2 ቆሮንቶስ 9 – NASV & HHH

New Amharic Standard Version

2 ቆሮንቶስ 9:1-15

1ለቅዱሳን ስለሚደረገው አገልግሎት ልጽፍላችሁ አያስፈልግም። 2ምክንያቱም ሌሎችን ለመርዳት ያላችሁን በጎ ፈቃድ ዐውቃለሁ፤ ካለፈው ዓመት ጀምሮ እናንተ በአካይያ የምትኖሩ ሌሎችን ለመርዳት ዝግጁ እንደ ሆናችሁ ለመቄዶንያ ሰዎች አፌን ሞልቼ ተናግሬአለሁ፤ ቅን ፍላጎታችሁም ብዙዎችን ለበጎ ሥራ አነሣሥቷል። 3እንግዲህ በዚህ ነገር በእናንተ ላይ ያለን ትምክሕት ከንቱ ሆኖ እንዳይቀር፣ አስቀድሞ ስለ እናንተ እንደ ተናገርሁት ተዘጋጅታችሁ እንድትገኙ ወንድሞችን ልኬአለሁ። 4ምናልባት የመቄዶንያ ሰዎች ከእኔ ጋር መጥተው ሳትዘጋጁ ቢያገኟችሁ፣ እናንተ ብቻ ሳትሆኑ እኛም ያን ያህል በእናንተ በመመካታችን እናፍራለን። 5ስለዚህ ወንድሞች አስቀድመው ወደ እናንተ እንዲመጡና ከዚህ በፊት ለመስጠት ቃል የገባችሁትን ስጦታ አጠናቅቃችሁ እንድትጠብቋቸው፣ እነርሱን መለመን አስፈላጊ ሆኖ አግኝቻለሁ፤ እንግዲህ በልግስና ለመስጠት ያሰባችሁት ነገር በግዴታ ሳይሆን በፈቃደኝነት የተዘጋጀ ይሆናል።

በልግስና መስጠት

6ይህን አስታውሱ፤ ጥቂት የዘራ ጥቂት ያጭዳል፤ ብዙ የዘራ ብዙ ያጭዳል። 7እያንዳንዱ ሰው በቅሬታ ወይም በግዴታ ሳይሆን፣ በልቡ ያሰበውን ያህል ይስጥ፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ሰው ይወድዳል። 8ሁልጊዜ በሁሉ ነገር የሚያስፈልጋችሁን ሁሉ አግኝታችሁ ለበጎ ሥራ ሁሉ እንድትተርፉ፣ እግዚአብሔር ጸጋን ሁሉ ሊያበዛላችሁ ይችላል፤ 9ይህም፣

“በተነ፤ ለድኾችም ሰጠ፤

ጽድቁ ለዘላለም ይኖራል”

ተብሎ እንደ ተጻፈው ነው።

10ለዘሪ ዘርን፣ ለመብላት እንጀራን የሚሰጥ እርሱ የምትዘሩትን አትረፍርፎ ይሰጣችኋል፤ የጽድቃችሁንም ፍሬ ያበዛላችኋል። 11ሁልጊዜ በልግስና መስጠት እንድትችሉ በሁሉ ነገር ያበለጽጋችኋል፤ ልግስናችሁም በእኛ በኩል የሚደርሳቸው ሰዎች እግዚአብሔርን ለማመስገን ምክንያት ይሆናቸዋል።

12ይህ የምትሰጡት አገልግሎት የቅዱሳንን ጕድለት የሚያሟላ ብቻ ሳይሆን፣ ብዙ ምስጋና ለእግዚአብሔር የሚቀርብበት ነው። 13የክርስቶስን ወንጌል ተቀብላችሁ ስለ ታዘዛችሁና ለእነርሱም ሆነ ለሌሎች ስላሳያችሁት ልግስና ሰዎች ተፈትኖ ስላለፈው አገልግሎታችሁ እግዚአብሔርን ያከብራሉ፤ 14ስለ እናንተም በሚጸልዩበት ጊዜ እግዚአብሔር ከሰጣችሁ ታላቅ ጸጋ የተነሣ ይናፍቋችኋል። 15በቃላት ሊገለጥ ስለማይቻል ስጦታው እግዚአብሔር ይመስገን።

Habrit Hakhadasha/Haderekh

אגרת פולוס השנייה אל-הקורנתים 9:1-15

1איני צריך לכתוב לכם על העזרה הכספית למאמינים ביהודה, 2כי אני יודע שאתם מוכנים לעזור, ואף התגאיתי בכם לפני המאמינים במקדוניה. ”המאמינים ביוון היו מוכנים לשלוח תרומה כבר לפני שנה“, אמרתי להם. התלהבותכם עוררה רבים מהם להשתתף בתרומה. 3עתה אני שולח אחים אלה רק כדי לוודא שאתם באמת מוכנים ושכבר אספתם את כל התרומות, כפי שאמרתי להם. איני רוצה לגלות שהפעם התגאיתי בכם לשווא.

4אם יבואו אתי האנשים ממקדוניה וייווכחו שאינכם מוכנים, הרי אתבייש מאוד וגם אתם תתביישו.

5על כן ביקשתי מהאחים לבוא אליכם לפני, כדי לוודא שהתרומה אשר הבטחתם אכן מוכנה. ברצוני שתתרמו מתוך נדיבות ולא מתוך קמצנות.

6זכרו, אם תתנו מעט תקבלו מעט. איכר שזורע זרעים מעטים יקצור יבול דל, אך אם יזרע זרעים רבים יקצור יבול רב. 7כל אחד ייתן כאשר ידרבנו לבו; אל תאלצו איש לתת מעל רצונו, כי אלוהים אוהב את הנותנים בשמחה. 8אלוהים יכול לתת לכם מעל מה שאתם צריכים, כך שתמיד יהיה לכם די והותר לעצמכם, ואף תוכלו לתת לנזקקים בנדיבות ובשמחה.

9ככתוב:9‏.9 ט 9 תהלים קיב 9 ”פזר נתן לאביונים, צדקתו עומדת לעד“.

10האלוהים שנותן לאיכר זרע לזרוע, ואחר כך יבול לאכול, ייתן לכם זרע בשפע ויברך את יבול מעשיכם הטובים.

11אכן, אלוהים ייתן לכם שפע כדי שתוכלו לתת לזולת בשפע, וכאשר נמסור את מתנותיכם לנזקקים הם יודו לאלוהים על עזרתכם הנדיבה. 12וכך שירותכם לא רק יספק את צרכי המאמינים, אלא גם יביאם לידי הודיה לה׳.

13הואיל ושירותכם זה עמד במבחן, יודו רבים לה׳ על עזרתכם הנדיבה, ועל שאתם מקיימים הלכה למעשה את בשורת המשיח שבה אתם מאמינים.

14יתרה מזאת, הם יתפללו בעדכם בחיבה רבה, בגלל החסד הנפלא שהעניק לכם אלוהים.

15הבה נודה לאלוהים על מתנתו העצומה מספר.