2 ነገሥት 1 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

2 ነገሥት 1:1-18

የእግዚአብሔር ፍርድ በአካዝያስ ላይ

1አክዓብ ከሞተ በኋላ ሞዓብ በእስራኤል ላይ ዐመፀ። 2በዚህ ጊዜ አካዝያስ በሰማርያ ካለው እልፍኝ ሰገነቱ ላይ ሳለ፣ ከዐይነ ርግቡ ሾልኮ ወድቆ ነበርና ታመመ፤ ስለዚህ፣ “ሄዳችሁ ከዚህ ሕመም እድን እንደ ሆነ የአቃሮንን አምላክ ብዔልዜቡልን ጠይቁ” ሲል መልእክተኞች ላከ።

3የእግዚአብሔር መልአክ ግን ቴስብያዊውን ኤልያስን እንዲህ አለው፤ “ተነሥተህ የሰማርያን ንጉሥ መልእክተኞች ለመገናኘት ውጣና፣ ‘የአቃሮንን አምላክ ብዔልዜቡልን ለመጠየቅ የምትሄዱ በእስራኤል አምላክ ስለሌለ ነውን?’ ብለህ ጠይቃቸው። 4ስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ከተኛህበት ዐልጋ አትነሣም፤ በርግጥ ትሞታለህ።’ ” ከዚያም ኤልያስ ሄደ።

5መልእክተኞቹ ወደ ንጉሡ ሲመለሱ እርሱም፣ “ለምን ተመልሳችሁ መጣችሁ?” ሲል ጠየቃቸው።

6እነርሱም እንዲህ ሲሉ መለሱለት፤ “አንድ ሰው ሊገናኘን መጥቶ፣ ‘ወደ ላካችሁ ንጉሥ ተመልሳችሁ ሂዱና፣ “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ የአቃሮንን አምላክ ብዔልዜቡልን ለመጠየቅ ሰዎች የምትልከው በእስራኤል አምላክ ስለሌለ ነውን? ስለዚህ ከተኛህበት ዐልጋ አትነሣም፤ በርግጥ ትሞታለህ።” ’ ”

7ንጉሡም፣ “ለመሆኑ ሊገናኛችሁ መጥቶ እንዲህ ያላችሁ ሰው እንዴት ያለ ነው?” ሲል ጠየቃቸው።

8እነርሱም “ሰውየው ጠጕራም ልብስ የለበሰ ነው፤ በወገቡም ላይ ጠፍር ታጥቋል” አሉት።

ንጉሡም፣ “ዐወቅሁት፤ ቴስብያዊው ኤልያስ ነው” አላቸው።

9ከዚያም ንጉሡ አንድ የአምሳ አለቃ ከአምሳ ወታደሮቹ ጋር ወደ ኤልያስ ላከ። የአምሳ አለቃውም ኤልያስ ወደ ተቀመጠበት ኰረብታ ጫፍ ወጥቶ፣ “አንተ የእግዚአብሔር ሰው፤ ንጉሡ፣ ‘ና ውረድ’ ይልሃል” አለው።

10ኤልያስም መልሶ የአምሳ አለቃውን፣ “እኔ የእግዚአብሔር ሰው ከሆንሁ፣ እሳት ከሰማይ ወርዳ፣ አንተንና አምሳውን ሰዎችህን ትብላ!” አለው። ከዚያም እሳት ከሰማይ ወርዳ የአምሳ አለቃውንና ሰዎቹን ፈጽማ በላች።

11እንደ ገናም ንጉሡ ሌላ የአምሳ አለቃ ከአምሳ ሰዎቹ ጋር ላከ፤ የአምሳ አለቃውም፣ “አንተ የእግዚአብሔር ሰው፤ ንጉሡ፣ ‘አሁኑኑ ና ውረድ’ ይልሃል” አለው።

12ኤልያስም መልሶ፣ “እኔ የእግዚአብሔር ሰው ከሆንሁ እሳት ከሰማይ ወርዳ አንተንና ሃምሳውን ሰዎችህን ትብላ!” አለው፤ ከዚያም እሳት ከሰማይ ወርዳ እርሱንና ሰዎቹን ፈጽማ በላች።

13ስለዚህም ንጉሡ ሦስተኛውን የአምሳ አለቃ ከአምሳ ሰዎቹ ጋር ላከ። ይህም ሦስተኛው የአምሳ አለቃ ወጥቶ፣ በኤልያስ ፊት በጕልበቱ ተንበርክኮ እንዲህ ሲል ለመነ፤ “አንተ የእግዚአብሔር ሰው፤ እባክህ የእኔና የእነዚህ የአምሳዎቹ አገልጋዮችህ ነፍስ በፊትህ የከበረች ትሁን። 14እነሆ፤ እሳት ከሰማይ ወርዳ፣ የፊተኞቹን ሁለት አምሳ አለቆችና ሰዎቻቸውን ሁሉ በላች፤ አሁን ግን ሕይወቴ በፊትህ የከበረች ትሁን።”

