2 ቆሮንቶስ 12 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

2 ቆሮንቶስ 12:1-21

ጳውሎስ ያየው ራእይና የተሰጠው መውጊያ

1በመመካት የሚገኝ ጥቅም ባይኖርም፣ መመካት ካስፈለገ ከጌታ ወደ ተቀበልሁት ራእይና መገለጥ አመራለሁ። 2ከዐሥራ አራት ዓመት በፊት እስከ ሦስተኛው ሰማይ ድረስ የተነጠቀ በክርስቶስ አንድ ሰው ዐውቃለሁ፤ የተነጠቀው በሥጋ ይሁን ወይም ከሥጋ ውጭ አላውቅም፤ እግዚአብሔር ግን ያውቃል። 3ይህ ሰው በሥጋ ይሁን ወይም ከሥጋ ውጭ እኔ አላውቅም፤ እግዚአብሔር ግን ያውቃል፤ 4እርሱም ወደ ገነት እንደ ተነጠቀ፣ በዚያም በሰው አንደበት ሊገለጥ የማይችል፣ ሰውም እንዲናገረው ያልተፈቀደለት ነገር ሰማ። 5እንደዚህ ስላለው ሰው እመካለሁ፤ ስለ ራሴ ግን ከደካማነቴ በስተቀር አልመካም። 6መመካት ብፈልግ እንኳ እንደ ሞኝ መቈጠር የለብኝም፤ ምክንያቱም የምናገረው እውነት ነው። ነገር ግን ማንም ስለ እኔ ከሚያየውና ከሚሰማው በላይ እንዳይገምተኝ ከመመካት እቈጠባለሁ።

7ከዚህ ታላቅ መገለጥ የተነሣ እንዳልታበይ የሥጋዬ መውጊያ፣ እርሱም የሚያሠቃየኝ የሰይጣን መልእክተኛ ተሰጠኝ። 8ይህ ነገር ከእኔ እንዲወገድልኝ፣ ጌታን ሦስት ጊዜ ለመንሁት፤ 9እርሱ ግን፣ “ጸጋዬ ይበቃሃል፤ ኀይሌ ፍጹም የሚሆነው በድካም ጊዜ ነውና” አለኝ። ስለዚህ የክርስቶስ ኀይል በእኔ ያድር ዘንድ፣ ይበልጥ ደስ እያለኝ በድካሜ እመካለሁ። 10ስለ ክርስቶስ በድካም፣ በስድብ፣ በመከራ፣ በስደትና በጭንቀት ደስ የምሰኘው ለዚህ ነው፤ ስደክም ያን ጊዜ ብርቱ ነኝና።

ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ሰዎች የነበረው ጭንቀት

11በመመካቴ ሞኝ ሆኛለሁ፤ ለዚህም ያበቃችሁኝ እናንተ ናችሁ፤ ስለ እኔ መመስከር የሚገባችሁ እናንተ ነበራችሁ። ደግሞም እኔ ከምንም የማልቈጠር ብሆንም፣ “ታላላቅ ሐዋርያት” ከሚባሉት በምንም አላንስም። 12የእውነተኛ ሐዋርያ ምልክቶች በመካከላችሁ ተደርገዋል፤ እነርሱም በትዕግሥት መጽናት፣ ምልክቶች፣ ድንቅ ነገሮችና ታምራት ናቸው። 13በእናንተ ላይ ሸክም ካለመሆኔ በቀር፣ ከሌሎች አብያተ ክርስቲያናት በምን አነሳችሁ? ይህን በደሌን ይቅር በሉኝ።

14ወደ እናንተ ለመምጣት ስዘጋጅ ይህ ሦስተኛዬ ነው፤ ስመጣ በምንም ነገር ሸክም አልሆንባችሁም፤ እኔ እናንተን እንጂ ከእናንተ ምንም አልፈልግምና፤ ደግሞም ወላጆች ለልጆች ገንዘብ ያከማቻሉ እንጂ ልጆች ለወላጆች አያከማቹም። 15እኔ ግን ስለ እናንተ ያለኝን ሁሉ ራሴንም ጭምር ብሰጥ ደስ ይለኛል፤ ታዲያ እኔ የምወድዳችሁ ይህን ያህል ከሆነ፣ እናንተ የምትወድዱኝ በጥቂቱ ነውን? 16የሆነው ሆኖ ሸክም አልሆንሁባችሁም፤ ነገር ግን በተንኰልና በዘዴ ያጠመድኋችሁ ሳይመስላችሁ አልቀረም! 17ለመሆኑ ወደ እናንተ በላክኋቸው ሰዎች አማካይነት በአንዱ እንኳ በዘበዝኋችሁን? 18ቲቶ ወደ እናንተ እንዲመጣ ለመንሁት፤ ወንድማችንንም ከእርሱ ጋር ላክሁት። ቲቶ በዘበዛችሁን? ከእርሱ ጋር በአንድ መንፈስ አልተመላለስንምን? አካሄዳችንስ አንድ አልነበረምን?

