2 ነገሥት 20 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

2 ነገሥት 20:1-21

የሕዝቅያስ መታመም

20፥1-11 ተጓ ምብ – 2ዜና 32፥24-26ኢሳ 38፥1-8

1በዚያ ጊዜ ሕዝቅያስ በጠና ታምሞ ሊሞት ተቃርቦ ነበር። የአሞጽ ልጅ ነቢዩ ኢሳይያስም ወደ እርሱ ሄዶ፣ “እግዚአብሔር፣ ‘ትሞታለህ፤ ከእንግዲህ በሕይወት አትኖርምና ቤትህን አስተካክል’ ብሎሃል” አለው።

2ሕዝቅያስም ፊቱን ወደ ግድግዳው መልሶ እንዲህ ሲል ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፤ 3እግዚአብሔር ሆይ፤ በታማኝነትና በፍጹም ልብ በፊትህ እንደ ሄድሁ፣ አንተን ደስ የሚያሰኝህንም እንዳደረግሁ ዐስብ፤” ሕዝቅያስም ምርር ብሎ አለቀሰ።

4ኢሳይያስ የመካከለኛውን አደባባይ ዐልፎ ከመሄዱ በፊት የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እርሱ መጣ፤ 5“ተመለስና የሕዝቤን አለቃ ሕዝቅያስን እንዲህ በለው፤ ‘የአባትህ የዳዊት አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ጸሎትህን ሰምቻለሁ፤ እንባህንም አይቻለሁ፤ እነሆ፤ እፈውስሃለሁ። ከዛሬ ሦስት ቀን በኋላ ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ትወጣለህ፤ 6በዕድሜህ ላይ ዐሥራ አምስት ዓመት እጨምርልሃለሁ፤ አንተንና ይህችንም ከተማ ከአሦር ንጉሥ እጅ እታደጋለሁ፤ ስለ እኔ ስለ ራሴና ስለ ባሪያዬ ስለ ዳዊት ስል ይህችን ከተማ እከላከልላታለሁ።’ ”

7ከዚያም ኢሳይያስ፣ “ትኵስ የበለስ ጥፍጥፍ አዘጋጁ” አላቸው፤ እነርሱም አዘጋጅተው ዕባጩ ላይ አደረጉለት፤ ተፈወሰም።

8ሕዝቅያስም፣ “እግዚአብሔር እኔን ስለ መፈወሱ፣ ከሦስት ቀን በኋላም ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ስለ መውጣቴ ምልክቱ ምንድን ነው?” ሲል ኢሳይያስን ጠየቀው።

9ኢሳይያስም፣ “እግዚአብሔር የሰጠውን ተስፋ እንደሚፈጽም ምልክቱ ይህ ነው፤ ጥላው ዐሥር ደረጃ ወደ ፊት ይቅደምን? ወይስ ዐሥር ደረጃ ወደ ኋላ ይመለስ?” ሲል ጠየቀው።

10ሕዝቅያስም መልሶ፣ “ጥላው ዐሥር ደረጃ ወደ ፊት መሄዱ ቀላል ነገር ነው፤ ይልቁን ዐሥር ደረጃ ወደ ኋላ ይመለስ” አለ።

11ከዚያም ነቢዩ ኢሳይያስ ወደ እግዚአብሔር ጮኸ፤ እግዚአብሔርም አካዝ በሠራው ደረጃ ላይ የወረደውን ጥላ ዐሥር ደረጃ ወደ ኋላው እንዲመለስ አደረገ።

ከባቢሎን የመጡ መልእክተኞች

20፥12-19 ተጓ ምብ – ኢሳ 39፥1-8

20፥20-21 ተጓ ምብ – 2ዜና 32፥32-33

12በዚያን ጊዜ የባቢሎን ንጉሥ የባልዳን ልጅ መሮዳክ ባልዳን የሕዝቅያስን መታመም ሰምቶ ስለ ነበር፣ ደብዳቤና ገጸ በረከት ለሕዝቅያስ ላከለት። 13ሕዝቅያስም መልክተኞቹን ተቀብሎ በዕቃ ቤቱ ያለውን ሁሉ ብሩን፣ ወርቁን ቅመማ ቅመሙንና ከፍ ያለ ዋጋ ያለውን ዘይት የጦር መሣሪያ ግምጃ ቤቱንና በቀረውም ግምጃ ቤት ያለውን በሙሉ አሳያቸው። በቤተ መንግሥቱም ሆነ በመላው ግዛቱ ሕዝቅያስ ሳያሳያቸው የቀረ ምንም ነገር አልነበረም።