15የእግዚአብሔርም መልአክ ኤልያስን፣ “አብረኸው ውረድ፤ ደግሞም አትፍራው” አለው። ስለዚህ ኤልያስ ተነሣ፤ አብሮትም ወደ ንጉሡ ወረደ።

16ንጉሡንም፣ “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ለመሆኑ የአቃሮንን አምላክ ብዔልዜቡልን ስለ ራስህ ለመጠየቅ መልእክተኞች የላክኸው በእስራኤል አምላክ ስለሌለ ነውን? ይህን በማድረግህም ከተኛህበት ዐልጋ ፈጽሞ አትነሣም፤ በርግጥ ትሞታለህ’ ” ብሎ ነገረው። 17ስለዚህ አካዝያስ ኤልያስ እንደ ተናገረው እንደ እግዚአብሔር ቃል ሞተ።

አካዝያስ ወንድ ልጅ ስላልነበረው፣ የኢዮሣፍጥ ልጅ ኢዮራም በይሁዳ በነገሠ በሁለተኛው ዓመት ወንድሙ ኢዮራም በእግሩ ተተክቶ ነገሠ። 18ሌላው አካዝያስ በዘመኑ ያከናወናቸውና የፈጸማቸው ሥራዎች ሁሉ በእስራኤል ነገሥታት ታሪክ የተጻፉ አይደለምን?

New International Reader’s Version

2 Kings 1:1-18

The Lord Judges Ahaziah

1After King Ahab died, Moab refused to remain under Israel’s control. 2Ahaziah had fallen through the window of his upstairs room in Samaria. He had hurt himself. So he sent messengers to ask the god named Baal-Zebub for advice. Baal-Zebub was the god of the city of Ekron. Ahaziah said to the messengers, “Go and ask Baal-Zebub whether I will get well again.”

3But the angel of the Lord spoke to Elijah, who was from Tishbe. The angel said, “Go up to see the messengers of Ahaziah, the king of Samaria. Tell them, ‘You are on your way to ask Baal-Zebub for advice. He is the god of Ekron. Are you going there to pray to that god? Do you think there is no God in Israel?’ 4The Lord says to Ahaziah, ‘You will never leave the bed you are lying on. You can be sure that you will die!’ ” So Elijah went to see the messengers.

5They returned to the king. He asked them, “Why have you come back?”

6“A man met us on our way there,” they replied. “He said to us, ‘Go back to the king who sent you. Tell him, “The Lord says, ‘You are sending messengers to ask Baal-Zebub for advice. He is the god of Ekron. Are you going there to pray to that god? Do you think there is no God in Israel? You will never leave the bed you are lying on. You can be sure that you will die!’ ” ’ ”

7The king asked the messengers, “What kind of man came to see you? Who told you these things?”

8They replied, “He was wearing clothes made out of hair. He had a leather belt around his waist.”

The king said, “That was Elijah from Tishbe.”

9Then Ahaziah sent a captain to Elijah. The captain had his group of 50 fighting men with him. Elijah was sitting on top of a hill. The captain went up to him. He said to Elijah, “Man of God, the king says, ‘Come down!’ ”

10Elijah answered the captain, “If I’m really a man of God, may fire come down from heaven! May it burn up you and your 50 men!” Then fire came down from heaven. It burned up the captain and his men.

11After that happened, the king sent another captain to Elijah. The captain had his 50 men with him. He said to Elijah, “Man of God, the king says, ‘Come down at once!’ ”

12Elijah replied, “If I’m really a man of God, may fire come down from heaven! May it burn up you and your 50 men!” Then the fire of God came down from heaven. It burned up the captain and his 50 men.

13So the king sent a third captain with his 50 men. The captain went up to Elijah. He fell on his knees in front of him. “Man of God,” he begged, “please have respect for my life! Please have respect for the lives of these 50 men! 14Fire has come down from heaven. It has burned up the first two captains and all their men. But please have respect for my life!”

15The angel of the Lord said to Elijah, “Go down along with him. Don’t be afraid of him.” So Elijah got up and went down to the king with the captain.

16Elijah told the king, “The Lord says, ‘You have sent messengers to ask Baal-Zebub for advice. He is the god of Ekron. Did you go there to pray to that god for advice? Do you think there is no God in Israel? You will never leave the bed you are lying on. You can be sure that you will die!’ ” 17So King Ahaziah died. It happened just as the Lord had said it would. He had spoken that message through Elijah.

Ahaziah didn’t have any sons. So Joram, his younger brother, became the next king after him. It was the second year of Jehoram, the king of Judah. Jehoram was the son of Jehoshaphat. 18All the other events of Ahaziah’s rule are written down. Everything he did is written in the official records of the kings of Israel.