2 ነገሥት 2 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

2 ነገሥት 2:1-25

ኤልያስ ወደ ሰማይ ዐረገ

1እግዚአብሔር ኤልያስን በዐውሎ ነፋስ ወደ ሰማይ የሚወስድበት ጊዜ ሲደርስ፣ ኤልያስና ኤልሳዕ ከጌልገላ ተነሥተው ይጓዙ ነበር። 2ኤልያስም ኤልሳዕን፣ “እግዚአብሔር እኔን ወደ ቤቴል ልኮኛልና አንተ በዚሁ ቈይ” አለው።

ኤልሳዕ ግን፣ “ሕያው እግዚአብሔርን፣ በሕያው ነፍስህም እምላለሁ፤ ከአንተ አልለይም” አለው። ስለዚህ አብረው ወደ ቤቴል ወረዱ።

3በቤቴል የነበሩ የነቢያት ማኅበር ወደ ኤልሳዕ ወጥተው፣ “እግዚአብሔር፣ ጌታህን ኤልያስን ዛሬ ከአንተ ነጥሎ እንደሚወስደው ዐውቀሃልን?” አሉት።

ኤልሳዕም፣ “አዎን ዐውቄአለሁ፤ እናንተ ግን ዝም በሉ” አለ።

4ከዚያም ኤልያስ፣ “ኤልሳዕ ሆይ፤ እግዚአብሔር እኔን ወደ ኢያሪኮ ልኮኛልና አንተ በዚሁ ቈይ” አለው።

እርሱም፤ “ሕያው እግዚአብሔርን፣ በሕያው ነፍስህም እምላለሁ፤ ከአንተ አልለይም” ሲል መለሰ። ስለዚህ አብረው ወደ ኢያሪኮ ሄዱ።

5በኢያሪኮ የነበሩትም የነቢያት ማኅበር ወደ ኤልሳዕ ወጥተው፣ “ለመሆኑ እግዚአብሔር፣ ጌታህን ኤልያስን ዛሬ ከአንተ ነጥሎ እንደሚወስደው ዐውቀሃልን?” አሉት።

እርሱም፣ “አዎን ዐውቄአለሁ፤ እናንተ ግን ዝም በሉ” ሲል መለሰ።

6ከዚያም ኤልያስ፣ “እግዚአብሔር እኔን ወደ ዮርዳኖስ ልኮኛልና አንተ እዚሁ ቈይ” አለው።

እርሱም፣ “ሕያው እግዚአብሔርን፤ በሕያው ነፍስህም እምላለሁ፤ ከአንተ አልለይም” ሲል መለሰ። ስለዚህ ሁለቱም አብረው ሄዱ።

7ከነቢያትም ማኅበር አምሳው ሄደው፣ ኤልያስና ኤልሳዕ ከቆሙበት ከዮርዳኖስ ትይዩ ራቅ ብለው ቆሙ። 8ኤልያስም ካባውን አውልቆ ጠቀለለውና ውሃውን መታበት፤ ከዚያም ውሃው ግራና ቀኝ ተከፈለ፤ ሁለቱም በደረቅ ምድር ተሻገሩ።

9ከተሻገሩ በኋላም ኤልያስ ኤልሳዕን፤ “ከአንተ ከመወሰዴ በፊት ምን ላደርግልህ እንደምትፈልግ ንገረኝ” አለው።

ኤልሳዕም፣ “መንፈስህ በዕጥፍ እንዲያድርብኝ እለምንሃለሁ” ብሎ መለሰ።

10ኤልያስም፣ “አስቸጋሪ ነገር ጠይቀሃል፤ ይሁን እንጂ እኔ ከአንተ ስወሰድ ብታየኝ፣ እንዳልከው ይሆንልሃል፤ አለዚያ ግን አይሆንም” አለው።