14ከዚያም ነቢዩ ኢሳይያስ ወደ ሕዝቅያስ ሄዶ፣ “እነዚያ ሰዎች ምን አሉህ? የመጡትስ ከወዴት ነው?” ሲል ጠየቀው።

ሕዝቅያስም መልሶ፣ “የመጡት ከሩቅ አገር ከባቢሎን ነው” አለው።

15ነቢዩም፣ “በቤተ መንግሥትህ ምን ምን አዩ?” ሲል ጠየቀው።

ሕዝቅያስም፣ “በቤተ መንግሥቴ ያለውን ሁሉ አይተዋል፤ በግምጃ ቤቶቼ ሳላሳያቸው የቀረ ምንም ነገር የለም” አለ።

16ከዚያም ኢሳይያስ ሕዝቅያስን እንዲህ አለው፤ “የእግዚአብሔርን ቃል ስማ፤ 17በቤተ መንግሥትህ ያለው ሁሉ አባቶችህም እስከ ዛሬ ድረስ ያከማቹት በሙሉ ወደ ባቢሎን የሚወሰድበት ጊዜ በርግጥ ይመጣል፤ አንዳች የሚቀር ነገር የለም ይላል እግዚአብሔር18የሥጋህ ቍራጭ የዐጥንትህ ፍላጭ ከሚሆኑት፣ ከምትወልዳቸው ልጆችህ አንዳንዶቹ በምርኮ ይወሰዳሉ፤ በባቢሎንም ቤተ መንግሥት ጃንደረቦች ይሆናሉ።” 19ሕዝቅያስም፣ “የተናገርኸው የእግዚአብሔር ቃል መልካም ነው” ሲል መለሰ፤ “እኔ እስካለሁ ድረስ ሰላምና ጸጥታ ከተገኘ የሆነው ይሁን” ብሎ አስቧልና። 20በሕዝቅያስ ዘመነ መንግሥት የተከናወነው ሌላው ሥራ፣ የፈጸመውም ሁሉ ኵሬውንና ውሃውን ወደ ከተማዪቱ ያመጣበትን የመሬት ለመሬት ቦይ እንዴት አድርጎ እንደ ሠራው በይሁዳ ነገሥታት ታሪክ ተጽፎ የሚገኝ አይደለምን? 21ሕዝቅያስም ከአባቶቹ ጋር አንቀላፋ፤ ልጁ ምናሴም በእግሩ ተተክቶ ነገሠ።

Thai New Contemporary Bible

2พงศ์กษัตริย์ 20:1-21

เฮเซคียาห์ประชวร

(2พศด.32:24-26; อสย.38:1-8)

1ครั้งนั้นเฮเซคียาห์ประชวรหนักใกล้สิ้นพระชนม์ ผู้เผยพระวจนะอิสยาห์บุตรอาโมศมาเข้าเฝ้าพระองค์และทูลว่า “องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสดังนี้ว่า จงจัดการบ้านเมืองให้เรียบร้อยเพราะเจ้าจะไม่หายป่วย แต่เจ้ากำลังจะตาย”

2เฮเซคียาห์ทรงหันพระพักตร์เข้าหากำแพง และอธิษฐานทูลองค์พระผู้เป็นเจ้าว่า 3“ข้าแต่องค์พระผู้เป็นเจ้า ขอทรงระลึกว่าข้าพระองค์ได้ดำเนินชีวิตอยู่ในทางของพระองค์อย่างซื่อสัตย์ ยอมอุทิศตนอย่างสิ้นสุดใจและทำสิ่งที่ดีในสายพระเนตรของพระองค์อย่างไร” แล้วเฮเซคียาห์ก็ทรงกันแสงอย่างขมขื่น

4ก่อนที่อิสยาห์จะก้าวพ้นเขตลานชั้นกลาง พระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้ามาถึงเขาว่า 5“จงกลับไปบอกเฮเซคียาห์ผู้นำของประชากรของเราว่า ‘พระยาห์เวห์พระเจ้าของดาวิดบรรพบุรุษของท่านตรัสดังนี้ว่า เราได้ยินคำอธิษฐานและได้เห็นน้ำตาของเจ้าแล้ว เราจะรักษาเจ้า วันที่สามนับจากนี้เจ้าจะลุกจากเตียงไปที่พระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้าได้ 6เราจะต่ออายุให้เจ้าอีกสิบห้าปี และเราจะช่วยเจ้ากับเมืองนี้ให้พ้นจากมือกษัตริย์อัสซีเรีย เราจะปกป้องเมืองนี้ไว้เพื่อตัวเราเองและเพื่อดาวิดผู้รับใช้ของเรา’ ”

7แล้วอิสยาห์กล่าวว่า “จงเตรียมยาพอกจากมะเดื่อ” พวกเขาจึงทำตามนั้นและนำมาพอกที่ฝี แล้วเฮเซคียาห์ก็หายประชวร

8เฮเซคียาห์ตรัสถามอิสยาห์ว่า “อะไรจะเป็นหมายสำคัญให้รู้ว่าองค์พระผู้เป็นเจ้าจะทรงรักษาเรา และวันที่สามนับจากนี้เราจะขึ้นไปยังพระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้าได้อีก?”

