2 ሳሙኤል 23 – NASV & BDS

New Amharic Standard Version

2 ሳሙኤል 23:1-39

የዳዊት የመጨረሻ ቃል

1የዳዊት የመጨረሻ ቃሉ ይህ ነው፤

“በያዕቆብ አምላክ የተቀባው፣

ልዑል ከፍ ከፍ ያደረገው ሰው፣

የእስራኤል ተወዳጁ ዘማሪ፣

የእሴይ ልጅ የዳዊት የትንቢት ቃል ይህ ነው፤

2የእግዚአብሔር መንፈስ በእኔ ተናገረ፤

ቃሉ በአንደበቴ ላይ ነበረ።

3የእስራኤል አምላክ ተናገረ፤

የእስራኤልም ዐለት እንዲህ አለኝ፤

‘ሰዎችን በጽድቅ የሚገዛ፣

በፈሪሀ እግዚአብሔርም የሚያስተዳድር፣

4እርሱ፣ ደመና በሌለበት፣ በማለዳ ፀሓይ በምትወጣበት ጊዜ፣

እንዳለው ብርሃን ነው፤

በምድር ላይ ሣርን እንደሚያበቅለው፣

ከዝናብም በኋላ እንዳለው የብርሃን ጸዳል ነው።’

5“የእኔስ ቤት በእግዚአብሔር ዘንድ ትክክል አይደለምን?

ሁሉንም ነገር አዘጋጅቶና ጠብቆ፣

ከእኔ ጋር ዘላለማዊ ኪዳን ያደረገ አይደለምን?

ድነቴን ከፍጻሜ የሚያደርሰው፣

መሻቴን ሁሉ የሚሰጠኝ እርሱ አይደለምን?

6ነገር ግን ክፉ ሰዎች ሁሉ፣

በእጅ እንደማይሰበሰብ እንደ እሾኽ ይጣላሉ።

7እሾኽ የሚነካ ሁሉ፣

የብረት መሣሪያ ወይም የጦር ዘንግ ይይዛል፤

ባሉበትም ቦታ ፈጽመው በእሳት ይቃጠላሉ።”

የኀያላኑ የዳዊት ሰዎች ጀብዱ

23፥8-39 ተጓ ምብ – 1ዜና 11፥10-41

8የዳዊት ኀያላን ሰዎች ስም የሚከተለው ነው፤

የታሕክሞን23፥8 የታሕክሞን ሰው ማለት ሐክሞናዊ ማለት ሊሆን ይችላል። (1ዜና 11፥11 ይመ)። ሰው ዮሴብ በሴትቤት23፥8 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች ግን፣ ኢያሱስቴ ይላሉ፣ ይኸውም፣ ያሾብዓም ነው (1ዜና 11፥11 ይመ)። የሦስቱ አለቆች አለቃ ሲሆን፣ እርሱም ጦሩን ሰብቆ በአንድ ውጊያ ላይ ስምንት መቶ ሰው የገደለ ነው።23፥8 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች ከዚህ ጋር ይስማማሉ (1ዜና 11፥11 ይመ)፤ ዕብራይስጡና አብዛኞቹ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች ግን ስምንት መቶ ሰዎችን የገደለው አዜናዊው አዲኑ ነበር ይላሉ።

9ከእርሱ ቀጥሎ የአሆሃዊው የዱዲ ልጅ ኤልዔዘር ነበረ፤ እርሱም ለጦርነት አንድ ላይ ተሰብስበው23፥9 1ዜና 11፥13 ይመ፤ ዕብራይስጡ ግን፣ በዚያ ተሰበሰቡ ይላል የነበሩትን ፍልስጥኤማውያንን በተገዳደሩ ጊዜ፣ ከዳዊት ጋር ከነበሩት ከሦስቱ ኀያላን ሰዎች አንዱ ነበር። ከዚያም የእስራኤል ሰዎች ሸሹ። 10እርሱ ግን የቆመበትን ስፍራ አልለቀቀም፤ እጁ እስኪዝልና ከሰይፉ ጋር እስኪጣበቅ ድረስ ፍልስጥኤማውያንን ወጋ፤ በዚያችም ዕለት እግዚአብሔር ታላቅ ድልን ሰጠ። የሸሸውም ሰራዊት ወደ ኤልዔዘር የተመለሰው የተገደሉትን ሰዎች ለመግፈፍ ብቻ ነበር።

