2 ነገሥት 19 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

2 ነገሥት 19:1-37

ኢየሩሳሌም ከጠላት እጅ እንደምትድን አስቀድሞ መነገሩ

19፥1-13 ተጓ ምብ – ኢሳ 37፥1-13

1ንጉሥ ሕዝቅያስ ይህን ሲሰማ ልብሱን ቀደደ፤ ማቅ ለብሶም ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ገባ። 2ከዚያም የቤተ መንግሥቱን አዛዥ ኤልያቄምን፣ ጸሓፊውን ሳምናስንና ዋና ዋናዎቹን ካህናት ማቅ ለብሰው ወደ አሞጽ ልጅ ወደ ነቢዩ ኢሳይያስ እንዲሄዱ ሁሉንም ላካቸው። 3እነርሱም እንዲህ አሉት፤ “ሕዝቅያስ የሚለው ይህ ነው፤ ‘እንግዲህ ይህች ዕለት የመከራ፣ የዘለፋና የውርደት ቀን ናት፤ ይህችም ቀን ልጆች ሊወለዱ ምጥ እንዳፋፋመበት፣ ነገር ግን ለመገላገል ዐቅም እንደታጣበት ሰዓት ናት። 4ሕያው እግዚአብሔርን ያንቋሽሽ ዘንድ በጌታው በአሦር ንጉሥ የተላከውን የጦር አዛዡን ቃል ሁሉ እግዚአብሔር አምላክህ ሰምቶ ይሆናልና፣ ስለ ሰማውም ቃል እግዚአብሔር እንዲገሥጸው በሕይወት ስለ ተረፉት ወገኖቻችን እባክህ ጸልይ።’ ”

5የንጉሥ ሕዝቅያስ ሹማምት ወደ ኢሳይያስ በመጡ ጊዜ፣ 6ኢሳይያስ እንዲህ አላቸው፤ “ለጌታችሁ እንዲህ ብላችሁ ንገሩት፤ ‘እንግዲህ እግዚአብሔር የሚለው ይህ ነው፤ “የአሦር ንጉሥ አገልጋዮች በእኔ ላይ የወረወሯቸውን የስድብ ቃላት በመስማትህ አትፍራ። 7እነሆ፣ አንድ ዐይነት መንፈስ አሳድርበታለሁ፤ የሆነ ወሬም ሲሰማ ወደ አገሩ ይመለሳል፤ እዚያም በሰይፍ እንዲወድቅ አደርገዋለሁ።” ’ ”

8የጦር አዛዡም የአሦር ንጉሥ ለኪሶን ትቶ መሄዱን ሲሰማ ተመለሰ፤ ንጉሡንም ልብናን ሲወጋ አገኘው።

9በዚህም ጊዜ የግብፅ ንጉሥ ኢትዮጵያዊው ቲርሐቅ ሊወጋው በመገሥገሥ ላይ መሆኑን ሰናክሬም ሰማ፤ ስለዚህ ወደ ሕዝቅያስ እንደ ገና እንዲህ ሲል መልእክተኞች ላከ፤ 10“ሂዱና ለይሁዳ ንጉሥ ለሕዝቅያስ እንዲህ በሉት፤ ‘የምትመካበት አምላክ፣ “ኢየሩሳሌም በአሦር ንጉሥ እጅ አትወድቅም” በማለት እንዳያታልልህ። 11መቼም የአሦር ነገሥታት በአገሮች ሁሉ ላይ ምን እንዳደረጉ ሰምተሃል፤ ፈጽሞ አጥፍተዋቸዋል፤ ታዲያ አንተስ ከዚህ የምታመልጥ ይመስልሃልን? 12የቀድሞ አባቶቼ ያጠፏቸውን ሕዝቦች ማለትም ጎዛንን፣ ካራንን፣ ራፊስን እንዲሁም በተላሳር የነበሩትን የዔድንን ሰዎች አማልክታቸው አድነዋቸዋልን? 13ለመሆኑ የሐማትና የአርፋድ ነገሥታት የት አሉ? የሴፈርዋይም ከተማ ንጉሥስ የት አለ? ደግሞስ የሄና ወይም የዒዋ ነገሥታት የት አሉ?’ ”