11እያዘገሙም ሲነጋገሩ ሳለ፣ የእሳት ሠረገላና የእሳት ፈረሶች ድንገት በመካከላቸው ገብተው ሁለቱን ለዩአቸው፤ ኤልያስም በዐውሎ ነፋስ ወደ ሰማይ ዐረገ። 12ኤልሳዕም ይህን አይቶ፣ “አባቴ አባቴ የእስራኤል ሠረገሎችና ፈረሰኞች!” ብሎ ጮኸ፤ ዳግመኛም ኤልያስን አላየውም፤ ከዚያም የገዛ ልብሱን ይዞ ከሁለት ቦታ ቀደደው። 13እርሱም ከኤልያስ የወደቀውን ካባ አነሣ፤ ተመልሶም በዮርዳኖስ ወንዝ ዳር ቆመ። 14ከኤልያስ፣ የወደቀውንም ካባ ይዞ ውሃውን መታና፣ “የኤልያስ አምላክ እግዚአብሔር ወዴት ነው?” አለ። ውሃውን ሲመታውም በግራና በቀኝ ተከፍሎለት ተሻገረ። 15ከኢያሪኮም መጥተው ይህን ያዩ የነበሩት የነቢያት ወገኖች፣ “የኤልያስ መንፈስ በኤልሳዕ ላይ ዐርፏል” አሉ፤ ሊያገኙትም ሄደው በፊቱ ወደ መሬት ዝቅ ብለው እጅ ነሡ። 16ከዚያም፣ “እነሆ፤ እኛ አገልጋዮችህ እዚህ አምሳ ጠንካራ ሰዎች አሉን፤ ምናልባትም የእግዚአብሔር መንፈስ ጌታህን አንሥቶ ከአንዱ ተራራ ላይ አስቀምጦት ወይም ከአንዱ ሸለቆ አግብቶት ይሆናልና እስቲ ሄደው ይፈልጉት” አሉት። ኤልሳዕም፣ “አይሆንም፤ አትላኳቸው” አለ።

17አይሆንም ለማለት ዕፍረት እስኪሰማው ድረስ ግድ አሉት፤ ስለዚህ፣ “በሉ እንግዲያው ላኳቸው” አለ። እነርሱም አምሳ ሰዎች ላኩ፤ ሰዎቹም ሦስት ቀን ሙሉ ፈልገው ሳያገኙት ቀሩ። 18በኢያሪኮ ቈይቶ ወደ ነበረው ወደ ኤልሳዕ በተመለሱም ጊዜ፣ “ቀድሞውንስ ቢሆን አትሂዱ ብያችሁ አልነበረምን?” አላቸው።

የውሃው መፈወስ

19የከተማዪቱም ሰዎች ኤልሳዕን፣ “እነሆ ጌታችን፤ እንደምታያት ይህች ከተማ ለኑሮ የተመቸች ናት፤ ይሁን እንጂ ውሃው መጥፎ ሲሆን ምድሪቱም ፍሬ የማትሰጥ ናት” አሉት።

20እርሱም፣ “እስቲ በአዲስ ማሰሮ ጨው ጨምራችሁ አምጡልኝ” አለ፤ እንዳለውም አመጡለት። 21ከዚያም ወደ ውሃው ምንጭ ሄዶ ጨው ጣለበትና “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ይህን ውሃ ፈውሸዋለሁ፤ ከእንግዲህ ወዲያ ለሞት ምክንያት አይሆንም፤ ምድሪቱንም ፍሬ እንዳትሰጥ አያደርጋትም’ አለ።” 22ኤልሳዕ እንደ ተናገረውም ውሃው እስከ ዛሬ ድረስ የተፈወሰ ነው።

