2 ነገሥት 20 – NASV & BPH

New Amharic Standard Version

2 ነገሥት 20:1-21

የሕዝቅያስ መታመም

20፥1-11 ተጓ ምብ – 2ዜና 32፥24-26ኢሳ 38፥1-8

1በዚያ ጊዜ ሕዝቅያስ በጠና ታምሞ ሊሞት ተቃርቦ ነበር። የአሞጽ ልጅ ነቢዩ ኢሳይያስም ወደ እርሱ ሄዶ፣ “እግዚአብሔር፣ ‘ትሞታለህ፤ ከእንግዲህ በሕይወት አትኖርምና ቤትህን አስተካክል’ ብሎሃል” አለው።

2ሕዝቅያስም ፊቱን ወደ ግድግዳው መልሶ እንዲህ ሲል ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፤ 3እግዚአብሔር ሆይ፤ በታማኝነትና በፍጹም ልብ በፊትህ እንደ ሄድሁ፣ አንተን ደስ የሚያሰኝህንም እንዳደረግሁ ዐስብ፤” ሕዝቅያስም ምርር ብሎ አለቀሰ።

4ኢሳይያስ የመካከለኛውን አደባባይ ዐልፎ ከመሄዱ በፊት የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እርሱ መጣ፤ 5“ተመለስና የሕዝቤን አለቃ ሕዝቅያስን እንዲህ በለው፤ ‘የአባትህ የዳዊት አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ጸሎትህን ሰምቻለሁ፤ እንባህንም አይቻለሁ፤ እነሆ፤ እፈውስሃለሁ። ከዛሬ ሦስት ቀን በኋላ ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ትወጣለህ፤ 6በዕድሜህ ላይ ዐሥራ አምስት ዓመት እጨምርልሃለሁ፤ አንተንና ይህችንም ከተማ ከአሦር ንጉሥ እጅ እታደጋለሁ፤ ስለ እኔ ስለ ራሴና ስለ ባሪያዬ ስለ ዳዊት ስል ይህችን ከተማ እከላከልላታለሁ።’ ”

7ከዚያም ኢሳይያስ፣ “ትኵስ የበለስ ጥፍጥፍ አዘጋጁ” አላቸው፤ እነርሱም አዘጋጅተው ዕባጩ ላይ አደረጉለት፤ ተፈወሰም።

8ሕዝቅያስም፣ “እግዚአብሔር እኔን ስለ መፈወሱ፣ ከሦስት ቀን በኋላም ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ስለ መውጣቴ ምልክቱ ምንድን ነው?” ሲል ኢሳይያስን ጠየቀው።

9ኢሳይያስም፣ “እግዚአብሔር የሰጠውን ተስፋ እንደሚፈጽም ምልክቱ ይህ ነው፤ ጥላው ዐሥር ደረጃ ወደ ፊት ይቅደምን? ወይስ ዐሥር ደረጃ ወደ ኋላ ይመለስ?” ሲል ጠየቀው።

10ሕዝቅያስም መልሶ፣ “ጥላው ዐሥር ደረጃ ወደ ፊት መሄዱ ቀላል ነገር ነው፤ ይልቁን ዐሥር ደረጃ ወደ ኋላ ይመለስ” አለ።

11ከዚያም ነቢዩ ኢሳይያስ ወደ እግዚአብሔር ጮኸ፤ እግዚአብሔርም አካዝ በሠራው ደረጃ ላይ የወረደውን ጥላ ዐሥር ደረጃ ወደ ኋላው እንዲመለስ አደረገ።

ከባቢሎን የመጡ መልእክተኞች

20፥12-19 ተጓ ምብ – ኢሳ 39፥1-8

20፥20-21 ተጓ ምብ – 2ዜና 32፥32-33

12በዚያን ጊዜ የባቢሎን ንጉሥ የባልዳን ልጅ መሮዳክ ባልዳን የሕዝቅያስን መታመም ሰምቶ ስለ ነበር፣ ደብዳቤና ገጸ በረከት ለሕዝቅያስ ላከለት። 13ሕዝቅያስም መልክተኞቹን ተቀብሎ በዕቃ ቤቱ ያለውን ሁሉ ብሩን፣ ወርቁን ቅመማ ቅመሙንና ከፍ ያለ ዋጋ ያለውን ዘይት የጦር መሣሪያ ግምጃ ቤቱንና በቀረውም ግምጃ ቤት ያለውን በሙሉ አሳያቸው። በቤተ መንግሥቱም ሆነ በመላው ግዛቱ ሕዝቅያስ ሳያሳያቸው የቀረ ምንም ነገር አልነበረም።

