2 ሳሙኤል 6 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

2 ሳሙኤል 6:1-23

ታቦቱ ወደ ኢየሩሳሌም ወጣ

6፥1-11 ተጓ ምብ – 1ዜና 13፥1-14

6፥12-19 ተጓ ምብ – 1ዜና 15፥25–16፥3

1ዳዊት እንደ ገና ከእስራኤል የተመረጡ በአጠቃላይ ሠላሳ ሺሕ ሰዎች ሰበሰበ። 2እርሱና አብረውት ያሉት ሰዎች ሁሉ በታቦቱ ላይ ባለው ኪሩቤል ላይ በተቀመጠው በሰራዊት ጌታ በእግዚአብሔርም ስም6፥2 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም ግን፣ ስም የሚለውን አይጨምርም። የተጠራውን የእግዚአብሔርን ታቦት ከዚያ ለማምጣት በይሁዳ ወዳለችው ወደ በኣል ሄዱ። 3የእግዚአብሔርንም ታቦት በአዲስ ሠረገላ ላይ አኑረው፣ በኰረብታ ላይ ካለው ከአሚናዳብ ቤት አውጥተው አመጡ፤ ሠረገላውን ይነዱ የነበሩትም የአሚናዳብ ልጆች ዖዛና አሒዮ ሲሆኑ፣ 4የእግዚአብሔርም ታቦት በሠረገላው ላይ ሆኖ6፥4 የሙት ባሕር ጥቅልልና አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ የማሶሬቲኩ ቅጅ ግን፣ ኰረብታው ላይ ካለው ከአቢናዳብ ቤት ከእግዚአብሔር ታቦት ጋር አመጡት ይላል።፣ አሒዮ ፊት ፊት ይሄድ ነበር። 5ዳዊትና የእስራኤል ቤት በሙሉ በዝማሬ፣ በበገና፣ በመሰንቆ፣ በከበሮ፣ በጸናጽልና በቃጭል ባለ ኀይላቸው ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት ያሸበሽቡ ነበር።

6ወደ ናኮን ዐውድማ ሲደርሱም በሬዎቹ ስለ ተደናቀፉ፣ ዖዛ እጁን ዘርግቶ የእግዚአብሔርን ታቦት ያዘ። 7ዖዛ በድፍረት ይህን ስላደረገ፣ የእግዚአብሔር ቍጣ በላዩ ላይ ነደደ፤ ስለዚህም እግዚአብሔር ቀሠፈው፤ እርሱም በእግዚአብሔር ታቦት አጠገብ እዚያው ሞተ።

8የእግዚአብሔር ቍጣ ዖዛንን ስለ ሰበረው፣ ዳዊት ተከፋ፤ ያም ቦታ እስከ ዛሬ ድረስ ፔሬዝ ዖዛ6፥8 ፔሬዝ ዖዛ ማለት ዑዛንን መሰባበር ማለት ነው ተብሎ ይጠራል።

9ዳዊት በዚያን ቀን እግዚአብሔርን ስለ ፈራ “የእግዚአብሔር ታቦት እንዴት ወደ እኔ ይመጣል?” አለ። 10ስለዚህ ዳዊት የእግዚአብሔር ታቦት አብሮት እንዲሆን ወደ ዳዊት ከተማ ይዞት ለመሄድ አልፈለገም፤ በዚህ ፈንታ አቅጣጫ ለውጦ የጌት ሰው ወደ ሆነው ወደ አቢዳራ ቤት ወሰደው። 11የእግዚአብሔርም ታቦት የጌት ሰው በሆነው በአቢዳራ ቤት ሦስት ወር ተቀመጠ፤ እግዚአብሔርም አቢዳራንና ቤተ ሰቡን ሁሉ ባረከ።

12በዚህ ጊዜ፣ “በእግዚአብሔር ታቦት ምክንያት የአቢዳራን ቤተ ሰውና ያለውን ሁሉ እግዚአብሔር ባረከለት” ብለው ለዳዊት ነገሩት። ስለዚህ ዳዊት ወደዚያው ወርዶ፣ የእግዚአብሔርን ታቦት ከአቢዳራ ቤት ወደ ዳዊት ከተማ በታላቅ ደስታ አመጣው። 13እነዚያ የእግዚአብሔርን ታቦት ተሸክመው የነበሩት ሰዎች ስድስት ርምጃ በሄዱ ቍጥር፣ አንድ በሬና አንድ የሠባ ጥጃ ይሠዋ ነበር። 14ዳዊትም የበፍታ ኤፉድ በወገቡ ታጥቆ በሙሉ ኀይሉ በእግዚአብሔር ፊት ይጨፍር ነበር። 15እንዲህ ባለ ሁኔታም ዳዊትና መላው የእስራኤል ቤት ሆይ እያሉና ቀንደ መለከቱን እየነፉ የእግዚአብሔርን ታቦት አመጡ።

