2 ነገሥት 16 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

2 ነገሥት 16:1-20

የይሁዳ ንጉሥ አካዝ

16፥1-20 ተጓ ምብ – 2ዜና 28፥1-27

1የሮሜልዩ ልጅ ፋቁሔ በነገሠ በዐሥራ ሰባተኛው ዓመት፣ የይሁዳ ንጉሥ፣ የኢዮአታም ልጅ አካዝ ነገሠ። 2አካዝ ሲነግሥ ዕድሜው ሃያ ዓመት ነበር፤ በኢየሩሳሌም ተቀምጦም ዐሥራ ስድስት ዓመት ገዛ። አባቱ ዳዊት ያደረገውን መልካም ነገር በአምላኩ በእግዚአብሔር ፊት አላደረገም። 3እርሱም የእስራኤልን ነገሥታት መንገድ ተከተለ፤ ይልቁንም እግዚአብሔር ከእስራኤላውያን ፊት ያሳደዳቸውን የአሕዛብን ርኩሰት ተከትሎ፣ ልጁን በእሳት የሚቃጠል መሥዋዕት አድርጎ አቀረበ።16፥3 ወይም፣ ልጁን ገደለ 4እንዲሁም ኰረብታ ላይ ባሉ ማምለኪያ ስፍራዎች፣ በኰረብታ ዐናቶችና ቅጠሉ በተንሰራፋው ዛፍ ሥር ሁሉ ሠዋ፤ ዕጣንም አጤሰ።

5የሶርያ ንጉሥ ረአሶንና የእስራኤል ንጉሥ የሮሜልዩ ልጅ ፋቁሔ ኢየሩሳሌምን ለመውጋትና አካዝን ለመክበብ ወጡ፤ ይሁን እንጂ ሊያሸንፉት አልቻሉም። 6በዚያን ጊዜም የሶርያ ንጉሥ ረአሶን የይሁዳን ሰዎች አሳድዶ፣ ኤላትን ወደ ሶርያ ግዛት መለሰ፤ ከዚያም ኤዶማውያን ወደ ኤላት መጥተው እስከ ዛሬ በዚያ ይኖራሉ።

7ከዚህ የተነሣም አካዝ፣ ወደ አሦር ንጉሥ ወደ ቴልጌልቴልፌልሶር፣ “እኔ አገልጋይህም ልጅህም ነኝ፤ ስለዚህ መጥተህ ከሚወጉኝ ከሶርያ ንጉሥና ከእስራኤል ንጉሥ እጅ አድነኝ” ሲል መልእክተኞች ላከበት። 8አካዝም በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስና በቤተ መንግሥቱ ግምጃ ቤቶች የሚገኘውን ብርና ወርቅ አውጥቶ ለአሦር ንጉሥ ገጸ በረከት ላከለት። 9የአሦር ንጉሥም፣ የአካዝን ልመና በመቀበል፤ ደማስቆን አጥቅቶ ያዛት፤ ሕዝቧን ማርኮ ወደ ቂር አፈለሳቸው፤ ረአሶንንም ገደለው።

10ከዚያም ንጉሥ አካዝ የአሦርን ንጉሥ ቴልጌልቴልፌልሶርን ለመገናኘት ወደ ደማስቆ ሄደ። በደማስቆም ያለውን መሠዊያ አይቶ፣ ንድፉን ከዝርዝር ጥናቱ ጋር ለካህኑ ለኦርያ ላከለት። 11ካህኑ ኦርያም ንጉሥ አካዝ ከደማስቆ በላከለት ዝርዝር ጥናት መሠረት መሠዊያ ሠራ፤ ንጉሡ አካዝ ከመመለሱም በፊት አጠናቀቀው። 12ንጉሡ ከደማስቆ ተመልሶ በመጣ ጊዜ፣ መሠዊያውን አየ፤ ቀርቦም በመሠዊያው ላይ ወጣ፤ 13ከዚያም የሚቃጠል መሥዋዕቱንና የእህል ቍርባኑን በመሠዊያው ላይ አቀረበ፤ የመጠጥ ቍርባኑን አፈሰሰ፤ የኅብረት መሥዋዕቱንም16፥13 በትውፊት፣ የሰላም መሥዋዕት ደም በመሠዊያው ላይ ረጨ። 14በአዲሱ መሠዊያና በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ መካከል፣ በእግዚአብሔር ፊት ቆሞ የነበረውን የናስ መሠዊያ፣ ከቦታው አስነሥቶ ከአዲሱ መሠዊያ በስተ ሰሜን በኩል አኖረው።