የሕዝቅያስ ጸሎት

19፥14-19 ተጓ ምብ – ኢሳ 37፥14-20

14ሕዝቅያስም ደብዳቤውን ከመልእክተኞቹ ተቀብሎ አነበበው፤ ከዚያም ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ወጥቶ ደብዳቤውን በእግዚአብሔር ፊት ዘረጋው። 15ከዚያም ሕዝቅያስ እንዲህ ሲል ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፤ “በኪሩቤል ላይ በዙፋንህ የተቀመጥህ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፤ በምድር ነገሥታት ሁሉ ላይ አምላክ አንተ ብቻ ነህ፤ ሰማይንና ምድርን የፈጠርህም አንተ ነህ። 16እግዚአብሔር ሆይ፤ አሁንም ጆሮህን አዘንብልና ስማ፤ እግዚአብሔር ሆይ፤ ዐይንህንም ክፈትና እይ፤ ሰናክሬም ሕያው እግዚአብሔርን ይሰድብ ዘንድ የላከውንም ቃል አድምጥ።

17እግዚአብሔር ሆይ፤ የአሦር ነገሥታት እነዚህን አሕዛብንና ምድራቸውን በርግጥ አጥፍተዋል። 18አማልክታቸውን በእሳት ውስጥ ጥለው አቃጥለዋቸዋል፤ በሰው እጅ የተሠሩ ዕንጨትና ድንጋይ ብቻ እንጂ አማልክት አልነበሩምና። 19አሁንም እግዚአብሔር አምላካችን ሆይ፤ የምድር መንግሥታት ሁሉ እግዚአብሔር አንተ ብቻ አምላክ መሆንህን እንዲያውቁ፣ ከእጁ አድነን።”

ኢሳይያስ ስለ ሰናክሬም መውደቅ ትንቢት ተናገረ

19፥20-37 ተጓ ምብ – ኢሳ 37፥21-38

19፥35-37 ተጓ ምብ – 2ዜና 32፥20-21

20ከዚያም የአሞጽ ልጅ ኢሳይያስ ወደ ሕዝቅያስ እንዲህ ሲል መልእክት ላከ፤ “የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር የሚለው ይህ ነው፤ ‘በአሦር ንጉሥ በሰናክሬም ላይ ወደ እኔ ያቀረብኸውን ልመና ሰምቻለሁ’ 21እንግዲህ እግዚአብሔር በእርሱ ላይ የተናገረው ቃል ይህ ነው፤

“ ‘ድንግሊቱ የጽዮን ልጅ፣

ትንቅሃለች፤ ታቃልልሃለችም፤

የኢየሩሳሌም ልጅ፣

አንተ በላይዋ ስትበርር ራሷን ትነቀንቅብሃለች።

22ለመሆኑ የሰደብኸውና ያቃለልኸው ማንን ነው?

ድምፅህንስ ከፍ ያደረግኸው?

ዐይንህንስ በኵራት ያነሣኸው በማን ላይ ነው?

በእስራኤል ቅዱስ ላይ ነው እንዴ?

23በመልእክተኞችህ አማካይነት፣

በአምላክ ላይ የስድብ መዓት አውርደሃል፤

እንዲህም ብለሃል፤

“በብዙ ሠረገሎቼ፣

የተራሮቹን ከፍታ፣

የሊባኖስንም የመጨረሻ ጫፍ ወጥቻለሁ፤

ረጃጅም ዝግባዎቹን፣

ምርጥ የሆኑ ጥዶቹንም ቈርጫለሁ፤

ወደ ሩቅ ዳርቻዎቹ፣

ወደ ውብ ደኖቹም ደርሻለሁ።

24በሌሎች አገሮችም የውሃ ጕድጓዶች ቈፍሬአለሁ፤

በዚያም ውሃ ጠጥቻለሁ፤

በእግሬ ጫማዎችም፣

የግብፅን ምንጮች ሁሉ ረግጬ አድርቄአለሁ።”

25“ ‘ከብዙ ጊዜ በፊት፣

ይህን እኔ እንዳደረግሁት አልሰማህም ነበርን?