16የእግዚአብሔር ታቦት ወደ ዳዊት ከተማ ሲገባ፣ የሳኦል ልጅ ሜልኮል በመስኮት ሆና ትመለከት ነበር፤ ንጉሥ ዳዊት በእግዚአብሔር ፊት ሲዘልልና ሲያሸበሽብ ባየችው ጊዜ በልቧ ናቀችው።

17ከዚያም የእግዚአብሔርን ታቦት አምጥተው፣ ዳዊት በተከለለት ድንኳን ውስጥ አግብተው በተዘጋጀለት ስፍራ አኖሩት፤ ዳዊትም የሚቃጠል መሥዋዕትና የኅብረት መሥዋዕት6፥17 በትውፊት የሰላም መሥዋዕት ይባላል። በእግዚአብሔር ፊት አቀረበ። 18ዳዊት የሚቃጠለውን መሥዋዕትና የኅብረቱን መሥዋዕት ካቀረበ በኋላ ሕዝቡን በሰራዊት ጌታ በእግዚአብሔር ስም ባረከ። 19የእስራኤል ወገን ለሆነው ለሕዝቡ ሁሉ፣ ለወንዱም ለሴቱም ለእያንዳንዱ ሰው አንዳንድ እንጀራ፣ አንዳንድ ሙዳ ሥጋና አንዳንድ የዘቢብ ጥፍጥፍ ሰጠ፤ ከዚህ በኋላ ሁሉም ወደየቤቱ ሄደ።

20ዳዊት ቤተ ሰቡን ለመመረቅ ወደ ቤቱ በተመለሰ ጊዜ፣ የሳኦል ልጅ ሜልኮል ልትቀበለው ወጥታ፣ “ዛሬ የእስራኤል ንጉሥ በመኳንንቱ ገረዶች ፊት እንደ አንድ ተራ ሰው ዕራቍቱን መታየቱ ክብሩ ሆኖ ነው!” አለችው።

21ዳዊትም እንዲህ አላት፤ “አዎን ከአባትሽና በቤቱ ካሉት ሁሉ አስበልጦ በእግዚአብሔር ሕዝብ በእስራኤል ላይ ገዥ አድርጎ በመረጠኝ በእግዚአብሔር ፊት አሸብሽቤአለሁ፤ አሁንም አሸበሽባለሁ። 22እንዲያውም ከዚህ ይልቅ ራሴን በፊቱ ዝቅ አደርጋለሁ፤ ከዚህም የባሰ የተናቅሁ እሆናለሁ፤ ነገር ግን በጠቀስሻቸው ገረዶች ፊት እከብራለሁ።”

23የሳኦልም ልጅ ሜልኮል እስከሞተችበት ጊዜ ድረስ ልጅ አልወለደችም ነበር።

Thai New Contemporary Bible

2ซามูเอล 6:1-23

ดาวิดอัญเชิญหีบพันธสัญญามายังเยรูซาเล็ม

(1พศด.13:1-14; 15:25—16:3)

1แล้วดาวิดนำพลอิสราเอลที่เลือกสรรแล้วสามหมื่นคน 2ไปยังบาอาลาห์แห่งยูดาห์6:2 คือ คีริยาทเยอาริม ภาษาฮีบรูว่าบาอาเลยูดาห์เป็นอีกรูปหนึ่งของบาอาลาห์แห่งยูดาห์ เพื่ออัญเชิญหีบพันธสัญญาของพระเจ้าซึ่งเรียกตามพระนามคือ พระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ผู้ประทับระหว่างเครูบบนหีบนั้น 3พวกเขาตั้งหีบพันธสัญญาของพระเจ้าบนเกวียนใหม่ และนำลงมาจากบ้านของอาบีนาดับซึ่งอยู่บนภูเขา โดยมีอุสซาห์กับอาหิโยบุตรอาบีนาดับเป็นผู้นำเกวียน 4ที่บรรทุกหีบพันธสัญญาของพระเจ้าและอาหิโยเดินนำหน้า 5ดาวิดและปวงชนอิสราเอลเฉลิมฉลองอย่างเต็มที่ต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้า มีการขับร้องและบรรเลงดนตรี6:5 ฉบับ MT. ว่าเฉลิมฉลองเฉพาะพระพักตร์องค์พระผู้เป็นเจ้าด้วยการบรรเลงเครื่องดนตรีทุกชนิดที่ทำจากไม้สนด้วยพิณเขาคู่ พิณใหญ่ รำมะนา กรับและฉาบ