19እስከ አሁን ድረስ በእናንተ ፊት ራሳችንን ስንከላከል የኖርን ይመስላችኋልን? በክርስቶስ ሆነን በእግዚአብሔር ፊት እንናገራለን፤ ደግሞም ወዳጆች ሆይ፤ ይህን ሁሉ የምናደርገው እናንተን ለማነጽ ነው። 20ወደ እናንተ በምመጣበት ጊዜ፣ እኔ እንደምፈልገው ሆናችሁ ላላገኛችሁ እችላለሁ ወይም እናንተ እንደምትፈልጉኝ ሆኜ ላታገኙኝ ትችላላችሁ ብዬ እፈራለሁ፤ ምናልባትም በመካከላችሁ ጥል፣ ቅናት፣ ቍጣ፣ አድመኝነት፣ ስም ማጥፋት፣ ሐሜት፣ እብሪትና ሁከት ይኖራል ብዬ እሠጋለሁ። 21ዳግመኛም ስመጣ አምላኬ በእናንተ ፊት ያዋርደኝ ይሆን ብዬ እፈራለሁ፤ ይኸውም ብዙዎች ከዚህ በፊት ስለ ሠሩት ኀጢአትና ስለ ፈጸሙትም ርኩሰት፣ ዝሙትና መዳራት ንስሓ ሳይገቡ ቀርተው እንዳላዝን ነው።

Thai New Contemporary Bible

2โครินธ์ 12:1-21

นิมิตและหนามยอกกายเปาโล

1ข้าพเจ้าต้องโอ้อวดต่อไปถึงแม้จะไม่เกิดประโยชน์อะไรขึ้นมา ข้าพเจ้าก็ขอเล่าถึงนิมิตและการทรงสำแดงต่างๆ จากองค์พระผู้เป็นเจ้า 2ข้าพเจ้ารู้จักชายคนหนึ่งในพระคริสต์ ผู้ซึ่งสิบสี่ปีที่แล้วถูกรับขึ้นไปยังสวรรค์ชั้นที่สาม จะไปในกายหรือนอกกายข้าพเจ้าไม่รู้ พระเจ้าทรงทราบ 3ข้าพเจ้าไม่รู้ว่าเขาไปในกายนี้หรือนอกกาย พระเจ้าทรงทราบ แต่ข้าพเจ้ารู้ว่าชายผู้นี้ 4ถูกรับขึ้นไปถึงเมืองบรมสุขเกษม เขาได้ยินสิ่งต่างๆ ซึ่งไม่อาจจะพรรณนาได้ สิ่งซึ่งไม่อนุญาตให้มนุษย์บอกเล่า 5ข้าพเจ้าจะอวดถึงคนเช่นนี้แหละ แต่ข้าพเจ้าจะไม่อวดตนเอง เว้นแต่เรื่องความอ่อนแอของข้าพเจ้า 6ถ้าหากว่าข้าพเจ้าเลือกที่จะอวด ข้าพเจ้าก็จะไม่เป็นเช่นคนโง่ เพราะข้าพเจ้าจะพูดความจริง แต่ข้าพเจ้ายับยั้งไว้เพื่อไม่ให้ใครยกย่องข้าพเจ้าเกินเลยจากสิ่งที่ข้าพเจ้าพูดหรือทำ

7เพื่อไม่ให้ข้าพเจ้าผยองเนื่องด้วยการทรงสำแดงอันยิ่งใหญ่เลิศล้ำเหล่านี้ จึงทรงให้มีหนามในเนื้อของข้าพเจ้า เป็นทูตของซาตานคอยทรมานข้าพเจ้า 8ข้าพเจ้าทูลวิงวอนองค์พระผู้เป็นเจ้าสามครั้งให้ทรงเอาหนามนี้ออกไปจากข้าพเจ้า 9แต่พระองค์ตรัสกับข้าพเจ้าว่า “พระคุณของเราเพียงพอสำหรับเจ้า เพื่อว่าฤทธิ์อำนาจของเราจะได้ปรากฏเต็มที่ในความอ่อนแอ” ฉะนั้นข้าพเจ้าจึงอวดความอ่อนแอของตนด้วยความยินดี เพื่อฤทธิ์อำนาจของพระคริสต์จะได้อยู่ในข้าพเจ้า 10ด้วยเหตุนี้แหละเพื่อพระคริสต์ ข้าพเจ้าจึงชื่นชมในความอ่อนแอ ในการสบประมาท ในความยากลำบาก ในการกดขี่ข่มเหง ในความยุ่งยาก เพราะเมื่อใดที่ข้าพเจ้าอ่อนแอเมื่อนั้นข้าพเจ้าก็เข้มแข็ง

