2 ተሰሎንቄ 3 – NASV & HHH

New Amharic Standard Version

2 ተሰሎንቄ 3:1-18

ለጸሎት የቀረበ ጥያቄ

1በቀረውስ ወንድሞች ሆይ፤ በእናንተ ዘንድ እንደ ሆነው የጌታ ቃል በፍጥነት እንዲሠራጭና እንዲከበር ለእኛ ጸልዩልን፤ 2ደግሞም ሰው ሁሉ እምነት ያለው ስለማይሆን ከዐመፀኞችና ከክፉ ሰዎች እንድንድን ጸልዩልን። 3ጌታ ግን ታማኝ ነው፤ እርሱም ያበረታችኋል፤ ከክፉውም ይጠብቃችኋል። 4እኛ ያዘዝናችሁን አሁን አደረጋችሁ፤ ወደ ፊትም እንደምታደርጉ በጌታ እንታመናለን። 5ጌታ ልባችሁን ወደ እግዚአብሔር ፍቅርና ወደ ክርስቶስ ጽናት ይምራው።

ሥራ መፍታት እንደማይገባ የተሰጠ ማስጠንቀቂያ

6ወንድሞች ሆይ፤ ሥራ ፈት ከሆነና ከእኛ በተቀበላችሁት ትምህርት3፥6 ወይም ወግ መሠረት ከማይኖር ወንድም እንድትርቁ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እናዝዛችኋለን፤ 7የእኛን ምሳሌ እንዴት መከተል እንደሚገባችሁ እናንተ ራሳችሁ ታውቃላችሁና። ከእናንተ ጋር በነበርንበት ጊዜ ሥራ ፈቶች አልነበርንም፤ 8ደግሞም የማንንም እንጀራ በነጻ አልበላንም፤ ነገር ግን ከእናንተ በአንዳችሁም ላይ ሸክም እንዳንሆን ሌሊትና ቀን እንደክምና እንሠራ ነበር፤ 9ይህን ያደረግነው ምሳሌነታችንን እንድትከተሉ ብለን እንጂ የሚያስፈልገንን ነገር ከእናንተ ለማግኘት ሥልጣን ሳይኖረን ቀርቶ አይደለም። 10ከእናንተ ጋር በነበርንበት ጊዜ፣ “ሊሠራ የማይወድድ አይብላ” ብለን ይህን ትእዛዝ ሰጥተናችሁ ነበርና። 11ከእናንተ አንዳንዶች ሥራ ፈቶች እንደ ሆኑ ሰምተናል፤ እነርሱም ያለ ሥራ እየዞሩ በሰው ጕዳይ ጣልቃ የሚገቡ ናቸው። 12እንደዚህ ያሉ ሰዎች ተግተው ሥራቸውን እንዲሠሩና እንጀራቸውን እንዲበሉ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እናዝዛቸዋለን፤ እንመክራቸዋለንም። 13እናንተ ግን ወንድሞች ሆይ፤ መልካም ሥራን ከመሥራት ከቶ አትታክቱ።

14በዚህ መልእክት ላይ ላለው ቃላችን የማይታዘዝ ማንም ቢኖር፣ እንደዚህ ያለውን ሰው በጥንቃቄ ተከታተሉት፤ በሥራውም እንዲያፍር ከእርሱ ጋር አትተባበሩ። 15ሆኖም እንደ ወንድም ገሥጹት እንጂ እንደ ጠላት አትቍጠሩት።

የመጨረሻ ሰላምታ

16የሰላም ጌታ ራሱ በሁሉም ነገር ዘወትር ሰላም ይስጣችሁ። ጌታ ከሁላችሁ ጋር ይሁን።

17ይህን ሰላምታ በገዛ እጄ የጻፍሁት እኔ ጳውሎስ ነኝ፤ የመልእክቶቼም ሁሉ መለያ ይህ ነው፤ አጻጻፌም እንደዚህ ነው።

18የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከሁላችሁ ጋር ይሁን።

Habrit Hakhadasha/Haderekh

אגרת פולוס השנייה אל-התסלוניקים 3:1-18

1לסיום, אחים יקרים, אנא, התפללו בעדנו. ראשית כל התפללו שבשורת ה׳ תופץ במהירות וביעילות בכל מקום, ותביא לו כבוד רב כפי שהביאה ביניכם. 2שנית, התפללו שלא ניפול בידי אנשים רשעים, שהרי לא כולם אוהבים את האדון. 3אך אתם יכולים לסמוך על האדון שיחזק וישמור אתכם מכל רע. 4האדון גם העניק לנו את הביטחון שאתם מקיימים הלכה למעשה את מה שלימדנו אתכם, ואף שתמשיכו בכך בעתיד. 5והאדון ישוע יכשיר את לבבכם להבין את משמעותה ועומקה של אהבת אלוהים וסבלנותו של המשיח.

6אחים יקרים, אנו מצווים עליכם בשם ישוע המשיח אדוננו ובסמכותו: התרחקו מכל מאמין עקשן שמסרב לקיים את ההוראות שמסרנו לכם. 7אתם יודעים היטב שעליכם להתנהג כמונו, שכן מעולם לא ראיתם אותנו סוטים מהדרך הנכונה; 8מעולם לא אכלנו בחינם – תמיד שילמנו בעד מה שקיבלנו. עבדנו קשה יומם ולילה כדי להרוויח את מחייתנו, כי לא רצינו להכביד על איש מכם. 9אל תחשבו שלא הייתה לנו הזכות לבקש מכם לספק את מזוננו – פשוט רצינו להראות לכם כיצד עליכם לעבוד לפרנסתכם.

10עוד בהיותנו אצלכם ביקשנו מכם לשמור על העיקרון: ”מי שלא יעבוד לא יאכל!“

11אך בכל זאת אנו שומעים כי יש ביניכם טפילים עצלים, המסרבים לעבוד ומבזבזים את זמנם ברכילות וחרחורי־ריב. 12אנחנו מזהירים את האנשים האלה ומצווים עליהם בשם אדוננו ישוע המשיח: לכו לעבוד והרוויחו את לחמכם בכבוד! 13ולשאר האחים אני אומר: לעולם אל תתייאשו ואל תפסיקו לעשות מעשים טובים.

14גרשו מקרבכם את מי שמסרב לשמוע לדברינו שכתובים במכתב זה, כדי שיתבייש בעצמו. 15אל תתייחסו אליו כאל אויב, אלא כאל אח תועה שיש להזהירו ולהחזירו לדרך הישר. 16ואדון השלום בעצמו יעניק לכם את שלומו בכל עת ובכל מקום. יהיה האדון עם כולכם.

17‏-18עתה אני, פולוס, מברך את כולכם בכתב־ידי, כמנהגי בסיום כל מכתבי, לאות וסימן שאני באמת הכתבתי אותם. זהו כתב ידי וזוהי חתימתי. יברך אדוננו ישוע המשיח את כולכם.