11ከእርሱም ቀጥሎ የአሮዳዊው የአጌ ልጅ ሣማ ነበር፤ ፍልስጥኤማውያንም ሌሒ በተባለ ስፍራ ምስር በሞላበት አንድ ዕርሻ ላይ በአንድነት ተሰብስበው ሳሉ፣ የእስራኤል ሰራዊት ከፍልስጥኤማውያን ፊት ሸሹ፤ 12ሣማ ግን የቆመበትን ስፍራ አልለቀቀም፤ ጦርነቱንም ተቋቁሞ ፍልስጥኤማውያንን ገደለ፤ በዚያችም ዕለት እግዚአብሔር ታላቅ ድል ሰጠ።

13በመከር ወራት፣ የፍልስጥኤም ሰራዊት በራፋይም ሸለቆ ሰፍሮ ሳለ፣ ከሠላሳዎቹ አለቆች ሦስቱ ዳዊት ወዳለበት ወደ ዓዶላም ዋሻ መጡ። 14በዚያም ጊዜ ዳዊት በምሽግ ውስጥ ነበረ፤ የፍልስጥኤማውያንም ሰራዊት በቤተ ልሔም ነበረ፤ 15ዳዊትም በናፍቆት፣ “በቤተ ልሔም በር አጠገብ ካለችው ጕድጓድ ውሃ ማን ባመጣልኝ!” አለ። 16ስለዚህ ሦስቱ ኀያላን በፍልስጥኤማውያን ሰራዊት መካከል ሰንጥቀው በማለፍ፣ በቤተ ልሔም በር አጠገብ ካለችው ጕድጓድ ውሃ ቀድተው ለዳዊት አመጡለት። እርሱ ግን አልጠጣውም፤ ይልቁን በእግዚአብሔር ፊት መሥዋዕት አድርጎ አፈሰሰው፤ 17“እርሱም፣ እግዚአብሔር ሆይ፤ እንዲህ ያለውን ነገር ላደርግ? ይህስ ከእኔ ይራቅ! ይህ በነፍሳቸው ቈርጠው የሄዱ ሰዎች ደም አይደለምን?” አለ፤ ዳዊትም ሊጠጣው አልፈለገም። እንግዲህ ሦስቱ ኀያላን ሰዎች ያደረጉት ጀብዱ እንዲህ ነበር።

18የጽሩያ ልጅ የኢዮአብ ወንድም አቢሳ የሦስቱ23፥18 አብዛኞቹ የዕብራይስጥ ቅጆች (እንዲሁም 1ዜና 11፥20 ይመ) ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ሁለት የዕብራይስጥ ቅጆችና የሱርስቱ ትርጕም፣ ሠላሳ ይላሉ። ኀያላን አለቃ ነበረ። በሦስት መቶ ሰዎች ላይ ጦሩን ሰብቆ የገደላቸውና እንደ ሦስቱ ኀያላን ሁሉ እርሱም ዝናን ያተረፈ ሰው ነበረ። 19አቢሳ ከሦስቱ ይልቅ እጅግ የከበረ አልነበረምን? ከእነርሱ እንደ አንዱ ባይሆንም አለቃቸው ነበረ።

20የቀብጽኤል አገር ሰው የሆነው የዮዳሄ ልጅ በናያስ ታላቅ ጀብዱ የሠራ ሌላው ጐበዝ ተዋጊ ነበረ፤ እርሱም ሁለት በጣም የታወቁ የሞዓብ ሰዎችን ገደለ፤ እንዲሁም በረዶ በጣለበት ዕለት በጕድጓድ ውስጥ ገብቶ አንበሳ ገድሏል፤ 21ደግሞም አንድ ግዙፍ ግብፃዊ ገድሏል፤ ግብፃዊው በእጁ ጦር የያዘ ቢሆንም፣ በናያስ ግን ሊገጥመው በትር ይዞ ወደ እርሱ ሄደ፤ ከግብፃዊውም እጅ ጦሩን በመንጠቅ በገዛ ጦሩ ገደለው።

