นพวกเขาจึงกลับมาร้องบอกยามรักษาการณ์ประตูเมืองว่า “พวกเราได้ออกไปที่ค่ายของชาวอารัม พบว่าม้าและลาถูกผูกไว้ เต็นท์ก็เป็นระเบียบดี แต่ไม่มีใครอยู่เลยสักคน” 11ยามรักษาการณ์จึงตะโกนแจ้งข่าวให้ทางพระราชวังทราบ

12กษัตริย์ตื่นบรรทม แล้วตรัสกับทหารทั้งหลายในคืนนั้นว่า “เราจะบอกพวกเจ้าให้ว่า นี่เป็นแผนของอารัม เขารู้ว่าเราอดอยากจึงทิ้งค่ายไปหลบซ่อนตัวอยู่ในทุ่งนา และคิดว่า ‘พวกเขาจะออกมาแน่ๆ เราจะได้จับพวกเขาและบุกเข้ายึดเมือง’ ”

13ทหารคนหนึ่งทูลว่า “เราน่าจะส่งสายสืบไปดูลาดเลา ให้พวกเขาใช้ม้าที่ยังเหลืออยู่สักห้าตัว ถ้าเกิดอะไรขึ้น ก็ไม่ได้สูญเสียอะไรไปมากกว่าอยู่ที่นี่ซึ่งก็ต้องตายเหมือนกับพวกเราชาวอิสราเอลที่เหลือ”

14ดังนั้นเขาเลือกรถม้าศึกมาสองคันพร้อมม้า และกษัตริย์ส่งพวกเขาออกไปยังกองทัพอารัม พระองค์ตรัสสั่งพวกเขาว่า “จงไปดูว่าเกิดอะไรขึ้น” 15พวกเขาตามไปถึงแม่น้ำจอร์แดน พบเสื้อผ้าและเครื่องใช้ไม้สอยซึ่งพวกอารัมทิ้งไว้ตลอดทางเนื่องจากหนีเตลิดไปอย่างชุลมุน แล้วพวกเขากลับมาทูลกษัตริย์ 16ประชาชนจึงกรูกันออกไปยึดข้าวของในค่ายอารัม จึงเป็นจริงตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าได้ตรัสไว้คือ แป้งประมาณ 7.3 ลิตร หรือข้าวบาร์เลย์ประมาณ 15 ลิตร ขายกันในราคาเพียง 1 เชเขลในวันนั้น

17กษัตริย์ทรงแต่งตั้งนายทหารองครักษ์คนนั้นให้ดูแลที่ประตูเมือง แต่เขาถูกประชาชนเหยียบตายที่นั่น ตามที่คนของพระเจ้าได้ทำนายไว้เมื่อวันก่อน คราวที่กษัตริย์เสด็จมาที่บ้านของเขา 18เหตุการณ์เป็นไปตามที่คนของพระเจ้าได้กล่าวกับกษัตริย์ว่า “วันพรุ่งนี้เวลาราวๆ นี้แป้งประมาณ 7.3 ลิตร หรือข้าวบาร์เลย์ประมาณ 15 ลิตร จะซื้อขายกันด้วยเงินหนัก 1 เชเขลที่ประตูเมืองสะมาเรีย”

19แต่นายทหารของกษัตริย์ได้แย้งคนของพระเจ้าว่า “ต่อให้องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงเปิดฟ้าสวรรค์ก็จะเป็นไปได้หรือ?” คนของพระเจ้าตอบว่า “เจ้าจะเห็นกับตา แต่เจ้าจะไม่มีโอกาสได้กิน!” 20และก็เป็นไปตามนั้นทุกประการ เพราะเขาถูกประชาชนเหยียบตายที่ประตูเมือง