2 ሳሙኤል 6 – NASV & BPH

New Amharic Standard Version

2 ሳሙኤል 6:1-23

ታቦቱ ወደ ኢየሩሳሌም ወጣ

6፥1-11 ተጓ ምብ – 1ዜና 13፥1-14

6፥12-19 ተጓ ምብ – 1ዜና 15፥25–16፥3

1ዳዊት እንደ ገና ከእስራኤል የተመረጡ በአጠቃላይ ሠላሳ ሺሕ ሰዎች ሰበሰበ። 2እርሱና አብረውት ያሉት ሰዎች ሁሉ በታቦቱ ላይ ባለው ኪሩቤል ላይ በተቀመጠው በሰራዊት ጌታ በእግዚአብሔርም ስም6፥2 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም ግን፣ ስም የሚለውን አይጨምርም። የተጠራውን የእግዚአብሔርን ታቦት ከዚያ ለማምጣት በይሁዳ ወዳለችው ወደ በኣል ሄዱ። 3የእግዚአብሔርንም ታቦት በአዲስ ሠረገላ ላይ አኑረው፣ በኰረብታ ላይ ካለው ከአሚናዳብ ቤት አውጥተው አመጡ፤ ሠረገላውን ይነዱ የነበሩትም የአሚናዳብ ልጆች ዖዛና አሒዮ ሲሆኑ፣ 4የእግዚአብሔርም ታቦት በሠረገላው ላይ ሆኖ6፥4 የሙት ባሕር ጥቅልልና አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ የማሶሬቲኩ ቅጅ ግን፣ ኰረብታው ላይ ካለው ከአቢናዳብ ቤት ከእግዚአብሔር ታቦት ጋር አመጡት ይላል።፣ አሒዮ ፊት ፊት ይሄድ ነበር። 5ዳዊትና የእስራኤል ቤት በሙሉ በዝማሬ፣ በበገና፣ በመሰንቆ፣ በከበሮ፣ በጸናጽልና በቃጭል ባለ ኀይላቸው ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት ያሸበሽቡ ነበር።

6ወደ ናኮን ዐውድማ ሲደርሱም በሬዎቹ ስለ ተደናቀፉ፣ ዖዛ እጁን ዘርግቶ የእግዚአብሔርን ታቦት ያዘ። 7ዖዛ በድፍረት ይህን ስላደረገ፣ የእግዚአብሔር ቍጣ በላዩ ላይ ነደደ፤ ስለዚህም እግዚአብሔር ቀሠፈው፤ እርሱም በእግዚአብሔር ታቦት አጠገብ እዚያው ሞተ።

8የእግዚአብሔር ቍጣ ዖዛንን ስለ ሰበረው፣ ዳዊት ተከፋ፤ ያም ቦታ እስከ ዛሬ ድረስ ፔሬዝ ዖዛ6፥8 ፔሬዝ ዖዛ ማለት ዑዛንን መሰባበር ማለት ነው ተብሎ ይጠራል።

9ዳዊት በዚያን ቀን እግዚአብሔርን ስለ ፈራ “የእግዚአብሔር ታቦት እንዴት ወደ እኔ ይመጣል?” አለ። 10ስለዚህ ዳዊት የእግዚአብሔር ታቦት አብሮት እንዲሆን ወደ ዳዊት ከተማ ይዞት ለመሄድ አልፈለገም፤ በዚህ ፈንታ አቅጣጫ ለውጦ የጌት ሰው ወደ ሆነው ወደ አቢዳራ ቤት ወሰደው። 11የእግዚአብሔርም ታቦት የጌት ሰው በሆነው በአቢዳራ ቤት ሦስት ወር ተቀመጠ፤ እግዚአብሔርም አቢዳራንና ቤተ ሰቡን ሁሉ ባረከ።

12በዚህ ጊዜ፣ “በእግዚአብሔር ታቦት ምክንያት የአቢዳራን ቤተ ሰውና ያለውን ሁሉ እግዚአብሔር ባረከለት” ብለው ለዳዊት ነገሩት። ስለዚህ ዳዊት ወደዚያው ወርዶ፣ የእግዚአብሔርን ታቦት ከአቢዳራ ቤት ወደ ዳዊት ከተማ በታላቅ ደስታ አመጣው። 13እነዚያ የእግዚአብሔርን ታቦት ተሸክመው የነበሩት ሰዎች ስድስት ርምጃ በሄዱ ቍጥር፣ አንድ በሬና አንድ የሠባ ጥጃ ይሠዋ ነበር። 14ዳዊትም የበፍታ ኤፉድ በወገቡ ታጥቆ በሙሉ ኀይሉ በእግዚአብሔር ፊት ይጨፍር ነበር። 15እንዲህ ባለ ሁኔታም ዳዊትና መላው የእስራኤል ቤት ሆይ እያሉና ቀንደ መለከቱን እየነፉ የእግዚአብሔርን ታቦት አመጡ።

16የእግዚአብሔር ታቦት ወደ ዳዊት ከተማ ሲገባ፣ የሳኦል ልጅ ሜልኮል በመስኮት ሆና ትመለከት ነበር፤ ንጉሥ ዳዊት በእግዚአብሔር ፊት ሲዘልልና ሲያሸበሽብ ባየችው ጊዜ በልቧ ናቀችው።