6เมื่อพวกเขามาถึงลานนวดข้าวของนาโคน วัวสะดุดเสียหลัก อุสซาห์ยื่นมือออกไปยึดหีบพันธสัญญาของพระเจ้าไว้ 7พระพิโรธขององค์พระผู้เป็นเจ้าจึงพลุ่งขึ้นต่ออุสซาห์ และทรงประหารเขาที่บังอาจทำอย่างไม่ยำเกรงพระองค์ เขาตายอยู่ข้างหีบพันธสัญญาของพระเจ้า

8ดาวิดไม่พอพระทัยเพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงพระพิโรธอุสซาห์ ที่แห่งนั้นจึงได้ชื่อว่า เปเรศอุสซาห์6:8 แปลว่า อุบัติภัยแก่อุสซาห์จวบจนบัดนี้

9ในวันนั้นดาวิดรู้สึกเกรงกลัวองค์พระผู้เป็นเจ้าและตรัสว่า “เราจะนำหีบพันธสัญญาขององค์พระผู้เป็นเจ้ากลับบ้านได้อย่างไร?” 10ฉะนั้นจึงทรงดำริไม่นำหีบพันธสัญญาขององค์พระผู้เป็นเจ้ากลับมายังเมืองดาวิด แต่นำไปไว้ที่บ้านของโอเบดเอโดมแห่งกัท 11หีบพันธสัญญาขององค์พระผู้เป็นเจ้าอยู่ที่นั่นเป็นเวลาสามเดือน องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงอวยพรแก่โอเบดเอโดมแห่งกัทและทุกคนในครัวเรือน

12มีคนมาทูลกษัตริย์ดาวิดว่า “องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงอวยพรครอบครัวโอเบดเอโดมและทุกสิ่งที่เขามีเนื่องด้วยหีบพันธสัญญาของพระเจ้า” ดังนั้นดาวิดจึงเสด็จไปอัญเชิญหีบพันธสัญญาของพระเจ้าจากบ้านของโอเบดเอโดมมายังเมืองดาวิดด้วยความยินดี 13เมื่อผู้หามหีบพันธสัญญาขององค์พระผู้เป็นเจ้าเดินไปได้หกก้าว ดาวิดก็ถวายวัวผู้หนึ่งตัวและลูกวัวขุนหนึ่งตัว 14ดาวิดทรงสวมเอโฟดลินิน เต้นรำต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้าอย่างสุดกำลัง 15ดาวิดและอิสราเอลทั้งปวงอัญเชิญหีบพันธสัญญาขององค์พระผู้เป็นเจ้ามาท่ามกลางเสียงโห่ร้องและเสียงแตร

16ขณะที่หีบพันธสัญญาขององค์พระผู้เป็นเจ้าผ่านเข้ามาในเมืองดาวิด มีคาลราชธิดาของซาอูลมองจากหน้าต่างเห็นกษัตริย์ดาวิดทรงโลดเต้นและร่ายรำต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้าก็นึกดูแคลนอยู่ในใจ

17พวกเขาอัญเชิญหีบพันธสัญญาขององค์พระผู้เป็นเจ้ามาตั้งไว้ในเต็นท์ซึ่งดาวิดทรงจัดเตรียมไว้ แล้วดาวิดถวายเครื่องเผาบูชา และเครื่องสันติบูชาต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้า 18หลังจากที่ถวายเครื่องเผาบูชาและเครื่องสันติบูชาเสร็จแล้ว ดาวิดก็ทรงอำนวยพรแก่ประชากรในพระนามของพระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ 19และประทานขนมปัง อินทผลัมอัด และขนมลูกเกดอย่างละหนึ่งก้อนแก่ทุกคนทั้งชายและหญิง แล้วประชาชนทั้งปวงพากันกลับบ้าน

20ส่วนดาวิดเสด็จกลับวังมาอวยพรแก่บรรดาเชื้อพระวงศ์ แต่มีคาลราชธิดาของซาอูลออกมารับเสด็จ และตรัสว่า “วันนี้กษัตริย์แห่งอิสราเอลสง่าภาคภูมิจริงนะ ทรงเปลื้องอาภรณ์ต่อหน้าทาสหญิงเหมือนคนถ่อยไร้ยางอาย!”

21ดาวิดตรัสว่า “เราทำเช่นนี้ต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้าผู้ทรงเลือกและแต่งตั้งเราให้เป็นผู้ปกครองเหนืออิสราเอลประชากรขององค์พระผู้เป็นเจ้าแทนที่จะเลือกราชบิดาของเจ้าหรือคนใดคนหนึ่งในวงศ์ตระกูลของเขา ดังนั้นเราจะเฉลิมฉลองต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้า 22แม้ว่าเราจะดูไร้เกียรติมากกว่านี้และดูด้อยค่าในสายตาของเราเอง แต่พวกทาสหญิงที่เจ้าเอ่ยมาก็จะยังคงให้เกียรติเรา”

23และมีคาลราชธิดาของซาอูลก็ไม่มีราชโอรสราชธิดาเลยตลอดชีวิต