2 ተሰሎንቄ 1 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

2 ተሰሎንቄ 1:1-12

1ጳውሎስ፣ ሲላስና1፥1 ግሪኩ ሲልዋኑስ ይላል። ጢሞቴዎስ፤

በእግዚአብሔር በአባታችን በጌታም በኢየሱስ ክርስቶስ ለሆኑት፣ ለተሰሎንቄ ሰዎች ቤተ ክርስቲያን፤

2ከእግዚአብሔር አብ፣ ከጌታ ከኢየሱስ ክርስቶስም ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።

የምስጋናና የልመና ጸሎት

3ወንድሞች ሆይ፤ እምነታችሁ በየጊዜው እያደገ በመሄዱና የእርስ በርስ ፍቅራችሁም እየጨመረ በመምጣቱ፣ ስለ እናንተ እግዚአብሔርን ሁልጊዜ በሚገባ ማመስገን አለብን። 4ስለዚህ በደረሰባችሁ ስደትና መከራ ሁሉ በመጽናታችሁ፣ እኛ ራሳችን ስለ ትዕግሥታችሁና ስለ እምነታችሁ በእግዚአብሔር አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ እንመካለን።

5ይህ ሁሉ የእግዚአብሔር ፍርድ ቅን መሆኑን የሚያመለክት ነው፤ ከዚህም የተነሣ መከራን ለምትቀበሉለት ለእግዚአብሔር መንግሥት የበቃችሁ ሆናችሁ ትቈጠራላችሁ። 6እግዚአብሔር ጻድቅ በመሆኑ መከራን ለሚያመጡባችሁ መከራን ይከፍላቸዋል፤ 7መከራን ለተቀበላችሁት ለእናንተም ሆነ ለእኛ ደግሞ ዕረፍት ይሰጠናል። ይህም የሚሆነው ጌታ ኢየሱስ በሚንበለበል እሳት ከኀያላን መላእክት ጋር ከሰማይ በሚገለጥበት ጊዜ ነው። 8በዚያ ጊዜ እግዚአብሔርን የማያውቁትንና ለጌታችንም ለኢየሱስ ወንጌል የማይታዘዙትን ይበቀላል። 9እነርሱም ከጌታ ፊትና ከኀይሉ ክብር ተወግደው በዘላለም ጥፋት ይቀጣሉ፤ 10የሚቀጡትም በቅዱሳኑ ዘንድ ሊከብርና በሚያምኑበትም ሁሉ ሊገረም በሚመጣበት በዚያን ቀን ይሆናል፤ እናንተም ከሚያምኑት መካከል ናችሁ፤ ምስክርነታችንን ተቀብላችኋልና።

11ይህን እያሰብን አምላካችን ለጥሪው የበቃችሁ አድርጎ እንዲቈጥራችሁ፣ መልካም ለማድረግ ያላችሁን ምኞትና ከእምነት የሆነውን ሥራችሁን ሁሉ በኀይሉ እንዲፈጽምላችሁ ዘወትር ስለ እናንተ እንጸልያለን። 12ደግሞም እንደ አምላካችንና1፥12 ወይም እንደ አምላካችን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ መጠን የጌታችን የኢየሱስ ስም በእናንተ ዘንድ እንዲከብርና እናንተም በእርሱ እንድትከብሩ ይህን እንጸልያለን።

Thai New Contemporary Bible

2เธสะโลนิกา 1:1-12

1จดหมายฉบับนี้จากข้าพเจ้าเปาโล สิลาส1:1 หรือสิลวานัสและทิโมธี

ถึงคริสตจักรของชาวเธสะโลนิกาในพระเจ้าพระบิดาของเราและองค์พระเยซูคริสต์เจ้า

2ขอพระคุณและสันติสุขจากพระเจ้าพระบิดาและพระเยซูคริสต์เจ้ามีแก่ท่านทั้งหลาย

ขอบพระคุณและทูลขอ

3พี่น้องทั้งหลาย เราควรขอบพระคุณพระเจ้าเพราะท่านเสมอและเป็นการถูกต้องแล้วที่ทำเช่นนั้น เนื่องด้วยความเชื่อของท่านจำเริญยิ่งๆ ขึ้นและความรักที่ท่านทุกคนมีต่อกันก็เพิ่มพูนขึ้น 4ฉะนั้นในหมู่คริสตจักรต่างๆ ของพระเจ้า เราจึงอวดถึงความทรหดอดทนและความเชื่อของท่านท่ามกลางการข่มเหงและการทดลองนานัปการที่ท่านเผชิญอยู่

5ทั้งหมดนี้เป็นหลักฐานว่าการพิพากษาของพระเจ้านั้นถูกต้อง และผลก็คือท่านจะได้รับการนับว่าคู่ควรกับอาณาจักรของพระเจ้าซึ่งท่านยอมทนทุกข์เพื่ออาณาจักรนั้น 6พระเจ้าทรงยุติธรรม พระองค์จะทรงเอาความลำบากคืนสนองแก่บรรดาผู้ทำให้ท่านลำบากยากเข็ญ 7และจะทรงบรรเทาทุกข์ให้แก่ท่านที่ได้รับความลำบากและแก่เราด้วย เหตุการณ์นี้จะเกิดขึ้นเมื่อองค์พระเยซูเจ้าทรงปรากฏจากสวรรค์ในเปลวไฟเจิดจ้าพร้อมกับเหล่าทูตสวรรค์ผู้มีฤทธิ์ของพระองค์ 8พระองค์จะทรงลงโทษบรรดาผู้ที่ไม่รู้จักพระเจ้าและไม่เชื่อฟังข่าวประเสริฐขององค์พระเยซูเจ้าของเรา 9พวกเขาจะถูกลงโทษด้วยความพินาศนิรันดร์ จะถูกแยกจากเบื้องพระพักตร์องค์พระผู้เป็นเจ้า และแยกจากพระบารมีแห่งฤทธานุภาพของพระองค์ 10ในวันนั้นพระองค์จะเสด็จมาเพื่อรับพระเกียรติสิริในหมู่ประชากรของพระองค์ และเพื่อเป็นที่อัศจรรย์ใจท่ามกลางผู้เชื่อทุกคนซึ่งรวมท่านทั้งหลายด้วย เพราะท่านได้เชื่อคำพยานของเราที่กล่าวแก่ท่าน

11โดยคำนึงถึงสิ่งเหล่านี้เราจึงอธิษฐานเผื่อท่านเสมอไม่ได้ขาด ขอให้พระเจ้าของเรานับว่าท่านคู่ควรกับการทรงเรียกของพระองค์ และขอทรงให้ความมุ่งหมายอันดีทุกอย่างของท่านและการกระทำทุกอย่างที่เกิดจากความเชื่อของท่านสำเร็จลุล่วงโดยฤทธิ์อำนาจของพระองค์ 12เราทูลขอเช่นนี้เพื่อพระนามขององค์พระเยซูเจ้าของเราจะได้รับการเทิดพระเกียรติสิริในท่านทั้งหลาย และท่านจะได้รับศักดิ์ศรีในพระองค์ตามพระคุณของพระเจ้าและองค์พระเยซูคริสต์เจ้าของเรา