በኤልሳዕ ላይ ተፌዘበት

23ኤልሳዕም ከዚያ ተነሥቶ ወደ ቤቴል ወጣ፤ በመንገድ ላይ ሲሄድ ሳለም ልጆች ከከተማ ወጥተው፣ “አንተ መላጣ፤ ውጣ! አንተ መላጣ ውጣ!” እያሉ አፌዙበት። 24ኤልሳዕም ዘወር ብሎ ተመለከታቸውና በእግዚአብሔር ስም ረገማቸው፤ ከዚያም ሁለት እንስት ድቦች ከዱር ወጥተው ከልጆቹ አርባ ሁለቱን ሰባበሯቸው። 25እርሱም ወደ ቀርሜሎስ ተራራ ሄደ፤ ከዚያም ወደ ሰማርያ ተመለሰ።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

列王纪下 2:1-25

以利亚被接到天上

1耶和华用旋风接以利亚升天之前,以利亚以利沙正在离开吉甲的路上。 2以利亚以利沙说:“你留在这里吧,耶和华吩咐我去伯特利。”以利沙说:“我凭永活的耶和华和你的性命起誓,我决不离开你。”于是二人前往伯特利3伯特利的众先知出来见以利沙,问他:“你知道耶和华今天要接走你师傅吗?”他说:“我知道,请不要作声。”

4以利亚以利沙说:“你留在这里吧,耶和华差遣我去耶利哥。”以利沙说:“我凭永活的耶和华和你的性命起誓,我决不离开你。”于是二人前往耶利哥5耶利哥的众先知来见以利沙,问他:“你知道耶和华今天要接走你师傅吗?”他说:“我知道,请不要作声。”

6以利亚以利沙说:“你留在这里吧,耶和华差遣我去约旦河。”以利沙说:“我凭永活的耶和华和你的性命起誓,我决不离开你。”于是二人继续前行。 7先知中有五十人跟他们来到约旦河,远远地站着,他们二人则站在河边。 8以利亚脱下外衣卷起来,用它击打河水,水立即左右分开,二人脚踏干地而过。

9到对岸后,以利亚以利沙说:“在我被接走之前,你要我为你做什么?”以利沙说:“请将你的灵加倍地给我。” 10以利亚说:“这是个很难的要求。不过,我被接走的时候,如果你看得见我,就可以得到,否则就得不到。” 11他们边走边谈,忽然有火马拉的火车把他们二人隔开,以利亚乘着旋风升上了天。 12以利沙见此情景,便喊道:“我父啊!我父啊!以色列的战车和骑兵啊!”以利沙以利亚消失在天空中,就悲伤地把自己的衣服撕成两半。

13他拿起以利亚身上掉下来的外衣,回到约旦河边, 14用它击打河水,说:“以利亚的上帝耶和华在哪里呢?”河水就左右分开,以利沙便过了河。

15耶利哥的先知们从远处看见他,就说:“以利亚的灵降在以利沙身上了。”他们就上前迎接,俯伏在他面前, 16说:“仆人们这里有五十个壮士,请让他们去寻找你师傅吧,或许耶和华的灵把他放在某座山上或某个山谷里了。”以利沙说:“你们不要派人去找了。” 17他们再三恳求,以利沙难以推辞,就让他们派人去了。他们派去了五十人,找了三天也没有找到。 18他们回来的时候,以利沙仍在耶利哥。他对他们说:“我不是早就告诉你们不要去吗?”

以利沙行神迹

19耶利哥城的人对以利沙说:“我主,你看这城地势很好,只是水不好,地里长不出庄稼。” 20以利沙说:“拿一个新碗装些盐给我。”他们就去照办。 21以利沙走到水源那里,把盐倒在水中说:“耶和华说,‘我洁净了这水,从此它不会再使人死亡,也不会再使土地贫瘠。’” 22果然如以利沙所说,那里的水变好了,直到如今。

23以利沙从那里去伯特利,正在赶路的时候,从城里出来一群少年讥笑他说:“秃头,上去吧!秃头,上去吧!” 24以利沙转身看着他们,奉耶和华的名咒诅他们。林中随即走出来两只母熊,咬死了其中的四十二个少年。 25以利沙伯特利上了迦密山,又从迦密山回到撒玛利亚