2 ቆሮንቶስ 1 – NASV & HHH

New Amharic Standard Version

2 ቆሮንቶስ 1:1-24

1በእግዚአብሔር ፈቃድ የክርስቶስ ኢየሱስ ሐዋርያ ከሆነው ከጳውሎስ፣ ከወንድማችንም ከጢሞቴዎስ፤

በቆሮንቶስ ላለችው ለእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን እንዲሁም በመላው አካይያ ለሚኖሩ ቅዱሳን ሁሉ፤

2ከአባታችን ከእግዚአብሔር፣ ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።

የመጽናናት አምላክ

3የርኅራኄ አባት፣ የመጽናናትም ሁሉ አምላክ የሆነው የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ። 4እኛ ራሳችን ከእግዚአብሔር በተቀበልነው መጽናናት፣ በመከራ ያሉትን ማጽናናት እንድንችል፣ እርሱ በመከራችን ሁሉ ያጽናናናል። 5የክርስቶስ ሥቃይ በእኛ ላይ የመብዛቱን ያህል መጽናናታችንም በክርስቶስ በኩል ይበዛልናል። 6መከራ ብንቀበል ስለ እናንተ መጽናናትና መዳን ነው። ብንጽናናም እኛ የተቀበልነውን መከራ በመቀበል በትዕግሥት እንድትጸኑ ስለ እናንተ መጽናናት ነው። 7ስለ እናንተ ያለን ተስፋ ጽኑ ነው፤ ምክንያቱም በመከራችን እንደ ተካፈላችሁ ሁሉ በመጽናናታችንም እንደምትካፈሉ እናውቃለን።

8ወንድሞች ሆይ፤ በእስያ ስለ ደረሰብን መከራ እንድታውቁ እንወድዳለን፤ በሕይወት ለመኖር እንኳ ተስፋ እስከምንቈርጥ ድረስ ከዐቅማችን በላይ የሆነ ጽኑ መከራ ደርሶብን ነበር። 9በርግጥም የሞት ፍርድ እንደ ተፈረደብን ይሰማን ነበር፤ ይህም የሆነው ሙታንን በሚያስነሣ በእግዚአብሔር እንድንታመን እንጂ፣ በራሳችን እንዳንታመን ነው። 10እርሱ እንዲህ ካለው የሞት አደጋ አድኖናል፤ ያድነናልም፤ ወደ ፊትም ደግሞ እንደሚያድነን ተስፋችንን በእርሱ ላይ ጥለናል። 11እናንተም በጸሎታችሁ ደግፉን፤ በብዙዎች ጸሎት ስለ ተሰጠን ስጦታ ብዙ ሰዎች ስለ እኛ1፥11 ብዙ ቅጆች እናንተ ይላሉ። ምስጋና ያቀርባሉ።

ጳውሎስ ዕቅዱን ለወጠ

12እንግዲህ ትምክሕታችን ይህ ነው፤ በዚህ ዓለም በተለይም ከእናንተ ጋር ባለን ግንኙነት፣ ከእግዚአብሔር በሆነ ቅድስናና ቅንነት እንደ ኖርን ኅሊናችን ይመሰክራል፤ ይህም በሰው ጥበብ ሳይሆን፣ በእግዚአብሔር ጸጋ ነው። 13ልታነብቡት ወይም ልትረዱት የማትችሉትን ነገር አንጽፍላችሁም፤ ሁሉንም እንደምትረዱ ተስፋ አደርጋለሁ። 14እናንተ በእኛ እንደምትመኩ ሁሉ እኛም በእናንተ እንደምንመካ አሁን የተረዳችሁን በከፊል ቢሆንም፣ በጌታ ኢየሱስ ቀን ሁሉን ትረዳላችሁ።

15በዚህ ርግጠኛ ስለ ነበርሁ በዕጥፍ እንድትጠቀሙ፣ በመጀመሪያ ልጐበኛችሁ ዐቅጄ ነበር። 16ወደ መቄዶንያ ስሄድ እግረ መንገዴን ልጐበኛችሁና ከመቄዶንያም በእናንተ በኩል ተመልሼ ወደ ይሁዳ ስሄድ በጕዞዬ እንድትረዱኝ ዐቅጄ ነበር። 17ይህን ሳቅድ በሚገባ ሳላስብ ያደረግሁት ይመስላችኋልን? ወይስ በዓለማዊ ልማድ አንዴ፣ “አዎን፣ አዎን” ወዲያው ደግሞ፣ “አይደለም፣ አይደለም” የምል ይመስላችኋልን?