9อิสยาห์ตอบว่า “นี่เป็นหมายสำคัญที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงให้แก่ท่าน เพื่อแสดงว่าองค์พระผู้เป็นเจ้าจะทรงทำตามที่ทรงสัญญาไว้คือ ท่านอยากให้เงาเคลื่อนไปข้างหน้าสิบขั้น หรือถอยหลังไปสิบขั้น?”

10เฮเซคียาห์ตรัสว่า “การที่เงาจะเคลื่อนไปข้างหน้าสิบขั้นก็เป็นเรื่องปกติ ดังนั้นขอให้ถอยหลังสิบขั้นก็แล้วกัน”

11ผู้เผยพระวจนะอิสยาห์จึงกราบทูลองค์พระผู้เป็นเจ้า พระองค์ก็ทรงบันดาลให้เงาบนนาฬิกาแดดของอาหัสเคลื่อนถอยหลังไปสิบขั้น

คณะทูตจากบาบิโลน

(2พศด.32:32-33; อสย.39:1-8)

12ครั้งนั้นเมโรดัคบาลาดันโอรสของกษัตริย์บาลาดันแห่งบาบิโลนได้ทราบข่าวว่าเฮเซคียาห์ประชวรก็ส่งสาส์นและของกำนัลมาให้ 13เฮเซคียาห์ต้อนรับผู้ส่งสาส์นเหล่านั้นและทรงอวดสมบัติทั้งสิ้นในท้องพระคลังให้พวกเขาชม คือเงิน ทอง เครื่องเทศ น้ำมันอย่างดี อาวุธยุทโธปกรณ์ และทุกสิ่งทุกอย่างที่มี ไม่มีสักสิ่งเดียวในพระราชวังหรือทั่วอาณาจักรที่เฮเซคียาห์ไม่ได้อวด

14แล้วผู้เผยพระวจนะอิสยาห์มาเข้าเฝ้ากษัตริย์เฮเซคียาห์ และทูลถามว่า “คนพวกนี้พูดอะไร? พวกเขามาจากไหน?”

เฮเซคียาห์ตรัสตอบว่า “มาจากบาบิโลนดินแดนอันไกลโพ้น”

15ผู้เผยพระวจนะทูลถามว่า “พวกเขาได้เห็นอะไรในวังของท่านบ้าง?”

เฮเซคียาห์ตรัสตอบว่า “พวกเขาเห็นทุกสิ่งทุกอย่างในวังของเรา ไม่มีสักสิ่งเดียวในท้องพระคลังที่เราไม่ได้ให้พวกเขาดู”

16อิสยาห์จึงกล่าวแก่เฮเซคียาห์ว่า “จงฟังพระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้าที่ว่า 17เวลานั้นจะมาถึงอย่างแน่นอน เมื่อทุกอย่างในวังของเจ้าและทุกสิ่งที่บรรพบุรุษของเจ้าได้สะสมไว้จวบจนบัดนี้จะถูกกวาดไปยังบาบิโลน จะไม่มีอะไรเหลือเลย องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสดังนี้ 18และวงศ์วานของเจ้าบางคน เลือดเนื้อเชื้อไขของเจ้าเองจะถูกกวาดต้อนไป ต้องกลายเป็นขันทีอยู่ในวังของกษัตริย์บาบิโลน”

19เฮเซคียาห์ตรัสตอบว่า “พระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้าตามที่ท่านว่ามาก็ดีอยู่” เพราะเฮเซคียาห์ดำริว่า “อย่างน้อยก็ยังจะมีความสงบสุขและความมั่นคงปลอดภัยในชั่วอายุของเราไม่ใช่หรือ?”

20เหตุการณ์อื่นๆ ในรัชกาลของเฮเซคียาห์ ความสำเร็จทั้งปวง การสร้างสระน้ำและท่อส่งน้ำมายังตัวเมืองมีบันทึกไว้ในจดหมายเหตุกษัตริย์แห่งยูดาห์ไม่ใช่หรือ? 21เฮเซคียาห์ทรงล่วงลับไปอยู่กับบรรพบุรุษ แล้วมนัสเสห์โอรสของพระองค์ขึ้นครองราชย์แทน