15ከዚያም ንጉሥ አካዝ፣ ካህኑን ኦርያን እንዲህ ሲል አዘዘው፤ “በዚህ በትልቁ አዲስ መሠዊያ ላይ የጧቱን የሚቃጠል መሥዋዕትና የማታውን የእህል ቍርባን፣ የንጉሡን የሚቃጠል መሥዋዕትና የእህሉን ቍርባን እንዲሁም የመላውን የአገሪቱን ሕዝብ የሚቃጠል መሥዋዕት፣ የእህልና የመጠጥ ቍርባናቸውን አቅርብ፤ የሚቃጠለውን መሥዋዕት ደምና የሌላውን መሥዋዕት ደም ሁሉ በመሠዊያው ላይ እርጨው፤ የናሱ መሠዊያ ግን እኔ መመሪያ ለመጠየቅ የምጠቀምበት ይሆናል።” 16ካህኑ ኦርያም ንጉሡ አካዝ እንዳዘዘው ሁሉ እንዲሁ አደረገ።

17ንጉሡ አካዝም የጐንና የጐን ሳንቃዎቹን ነቅሎ ወሰደ፤ በተንቀሳቃሹ መቆሚያ ላይ ያሉትን የመታጠቢያ ሳሕኖች አስወገደ። የውሃ ማጠራቀሚያውን ክብ ገንዳ ከታች ተሸክመው ከያዙት ከዐሥራ ሁለቱ የናስ ቅርጽ ኮርማዎች ላይ አውርዶ በጠፍጣፋ ድንጋይ ላይ አስቀመጠው። 18የአሦርንም ንጉሥ ለማስደሰት ሲል፣ በዕለተ ሰንበት ንጉሣዊ ዙፋን16፥18 የሰብዓ ሊቃናት መሥዋዕት ትርጕም፣ የዙፋኑ ሰሌዳ ይላል። እንዲዘረጋበት በቤተ መቅደሱ ውስጥ የተሠራውን ከፍ ያለ ስፍራና ነገሥታቱ ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ የሚገቡበትን በውጭ ያለውን መግቢያ አነሣ።

19በአካዝ ዘመነ መንግሥት የተከናወነው ሌላው ሥራ፣ የፈጸመውም ሁሉ በይሁዳ ነገሥታት ታሪክ ተጽፎ የሚገኝ አይደለምን? 20አካዝም ከአባቶቹ ጋር አንቀላፋ፤ ከእነርሱ ጋር በዳዊት ከተማ ተቀበረ። ልጁ ሕዝቅያስም በእግሩ ተተክቶ ነገሠ።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

列王紀下 16:1-20

亞哈斯做猶大王

1利瑪利的兒子比加執政第十七年,猶大約坦的兒子亞哈斯登基。 2他二十歲登基,在耶路撒冷統治十六年。他沒有效法他祖先大衛做耶和華視為正的事, 3反而步以色列諸王的後塵,效法耶和華在以色列人面前趕走的外族人的可憎行徑,把自己的兒子焚燒獻作祭物。 4他在邱壇、山岡和綠樹下獻祭燒香。

5亞蘭利汛利瑪利的兒子以色列比加前來攻打耶路撒冷,圍住亞哈斯,但屢攻不下。 6當時,亞蘭利汛收復以拉他,趕走城內的猶大人。亞蘭人至今居住在那裡。 7亞哈斯差遣使者去見亞述提革拉·毗列色,對他說:「我是你的僕人、你的兒子,現在亞蘭王和以色列王攻打我,求你從他們手中拯救我。」 8亞哈斯把耶和華殿裡和王宮庫房裡的金銀送給亞述王。 9亞述王答應了他,起兵攻陷大馬士革,殺了利汛,把城中的居民擄到吉珥

10亞哈斯王在大馬士革亞述提革拉·毗列色的時候,看到一座壇,便派人將壇的模型和詳細的製造方法送到烏利亞祭司那裡。 11烏利亞祭司按照送來的模型,在亞哈斯王返回之前建造了一座壇。 12王從大馬士革回來,看見那座壇,就到上面獻祭。 13他在上面獻上燔祭、素祭和奠祭,又將平安祭祭牲的血灑在壇上。 14他把獻給耶和華的銅壇從耶和華的殿前搬到新壇的北邊,銅壇原來放在殿和新壇之間。 15他吩咐烏利亞祭司:「要在這座大壇上獻早晨的燔祭、晚上的素祭,王的燔祭、素祭,國中民眾的燔祭、素祭和奠祭,燔祭牲和平安祭牲的血也要灑在上面,但銅壇要供我個人求問之用。」 16烏利亞祭司遵命而行。

17亞哈斯王拆掉盆座的鑲板,搬走盆,將銅海從銅牛背上搬下來,放在鋪石的地上。 18為了亞述王,他挪走耶和華殿裡為安息日而蓋的走廊,封閉了王從外面進耶和華殿的入口。

19亞哈斯其他的事都記在猶大的列王史上。 20亞哈斯與祖先同眠後,葬在大衛城他的祖墳裡。他兒子希西迦繼位。