17ከዚያም የእግዚአብሔርን ታቦት አምጥተው፣ ዳዊት በተከለለት ድንኳን ውስጥ አግብተው በተዘጋጀለት ስፍራ አኖሩት፤ ዳዊትም የሚቃጠል መሥዋዕትና የኅብረት መሥዋዕት6፥17 በትውፊት የሰላም መሥዋዕት ይባላል። በእግዚአብሔር ፊት አቀረበ። 18ዳዊት የሚቃጠለውን መሥዋዕትና የኅብረቱን መሥዋዕት ካቀረበ በኋላ ሕዝቡን በሰራዊት ጌታ በእግዚአብሔር ስም ባረከ። 19የእስራኤል ወገን ለሆነው ለሕዝቡ ሁሉ፣ ለወንዱም ለሴቱም ለእያንዳንዱ ሰው አንዳንድ እንጀራ፣ አንዳንድ ሙዳ ሥጋና አንዳንድ የዘቢብ ጥፍጥፍ ሰጠ፤ ከዚህ በኋላ ሁሉም ወደየቤቱ ሄደ።

20ዳዊት ቤተ ሰቡን ለመመረቅ ወደ ቤቱ በተመለሰ ጊዜ፣ የሳኦል ልጅ ሜልኮል ልትቀበለው ወጥታ፣ “ዛሬ የእስራኤል ንጉሥ በመኳንንቱ ገረዶች ፊት እንደ አንድ ተራ ሰው ዕራቍቱን መታየቱ ክብሩ ሆኖ ነው!” አለችው።

21ዳዊትም እንዲህ አላት፤ “አዎን ከአባትሽና በቤቱ ካሉት ሁሉ አስበልጦ በእግዚአብሔር ሕዝብ በእስራኤል ላይ ገዥ አድርጎ በመረጠኝ በእግዚአብሔር ፊት አሸብሽቤአለሁ፤ አሁንም አሸበሽባለሁ። 22እንዲያውም ከዚህ ይልቅ ራሴን በፊቱ ዝቅ አደርጋለሁ፤ ከዚህም የባሰ የተናቅሁ እሆናለሁ፤ ነገር ግን በጠቀስሻቸው ገረዶች ፊት እከብራለሁ።”

23የሳኦልም ልጅ ሜልኮል እስከሞተችበት ጊዜ ድረስ ልጅ አልወለደችም ነበር።

Bibelen på hverdagsdansk

2. Samuelsbog 6:1-23

David henter arken og fører den til Jerusalem

1Derefter udvalgte David 30.000 af Israels bedste krigere 2og gik i spidsen for dem til Ba’ala6,2 Et andet navn for Kirjat-Jearim, jf. 1.Krøn. 13,6. i Judas stammeområde for at bringe den almægtige Herres Ark hjem—han, der troner mellem keruberne. 3-4Arken, der i lang tid havde stået i Abinadabs hus på højen, blev anbragt på en ny oksekærre, som blev styret af Abinadabs to sønner, Uzza og Ahjo. Uzza gik ved siden af arken og Ahjo foran. 5David og Israels øvrige ledere dansede og sang af alle kræfter til Herrens ære til musik fra lyrer, harper, tamburiner, kastagnetter og bækkener.

6Men da de nåede til Nakons tærskeplads, snublede okserne, og Uzza rakte hånden ud for at støtte Guds Ark. 7Da blev Herren vred og straffede Uzza, fordi han ikke viste ærefrygt for Guds Ark, som ikke måtte røres, og han døde på stedet. 8David var oprørt over, at Herren havde straffet Uzza så hårdt. Derfor kaldte han stedet for „Peretz-Uzza”,6,8 Navnet betyder: „Udfaldet mod Uzza”. hvilket det hedder den dag i dag.

9Episoden gjorde, at David blev bange for Herren. „Hvordan tør jeg bringe Herrens Ark hjem til mig?” sagde han. 10Derfor ombestemte han sig, og i stedet for at føre Herrens Ark ind i Davidsbyen, lod han den indtil videre opbevare hos Obed-Edom fra Gat. 11Der stod den i tre måneder, og Herren velsignede Obed-Edom og hans familie.

12Da David hørte, at Herrens Ark havde bragt velsignelse til Obed-Edoms familie og ejendom, arrangerede han et festligt optog for at føre arken op til Davidsbyen. 13Så snart de, som bar Herrens Ark, havde gået seks skridt, gjorde de holdt, mens der blev ofret en tyr og en fedekalv. 14David var begejstret og dansede uhæmmet for Herren, iført en præstedragt. 15Sådan førte David og israelitterne under jubelråb og trompetfanfarer Herrens Ark op til Davidsbyen.

16Men da processionen nåede ind til Davidsbyen, og Davids kone Mikal, Sauls datter, fra sit vindue så kong David hoppe rundt og danse for Herren, følte hun foragt for ham.

17Herrens Ark blev anbragt i det telt, som David havde ladet indrette til den. Derefter ofrede han brændofre og takofre til Herren, 18og han velsignede folket i Herren den Almægtiges navn. 19Så gav han hver af de tilstedeværende, både mænd og kvinder, en gave bestående af et brød, en daddelkage og en rosinkage, og de gik alle hver til sit.

20Da David vendte hjem for at velsigne sin familie, kom Mikal ham i møde og udbrød forarget: „Som Israels konge dog tog sig værdigt ud i dag! Hvad skulle det gøre godt for at danse halvnøgen omkring for øjnene af byens kvinder? Sikken tåbelig opførsel!”

21David svarede: „Jeg dansede for Herren, som udvalgte mig til konge i stedet for din far og hans slægt, og som gjorde mig til leder for sit folk Israel. 22Og jeg vil blive ved med at danse til Guds ære, også selvom det er ydmygende, og du foragter mig for det. Men de kvinder, du nævnte, respekterer mig faktisk for at vise min glæde!”

23Mikal, Sauls datter, forblev barnløs hele sit liv.