เปาโลห่วงใยพี่น้องชาวโครินธ์

11ข้าพเจ้าได้ทำตนเองให้เป็นคนโง่ไปแล้วสิ แต่พวกท่านก็เป็นผู้ผลักดันให้ข้าพเจ้าเป็นอย่างนี้ ท่านทั้งหลายน่าจะชมเชยข้าพเจ้า เพราะถึงแม้ว่าข้าพเจ้าจะไม่มีอะไรดีเด่น แต่ข้าพเจ้าก็ไม่ได้ด้อยไปกว่า “ยอดอัครทูต” เหล่านั้น 12สิ่งต่างๆ ที่บ่งบอกถึงความเป็นอัครทูตเช่น หมายสำคัญ การอัศจรรย์และปาฏิหาริย์ต่างๆ ก็ทำแล้วท่ามกลางพวกท่านด้วยความพากเพียรอดทนบากบั่น 13ท่าน

ด้อยกว่าคริสตจักรอื่นๆ ตรงไหน? ยกเว้นที่ข้าพเจ้าไม่เคยเป็นภาระแก่ท่าน โปรดอภัยข้าพเจ้าในความผิดข้อนี้!

14บัดนี้ข้าพเจ้าพร้อมที่จะมาเยี่ยมพวกท่านเป็นครั้งที่สาม และข้าพเจ้าจะไม่เป็นภาระแก่ท่าน เพราะสิ่งที่ข้าพเจ้าต้องการคือตัวท่านไม่ใช่ทรัพย์สินของท่าน ควรหรือที่ลูกๆ จะเก็บออมให้พ่อแม่? พ่อแม่ต่างหากที่ควรสะสมไว้ให้ลูก 15ดังนั้นข้าพเจ้าก็ยินดีที่จะใช้ทุกสิ่งที่มีและทุ่มเทตัวเองเพื่อท่าน ถ้าข้าพเจ้ารักท่านมากขึ้น ท่านจะรักข้าพเจ้าน้อยลงหรือ? 16อย่างที่เป็นมาข้าพเจ้าไม่เคยเป็นภาระแก่พวกท่าน แต่คนเจ้าเล่ห์อย่างข้าพเจ้าใช้กลเม็ดดักจับท่าน! 17ข้าพเจ้าฉกฉวยประโยชน์จากพวกท่านผ่านทางใครคนใดที่ข้าพเจ้าได้ส่งมาหรือ? 18ข้าพเจ้าขอให้ทิตัสมาหาท่านและข้าพเจ้าก็ส่งพี่น้องคนหนึ่งมากับเขาด้วย ทิตัสไม่ได้ฉกฉวยอะไรจากท่านใช่ไหม? เราไม่ได้ทำหน้าที่ด้วยใจแบบเดียวกันและดำเนินตามแนวทางเดียวกันหรอกหรือ? 19ตลอดมานี้ท่านคิดว่าเราแก้ตัวอยู่ใช่ไหม? ที่จริงเราพูดในสายพระเนตรของพระเจ้าอย่างคนที่อยู่ในพระคริสต์ ท่านที่รักทุกสิ่งที่เราทำก็ทำเพื่อเสริมสร้างพวกท่าน 20เนื่องจากข้าพเจ้าเกรงว่าเมื่อมาถึงข้าพเจ้าจะไม่เห็นท่านเป็นอย่างที่ข้าพเจ้าอยากให้เป็น และท่านก็จะไม่เห็นข้าพเจ้าเป็นอย่างที่ท่านอยากให้เป็น ข้าพเจ้ากลัวว่าอาจจะมีการทะเลาะเบาะแว้ง อิจฉาริษยา ฉุนเฉียว แตกแยก นินทาว่าร้าย หยิ่งลำพองและความวุ่นวาย 21ข้าพเจ้าเกรงว่าเมื่อข้าพเจ้ามาอีกครั้ง พระเจ้าของข้าพเจ้าจะทรงทำให้ข้าพเจ้าต่ำลงต่อหน้าพวกท่าน และข้าพเจ้าจะเศร้าเสียใจเนื่องด้วยหลายคนที่ได้ทำบาปและยังไม่ยอมกลับใจละทิ้งความเสื่อมทราม ความบาปทางเพศ และการเสเพลซึ่งเขาได้ปล่อยตัวลุ่มหลง