2 ቆሮንቶስ 3 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

2 ቆሮንቶስ 3:1-18

1እንደ ገና ራሳችንን ልናመሰግን እንጀምራለንን? ወይስ እንደ ሌሎቹ ለእናንተ ወይም ከእናንተ የተጻፈ የምስጋና ደብዳቤ ያስፈልገን ይሆንን? 2እናንተ እኮ ሰው ሁሉ የሚያውቃችሁና የሚያነብባችሁ በልባችን ላይ የተጻፋችሁ ደብዳቤዎቻችን ናችሁ፤ 3እናንተ በቀለም ሳይሆን በሕያው እግዚአብሔር መንፈስ፣ በድንጋይ ጽላት ላይ ሳይሆን በሰው ልብ ጽላት ላይ የተጻፋችሁና በእኛ የተገለገላችሁ የክርስቶስ ግልጽ ደብዳቤ ናችሁ።

4በክርስቶስ በኩል በእግዚአብሔር ላይ ያለን እምነት ይህን የመሰለ ነው፤ 5ብቃታችን ከእግዚአብሔር ነው እንጂ፣ በራሳችን ብቃት ከእኛ ነው የምንለው አንዳች ነገር የለንም። 6እርሱም በፊደል ላይ ሳይሆን በመንፈስ ላይ የተመሠረተውን የአዲሱ ኪዳን አገልጋዮች እንድንሆን ብቁዎች አደረገን፤ ምክንያቱም ፊደል ይገድላል፤ መንፈስ ግን ሕይወትን ይሰጣል። 7እንግዲህ እስራኤላውያን ከፊቱ ክብር የተነሣ የሙሴን ፊት ትኵር ብለው ማየት እስኪሳናቸው ድረስ፣ ያ ከጊዜ በኋላ የሚያልፈውና በድንጋይ ላይ በፊደል የተቀረጸው የሞት አገልግሎት በክብር ከመጣ፣ 8ታዲያ፣ የመንፈስ አገልግሎት እንዴት ከዚያ የላቀ ክብር አይኖረውም? 9ሰዎችን የሚኰንነው አገልግሎት የከበረ ከሆነ፣ የሚያጸድቀው አገልግሎት የቱን ያህል ይበልጥ የከበረ ይሆን! 10ከዚህ በፊት ክቡር የነበረው የላቀ ክብር ካለው ጋር ሲወዳደር ክብር የሌለው ሆኗል። 11የሚያልፈው ያን ያህል ክብር ከነበረው፣ ጸንቶ የሚኖረውማ እንዴት የላቀ ክብር አይኖረውም?

12እንግዲህ ይህን የመሰለ ተስፋ ስላለን፣ በድፍረት እንናገራለን። 13እስራኤላውያን የፊቱ ማንጸባረቅ እየጠፋ ሲሄድ መጨረሻውን እንዳይመለከቱ፣ ፊቱን በጨርቅ እንደ ሸፈነው እንደ ሙሴ አይደለንም። 14ነገር ግን ብሉይ ኪዳን በተነበበ ቍጥር፣ ያ መሸፈኛ እስከ ዛሬ ድረስ ስላልተወገደ ልቡናቸው እንደ ደነዘዘ ነው፤ መሸፈኛው አሁንም አልተወገደም፤ የሚወገደው በክርስቶስ ብቻ ነውና። 15እስከ ዛሬም ድረስ የሙሴ መጻሕፍት በተነበቡ ቍጥር መሸፈኛው ልቡናቸውን ይሸፍናል። 16ነገር ግን አንድ ሰው ወደ ጌታ ዘወር ሲል መሸፈኛው ይወገዳል። 17ጌታ መንፈስ ነው፤ የጌታም መንፈስ ባለበት በዚያ ነጻነት አለ። 18እኛም ሁላችን ባልተሸፈነ ፊት የጌታን ክብር እንደ መስተዋት እያንጸባረቅን፣3፥18 ወይም የጌታን ክብር በጥሞና እያሰላሰልን የእርሱን መልክ እንድንመስል ከክብር ወደ ክብር እንለወጣለን፤ ይህም የሚሆነው መንፈስ ከሆነ ጌታ ነው።