18እግዚአብሔር ታማኝ እንደ ሆነ ሁሉ፣ ለእናንተ የምንናገረው ቃላችን፣ “አዎን” እና “አይደለም” ሊሆን አይችልም፤ 19ምክንያቱም እኔም ሆንሁ ሲላስና1፥19 ግሪኩ ሲልዋኑስ ይላል። ጢሞቴዎስ፣ እኛ የሰበክንላችሁ የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ “አዎን” እና “አይደለም” አልነበረም፤ ነገር ግን በእርሱ ዘወትር፣ “አዎን” ነው። 20በእግዚአብሔር የተሰጡ ተስፋዎች ሁሉ፣ “አዎን” የሚሆኑት በእርሱ ነውና፤ እኛም በእርሱ አማካይነት ለእግዚአብሔር ክብር፣ “አሜን” የምንለው በዚህ ምክንያት ነው። 21እንግዲህ፣ እኛንም እናንተንም በክርስቶስ ጸንተን እንድንቆም የሚያደርገን እግዚአብሔር ነው፤ የቀባንም እርሱ ነው፤ 22የእርሱ ለመሆናችን ማኅተሙን ያተመብን ደግሞም ወደ ፊት ለምናገኘው ነገር የመንፈሱን ዋስትና በልባችን ያኖረ እርሱ ነው።

23ወደ ቆሮንቶስ ተመልሼ ያልመጣሁት እንዳላሳዝናችሁ ብዬ ነው፤ ይህ እውነት ካልሆነ እግዚአብሔር ይመስክርብኝ። 24ጸንታችሁ የምትቆሙት በእምነት ስለሆነ፣ ደስ እንዲላችሁ ከእናንተ ጋር እንሠራለን እንጂ በእምነታችሁ ላይ ለመሠልጠን አይደለም።

Habrit Hakhadasha/Haderekh

אגרת פולוס השנייה אל-הקורנתים 1:1-24

1מאת פולוס, שליח ישוע המשיח לפי רצון אלוהים, ומאת אחינו טימותיוס.

אל המאמינים המשיחיים בקורינתוס וביוון כולה.

2מי ייתן שהאלוהים אבינו וישוע המשיח אדוננו יברך כל אחד מכם ויעניק לכם שלום.

3הבה נברך את האלוהים אבי המשיח אדוננו, שכן הוא מקור ואב הרחמים, שמנחם ומעודד אותנו בצרותינו. 4אלוהים מנחם אותנו בצרותינו, על־מנת שבאותו אופן נעזור גם אנחנו למתנסים בצרות שעברו עלינו. 5שכן ככל שאנו מרבים לסבול למען המשיח, כך הוא ירבה לעודדנו ולנחמנו. 6אם אנחנו סובלים, הרי שזה למען נחמתכם וישועתכם; אם אנחנו מנוחמים, הרי שזה למען נחמתכם: להראות לכם מניסיוננו כיצד ינחם אלוהים גם אתכם כשתתנסו בסבלנו. 7אין לנו ספק שאם עליכם לסבול כמונו, הרי שגם תנוחמו כמונו.

8אחים יקרים, ברצוננו להזכיר לכם את דבר הצרות שעברו עלינו באסיה. המשא והלחצים היו כבדים מנשוא, עד כי לא האמנו שנישאר בחיים. 9חשנו שנגזר עלינו דין מוות, אך הדבר נועד ללמדנו שאל לנו לבטוח בעצמנו, אלא רק באלוהים המחיה את המתים. 10אלוהים אכן הצילנו ממוות נורא, ואנו בטוחים שאף יוסיף להצילנו. 11אך על כולכם להתפלל בעדנו, כי ככל שירבו המתפללים למען ביטחוננו, כן ירבו המודים לאלוהים כשיענה לתפילותיכם.

12אנו גאים בעובדה שתמיד התנהגנו בתם ויושר, בוטחים באלוהים ולא בעצמנו. גם איתכם נהגנו כך! 13‏-14מכתבי היו כנים ולא כתבתי דבר בין השורות. ואם כי עדיין אינכם מכירים אותי היטב (אני מקווה שבקרוב תטיבו להכירני), אנא, השתדלו להתגאות בי, כשם שאני אתגאה בכם ביום שובו של ישוע אדוננו.

15‏-16הואיל ולא הטלתי ספק בביטחונכם והבנתכם, החלטתי לבקרכם בדרכי למקדוניה ובשובי משם, כדי שאהיה לכם לברכה כפולה וכדי שתשלחוני ליהודה. 17ודאי תשאלו מדוע שיניתי את דעתי; האם נהגתי בפזיזות? או האם נהגתי באנוכיות ואמרתי ”כן“ כשהתכוונתי ל”לא“? 18חס וחלילה! כשם שאלוהים מהימן כך לא נהגתי בקלות ראש. כשאני אומר ”כן“ אני מתכוון לכך. 19טימותיוס, סילוונוס ואני סיפרנו לכם על ישוע המשיח בן־האלוהים. המשיח תמיד מקיים את דבריו ולעולם אינו אומר ”כן“ בהתכוונו ל”לא“.

20הוא מקיים את כל הבטחות אלוהים, יהיה מספרן אשר יהיה. אנו סיפרנו לכולם מה נאמן הוא, וכך פארנו את שם אלוהים. 21אלוהים הוא אשר עשה אתכם ואותי למאמינים משיחיים נאמנים, והטיל עלינו את השליחות לבשר את הבשורה. 22הוא אף חתם אותנו בחותמו, והשכין בלבנו את רוח הקודש כערבות להשתייכותנו אליו.

23אלוהים עדי שלא באתי אליכם עד כה מפני שחסתי עליכם; לא רציתי לצער אתכם בתוכחה קשה. 24איני מנסה לשפוט אתכם בענייני האמונה, שהרי אמונתכם איתנה. ברצוני לעזור לשמחתכם; כן, ברצוני לשמח אתכם ולא לצער.