ዕቅዱን ገና ድሮ አውጥቼ፣

አሁን ግን እንዲፈጸም አደረግሁት፤

ይህም የተመሸጉትን ከተሞች፣

አንተ የድንጋይ ክምር ማድረግህ ነው።

26የሚኖሩባቸውም ሰዎች ኀይላቸው ተሟጥጦ ዐልቋል፤

ደንግጠውም የኀፍረት ማቅ ለብሰዋል፤

ሜዳ ላይ እንደ በቀለ ተክል፣

ገና እንዳልጠነከረ የቡቃያ ሥር፣

በቤት ጣራ ላይ በቅሎ፣

ገና ሳያድግ እንደ ጠወለገ ሣርም ሆነዋል።

27“ ‘የት እንደምትቀመጥ፣

መቼ መጥተህ መቼ እንደምትሄድ፣

በእኔም ላይ የተቈጣኸውን ቍጣ ዐውቃለሁ።

28በእኔ ላይ በመቈጣትህ፣

ንቀትህም ወደ ጆሮዬ ስለ ደረሰ፣

ስናጋዬን በአፍንጫህ አደርጋለሁ፤

ልጓሜን በአፍህ አስገባለሁ፤

በመጣህበትም መንገድ

እንድትመለስ አደርጋለሁ።’

29“ሕዝቅያስ ሆይ፤ ምልክቱ ይህ ነው፤

“በዚህ ዓመት በገዛ እጁ የበቀለውን፣

በሚመጣው ዓመት ደግሞ የገቦውን እህል ትበላላችሁ፤

በሦስተኛው ዓመት ግን ትዘራላችሁ፤ ታጭዳላችሁ፤

ወይንም ትተክላላችሁ፤ ፍሬውንም ትበላላችሁ።

30አሁንም ከዳዊት ቤት የተረፉት፣

ሥራቸውን ወደ ታች ይሰድዳሉ፤ ወደ ላይም ፍሬ ያፈራሉ።

31ከኢየሩሳሌም በሕይወት የተረፉት፣

ከጽዮን ተራራም ከሞት ያመለጡት ይወጣሉና።

የእግዚአብሔር ቅናት ይህን ታደርጋለች።

32“እንግዲህ እግዚአብሔር ስለ አሦር ንጉሥ የሚለው ይህ ነው፤

“ ‘ወደዚህች ከተማ ፈጽሞ አይገባም፤

አንዲትም ፍላጻ አይወረውርባትም፤

ጋሻ አንግቦ ወደ እርሷ አይቀርብም፤

በዐፈርም ቍልል አይከብባትም።

33በመጣበት መንገድ ተመልሶ ይሄዳል፤

ተመልሶ ይሄዳታል እንጂ ወደዚህች ከተማ ፈጽሞ አይገባም’

ይላል እግዚአብሔር

34‘ስለ ራሴና ስለ ባሪያዬም ስለ ዳዊት ስል፣

ይህችን ከተማ አድናት ዘንድ እጋርዳታለሁ።’ ”

35በዚያችም ሌሊት የእግዚአብሔር መልአክ ወጥቶ ከአሦራውያን ሰፈር መቶ ሰማንያ አምስት ሺሕ ሰው ገደለ። በማግስቱም ሰዎቹ ሲነቁ፣ ቦታው ሬሳ በሬሳ ሆኖ ተገኘ። 36የአሦር ንጉሥ ሰናክሬም ከዚያ ተነሥቶ ሄደ፤ ወደ ነነዌም ተመልሶ በዚያ ተቀመጠ።

37አንድ ቀንም ናሳራክ በተባለው አምላኩ ቤተ ጣዖት ገብቶ በመስገድ ላይ ሳለ፣ አድራሜሌክና ሳራሳር የተባሉ ልጆቹ በሰይፍ ገደሉት፤ ከዚያም አምልጠው ወደ አራራት ሸሹ። ልጁ አስራዶንም በእግሩ ተተክቶ ነገሠ።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

列王紀下 19:1-37

希西迦向以賽亞求助

1希西迦王聽了就撕裂衣服,披上麻衣,進入耶和華的殿。 2他派身披麻衣的宮廷總管以利亞敬、書記舍伯那和祭司中的長者去見亞摩斯的兒子以賽亞先知, 3對他說:「希西迦說,『今天是遭難、蒙羞、受辱的日子,就像嬰兒要出生,產婦卻無力生產一樣。 4亞述王派他的將軍來辱罵永活的上帝,也許你的上帝耶和華聽見那些話,就會懲罰他。所以,請你為我們這些剩下的人禱告。』」 5希西迦王的臣僕說完這些話後, 6以賽亞對他們說:「告訴你們主人,耶和華這樣說,『你不要因亞述王的僕人那些褻瀆我的話而害怕。 7我必驚動19·7 驚動」希伯來文是「使靈進入」。亞述王的心,讓他聽見一些風聲後便返回本國,在那裡死於刀下。』」