22የዮዳሄ ልጅ የበናያስ ጀግንነት እንደዚህ ያለ ነበረ፤ እርሱም እንደ ሦስቱ ኀያላን ሁሉ ዝናን ያተረፈ ሲሆን፣ 23ከሠላሳዎቹ ሁሉ በላይ የከበረ ሰው ነበረ፤ ነገር ግን ከሦስቱ እንደ አንዱ አልነበረም። ዳዊትም የክብር ዘበኞቹ አለቃ አድርጎ ሾመው።

24ከሠላሳዎቹ መካከል የሚከተሉት ይገኙባቸዋል፤

የኢዮአብ ወንድም አሣሄል፣

የቤተ ልሔሙ ሰው የዱዲ ልጅ ኤልያናን፣

25አሮዳዊው ሣማ፣

አሮዳዊው ኤሊቃ፣

26ፈሊጣዊው ሴሌስ፣

የቴቁሐዊው የዒስካ ልጅ ዒራስ፣

27ዓናቶታዊው አቢዔዜር፤

ኩሳታዊው ምቡናይ23፥27 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች (እንዲሁም 1ዜና 11፥29 ይመ) ግን፣ ሲባካይ ይላሉ።

28አሆሃዊው ጸልሞን፣

ነጦፋዊው ማህራይ፣

29የነጦፋዊው የበዓና ልጅ ሔሌብ23፥29 አብዛኞቹ የዕብራይስጥ ቅጆች ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ አንዳንድ የዕብራይስጥ ቅጆችና ቩልጌት (እንዲሁም 1ዜና 11፥30 ይመ) ግን፣ ሔሌድ ይላሉ።

ከብንያም ወገን የጊብዓ ሰው የሆነው የሪባይ ልጅ ኢታይ፣

30ጲርዓቶናዊው በናያስ፣

የገዓስ ሸለቆ ሰው ሂዳይ23፥30 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች (እንዲሁም 1ዜና 11፥32 ይመ) ግን፣ ሁራይ ይላሉ።

31ዐረባዊው አቢዓልቦን፣

በርሑማዊው ዓዝሞት፣

32ሸዓልቦናዊው ኤሊያሕባ፣

የአሳን ልጆች፤ ዮናታን የተባለው፣

33የአሮዳዊው የሣማ ልጅ23፥33 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች (እንዲሁም 1ዜና 11፥34 ይመ) ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ዕብራይስጡ ግን ልጅ የሚለውን አይጨምርም።

የአሮዳዊው የሻራር23፥33 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች (እንዲሁም 1ዜና 11፥35 ይመ) ግን፣ ሳካር ይላሉ። ልጅ አሒአም፤

34የማዕካታዊው የአሐሰባይ ልጅ ኤሌፋላት፣

የጊሎናዊው የአኪጦፌል ልጅ ኤሊአም፣

35ቀርሜሎሳዊው ሐጽሮ፤

አርባዊው ፈዓራይ፣

36የሱባ ሰው የሆነው የናታን ልጅ ይግዓል፣

37አሞናዊው ጻሌቅ፣

የጽሩያ ልጅ የኢዮአብ ጦር መሣሪያ ያዥ የነበረው ብኤሮታዊው ነሃራይ፣

38ይትራዊው ዒራስ፣

ይትራዊው ጋሬብ፣

39እንዲሁም ኬጢያዊው ኦርዮ።

በጠቅላላው ሠላሳ ሰባት ነበሩ።

La Bible du Semeur

2 Samuel 23:1-39

Les dernières déclarations de David

1Voici les dernières paroles de David :

Voici ce que déclare ╵David, fils d’Isaï,

cet homme haut placé,

qui a reçu l’onction ╵de la part du Dieu de Jacob,

oui, voici les paroles ╵qu’Israël se plaît à chanter23.1 Autres traductions : David… dont Israël se plaît à chanter les exploits ou du chantre agréable d’Israël..

2L’Esprit de l’Eternel ╵s’est exprimé par moi,

ses paroles sont sur ma langue.