14ከዚያም ነቢዩ ኢሳይያስ ወደ ሕዝቅያስ ሄዶ፣ “እነዚያ ሰዎች ምን አሉህ? የመጡትስ ከወዴት ነው?” ሲል ጠየቀው።

ሕዝቅያስም መልሶ፣ “የመጡት ከሩቅ አገር ከባቢሎን ነው” አለው።

15ነቢዩም፣ “በቤተ መንግሥትህ ምን ምን አዩ?” ሲል ጠየቀው።

ሕዝቅያስም፣ “በቤተ መንግሥቴ ያለውን ሁሉ አይተዋል፤ በግምጃ ቤቶቼ ሳላሳያቸው የቀረ ምንም ነገር የለም” አለ።

16ከዚያም ኢሳይያስ ሕዝቅያስን እንዲህ አለው፤ “የእግዚአብሔርን ቃል ስማ፤ 17በቤተ መንግሥትህ ያለው ሁሉ አባቶችህም እስከ ዛሬ ድረስ ያከማቹት በሙሉ ወደ ባቢሎን የሚወሰድበት ጊዜ በርግጥ ይመጣል፤ አንዳች የሚቀር ነገር የለም ይላል እግዚአብሔር18የሥጋህ ቍራጭ የዐጥንትህ ፍላጭ ከሚሆኑት፣ ከምትወልዳቸው ልጆችህ አንዳንዶቹ በምርኮ ይወሰዳሉ፤ በባቢሎንም ቤተ መንግሥት ጃንደረቦች ይሆናሉ።” 19ሕዝቅያስም፣ “የተናገርኸው የእግዚአብሔር ቃል መልካም ነው” ሲል መለሰ፤ “እኔ እስካለሁ ድረስ ሰላምና ጸጥታ ከተገኘ የሆነው ይሁን” ብሎ አስቧልና። 20በሕዝቅያስ ዘመነ መንግሥት የተከናወነው ሌላው ሥራ፣ የፈጸመውም ሁሉ ኵሬውንና ውሃውን ወደ ከተማዪቱ ያመጣበትን የመሬት ለመሬት ቦይ እንዴት አድርጎ እንደ ሠራው በይሁዳ ነገሥታት ታሪክ ተጽፎ የሚገኝ አይደለምን? 21ሕዝቅያስም ከአባቶቹ ጋር አንቀላፋ፤ ልጁ ምናሴም በእግሩ ተተክቶ ነገሠ።

Bibelen på hverdagsdansk

2. Kongebog 20:1-21

Hizkijas sygdom og helbredelse

1Senere blev Hizkija alvorligt syg og lå for døden. Da kom profeten Esajas til ham og sagde: „Gør dig klar til at dø, for Herren siger, du ikke bliver rask igen.”

2Esajas gik igen, og Hizkija vendte ansigtet mod væggen. 3„Åh, Herre,” tryglede han, „husk dog på, hvordan jeg altid har bestræbt mig på at adlyde dig og behage dig i alt, hvad jeg har foretaget mig.” Og han græd højt.

4Før Esajas var nået ud af paladsets gård, sagde Herren til ham: 5„Gå tilbage til Hizkija, mit folks leder, og sig til ham: Herren, din forfar Davids Gud, har hørt din bøn og set dine tårer. Jeg vil alligevel helbrede dig, så du i overmorgen kan stå op og gå ind i templet. 6Jeg vil give dig endnu 15 år at leve i, og jeg vil frelse både dig og Jerusalem fra assyrerkongen, for min egen æres skyld og for min tjener Davids skyld.”

7Derpå sagde Esajas til kongens tjenere: „Kom med et figenplaster.” Tjenerne kom så med et figenplaster og lagde det på det syge sted, for at kongen kunne blive rask.

8Hizkija spurgte Esajas: „Hvilket tegn får jeg på, at Herren virkelig vil helbrede mig, så jeg kan gå op til Herrens hus i overmorgen?”

9Esajas svarede: „Hvilket tegn vil du helst have? Skal skyggen på soluret gå ti streger frem eller ti streger tilbage?”

10„Siden skyggen normalt går frem, vil jeg foretrække den gør det modsatte,” svarede Hizkija. „Lad skyggen gå ti streger tilbage.”

11Så bad Esajas Herren om at gøre, som kongen havde bedt om, og Herren lod skyggen gå ti streger tilbage på Ahaz’ solur.

Profeti om bortførelsen til Babylonien

12Nogen tid senere sendte Merodak-Baladan, som var søn af kong Baladan af Babylonien, nogle sendebud af sted med hilsener og en gave til Hizkija, for Babyloniens konge havde hørt om hans sygdom. 13Hizkija var beæret over det fine besøg og viste dem alle sine rigdomme, sit sølv og guld, sine røgelsesstoffer og forskellige aromatiske olier og sit våbenarsenal, ja, der var ikke den ting, han ikke viste dem.

14Bagefter opsøgte Esajas kong Hizkija og spurgte ham: „Hvor kom de mænd fra, og hvad ville de?”

„De kom helt fra Babylonien!” svarede Hizkija.

15„Hvad så de i paladset?” spurgte Esajas.

„Det hele!” svarede Hizkija. „Jeg viste dem alle mine rigdomme.”

16„Hør Herrens ord,” sagde Esajas. 17„Der kommer en dag, hvor alt i det her palads skal føres bort til Babylonien, både de rigdomme, du selv har samlet, og det, dine forfædre har samlet—intet vil blive tilbage. 18Nogle af dine egne efterkommere vil blive bortført og gjort til tjenere ved den babyloniske konges hof.”

19„Det er godt at høre fra Herren,” sagde Hizkija. Han tænkte ved sig selv: „Der er i det mindste fred og ro, så længe jeg lever.”

20Resten af kong Hizkijas historie og hans bedrifter er beskrevet i Judas kongers krønikebog. Der fortælles også om den dam, han konstruerede, og den vandtunnel, han lod grave for at lede vand ind i byen. 21Da han døde, blev hans søn Manasse konge i hans sted.