希西迦向上帝禱告

8亞述的將軍聽說亞述王已離開拉吉,便回去見王,發現王在攻打立拿9亞述王聽說古實特哈加正前來攻打他,便再次派使者去對希西迦說: 10「不要讓你所倚靠的上帝愚弄你,說什麼耶路撒冷必不會被亞述王攻陷。 11你肯定聽過亞述諸王掃滅列國的事,難道你能倖免嗎? 12我先祖毀滅了歌散哈蘭利色提·拉撒伊甸人,這些國家的神明救得了他們嗎? 13哈馬王、亞珥拔王、西法瓦音城的王、希拿王和以瓦王如今在哪裡呢?」

14希西迦從使者手中接過信,讀完後走進耶和華的殿,在耶和華面前展開信, 15禱告說:「坐在二基路伯天使之上、以色列的上帝耶和華啊,唯有你是天下萬國的上帝,你創造了天地。 16耶和華啊,求你側耳垂聽!耶和華啊,求你睜眼察看!求你聽聽西拿基立派使者來辱罵永活上帝的話。 17耶和華啊,亞述諸王確實掃滅列國,使其土地荒涼, 18把列國的神像丟在火中。因為那些神像只是人用木頭石頭製造的,根本不是神。 19我們的上帝耶和華啊,現在求你從亞述王手中拯救我們,讓天下萬國都知道唯有你是耶和華。」

以賽亞給希西迦的信息

20亞摩斯的兒子以賽亞派人告訴希西迦:「以色列的上帝耶和華說,『我已經聽見你關於亞述西拿基立的禱告。 21以下是耶和華對他的判語,

錫安的居民藐視你,嘲笑你;

耶路撒冷的居民朝你逃竄的背影搖頭。

22你在侮辱、褻瀆誰呢?

你不放在眼裡、

高聲罵的是誰呢?

以色列的聖者!

23你藉你的使者辱罵主,

你說你率領許多戰車上到群山之巔,

上到黎巴嫩的巔峰,

砍下最高的香柏樹和上好的松樹,

征服最高的山和最美的樹林。

24你自誇已在外邦之地挖井取水,

已用腳掌踏乾埃及的河流。

25『難道你不知道這是我在太初所定、

在亙古就籌畫好的嗎?

如今我實現了所定的計劃——

藉著你使堅城淪為廢墟。

26城中的居民軟弱無力,

驚慌失措,羞愧難當,

脆弱如野草和菜蔬,

又像還未長大就被曬焦的房頂草。

27『你起你坐,你出你進,

你向我發怒,我都知道。

28因為你向我發怒,

你狂傲的話達到了我耳中,

我要用鉤子鉤住你的鼻子,

把嚼環放在你嘴裡,

使你原路返回。』

29希西迦啊,我要賜給你們一個兆頭,你們今年要吃野生的,明年也要吃自然生長的,後年要播種收割,栽種葡萄園,吃園中的果子。 30猶大的倖存者要再次向下扎根,向上結果。 31因為將有餘民從耶路撒冷出來,有倖存者從錫安山出來。耶和華必熱切地成就這事。

32「至於亞述王,耶和華說,『他必不能進這城或向這裡射一箭,必不能手持盾牌兵臨城下或修築攻城的高臺。 33他從哪條路來,也將從哪條路回去,他必進不了這城。這是耶和華說的。 34我必為自己和我僕人大衛而保護、拯救這城。』」

35當晚,耶和華的天使到亞述營中殺了十八萬五千人。人們清早起來,發現到處是屍體。 36亞述西拿基立便拔營回國,住在尼尼微37一天,亞述王在他的神明尼斯洛的廟裡祭拜時,他的兩個兒子亞得米勒沙利色用刀殺了他,逃往亞拉臘。他的另一個兒子以撒哈頓繼位。