Thai New Contemporary Bible

2โครินธ์ 3:1-18

1นี่เรากำลังจะชมตนเองอีกแล้วหรือ? หรือเราเป็นเหมือนบางคนที่ต้องการจดหมายรับรองจากท่านหรือถือจดหมายรับรองมาหาท่าน? 2ตัวท่านเองคือจดหมายของเรา จารึกอยู่ที่ดวงใจของเราให้ทุกคนได้รู้และได้อ่าน 3ท่านแสดงให้เห็นว่าท่านเป็นจดหมายจากพระคริสต์ เป็นผลจากพันธกิจของเรา ไม่ใช่เขียนด้วยหมึกแต่เขียนขึ้นด้วยพระวิญญาณของพระเจ้าผู้ทรงพระชนม์อยู่ ไม่ได้จารึกบนแผ่นศิลาแต่จารึกบนดวงใจมนุษย์

4นี่คือความมั่นใจของเราโดยทางพระคริสต์เฉพาะพระพักตร์พระเจ้า 5ไม่ใช่ว่าเราเองมีความสามารถที่จะอ้างสิทธิ์ในสิ่งใด แต่ความสามารถของเรามาจากพระเจ้า 6พระองค์ทรงให้เรามีความสามารถที่จะเป็นพันธกรแห่งพันธสัญญาใหม่ ไม่ใช่พันธสัญญาแห่งบทบัญญัติที่จารึกไว้ แต่เป็นพันธสัญญาแห่งพระวิญญาณ เพราะบทบัญญัติประหารชีวิตแต่พระวิญญาณประทานชีวิต

รัศมีแห่งพันธสัญญาใหม่

7ถ้าพันธกิจซึ่งนำความตายมา ที่จารึกด้วยตัวอักษรบนแผ่นศิลา ยังมากับรัศมี แม้รัศมีนี้จะจางหายไป แต่ก็เป็นเหตุทำให้ชนอิสราเอลไม่กล้ามองหน้าโมเสส 8แล้วพันธกิจแห่งพระวิญญาณจะไม่ยิ่งเปี่ยมด้วยรัศมีกว่านั้นหรือ? 9หากพันธกิจที่ตัดสินโทษมนุษย์ยังเปล่งรัศมี พันธกิจที่นำความชอบธรรมมาให้จะเปล่งรัศมีเจิดจ้ายิ่งกว่านั้นสักเท่าใด! 10เพราะสิ่งที่เคยมีรัศมีเจิดจ้า บัดนี้ก็อับแสงไปเมื่อเทียบกับรัศมีอันเจิดจ้ายิ่งกว่า 11และถ้าสิ่งที่กำลังเลือนหายยังมากับรัศมี รัศมีของสิ่งที่ยืนยงจะยิ่งใหญ่เหนือกว่านั้นสักเท่าใด!

12เหตุฉะนั้นเพราะเรามีความหวังใจเช่นนี้ เราจึงมีใจกล้า 13เราไม่เหมือนโมเสสซึ่งเอาผ้าคลุมหน้าเพื่อไม่ให้ชนอิสราเอลมองเห็นรัศมีที่กำลังจางหายไป 14แต่ครั้งนั้นจิตใจของพวกเขาก็ดื้อด้าน เพราะจนถึงทุกวันนี้ผ้าคลุมหน้าเดียวกันนั้นก็ยังคงอยู่เมื่อเขาอ่านพันธสัญญาเดิม ผ้าคลุมหน้านี้ยังไม่ได้ถูกเอาออกไป เพราะในพระคริสต์เท่านั้นที่ผ้านี้จะถูกเอาออกไปได้ 15กระทั่งทุกวันนี้เมื่ออ่านบัญญัติของโมเสส ผ้าก็ยังคลุมใจของพวกเขาอยู่ 16แต่เมื่อใดที่มีใครหันกลับมาหาองค์พระผู้เป็นเจ้า ผ้าคลุมนั้นก็จะถูกนำออกไป 17องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงเป็นพระวิญญาณ ที่ใดมีพระวิญญาณขององค์พระผู้เป็นเจ้า ที่นั่นก็มีเสรีภาพ 18และเราทั้งหลายผู้ไม่มีผ้าคลุมหน้าล้วนใคร่ครวญ3:18 หรือสะท้อนพระเกียรติสิริขององค์พระผู้เป็นเจ้า เรากำลังรับการเปลี่ยนแปลงให้เป็นเหมือนพระองค์ด้วยรัศมีที่เพิ่มพูนขึ้นทุกที อันเป็นรัศมีซึ่งมาจากองค์พระผู้เป็นเจ้าผู้ทรงเป็นพระวิญญาณ