3Le Dieu d’Israël a parlé,

le rocher d’Israël m’a dit :

Le juste gouverneur des hommes

qui gouverne avec la crainte de Dieu

4est pareil au soleil ╵qui se lève au matin

et répand sa lumière ╵dans un ciel sans nuage,

et la verdure sort de terre ╵par ses rayons et par la pluie.

5N’en est-il pas ainsi ╵de ma dynastie devant Dieu,

puisqu’il a conclu avec moi ╵une alliance éternelle,

en tout bien établie ╵et qu’il respectera toujours ?

En toutes circonstances, ╵il œuvre à mon salut,

il accomplit tous mes désirs.

6Mais les vauriens sont tous ╵pareils à des épines ╵que l’on rejette au loin.

On ne les saisit pas ╵avec une main nue,

7celui qui veut les prendre

se munit d’un crochet de fer ╵ou du bois d’une lance,

et il les jette au feu, ╵pour les brûler sur place.

Les valeureux guerriers de David

(1 Ch 11.10-41)

8Voici les noms des guerriers de David : Le premier est Yosheb-Bashébeth le Tahkmonite, il était chef du groupe des trois. C’est lui qui23.8 D’après certains manuscrits de l’ancienne version grecque (voir 1 Ch 11.11) ; le texte hébreu traditionnel et d’autres manuscrits de l’ancienne version grecque ont : c’est Adino l’Etsnite qui…, avec son javelot, tua huit cents hommes au cours d’un seul combat.

9Le second était Eléazar, fils de Dodo et petit-fils d’Ahohi. Il était l’un des trois guerriers qui accompagnèrent David lorsqu’il défia les Philistins rassemblés23.9 Selon 1 Ch 11.13 : rassemblés à Pas-Dammin. pour la bataille. Déjà, les hommes d’Israël battaient en retraite et gagnaient les hauteurs, 10mais lui tint bon et frappa les Philistins jusqu’à ce que sa main fût engourdie et resta crispée sur la poignée de son épée. Ce jour-là, l’Eternel accorda une grande victoire à Israël ; les Israélites n’eurent plus qu’à revenir derrière Eléazar pour s’emparer des dépouilles.

11Après lui vient Shamma, fils d’Agué de Harar. Les Philistins s’étaient rassemblés à Léhi. Il y avait là un champ couvert de lentilles. Les Israélites avaient pris la fuite devant les Philistins, 12mais Shamma prit position au milieu du champ, le libéra et frappa les Philistins. Ainsi l’Eternel accorda une victoire éclatante à Israël.

13Un jour, au début du temps de la moisson, trois membres du groupe des trente vinrent trouver David dans la caverne d’Adoullam23.13 Voir 1 S 22.1., tandis qu’une troupe de Philistins était campée dans la vallée des Rephaïm. 14David se trouvait alors dans son refuge fortifié et un poste de Philistins occupait Bethléhem.

15David fut soudain pris d’un brûlant désir et s’écria : Qui me fera boire de l’eau du puits qui se trouve à la porte de Bethléhem ?

16Alors les trois guerriers pénétrèrent dans le camp des Philistins et puisèrent de l’eau au puits qui est à la porte de Bethléhem. Ils l’apportèrent et la présentèrent à David ; mais il ne voulut pas en boire, et il la répandit en libation pour l’Eternel. 17Il s’exclama : Que l’Eternel me garde de faire pareille chose ! Cette eau représente le sang de ces hommes qui sont allés là-bas au péril de leur vie.

Il refusa donc de la boire. Tel fut l’exploit de ces trois guerriers.

18Abishaï, frère de Joab, fils de Tserouya, était le chef de ce groupe de trois. Un jour, il brandit son javelot contre trois cents hommes et les tua. Ainsi, il devint célèbre parmi le second groupe des trois. 19Il était le plus considéré parmi ces trois et devint leur chef ; mais il n’égala pas les trois du premier groupe.

20Benaya de Qabtséel, fils de Yehoyada et petit-fils d’un homme valeureux qui avait accompli23.20 L’ancienne version grecque a : Benaya, fils de Yehoyada, était un vaillant guerrier de Qabtséel, qui avait accompli… de nombreux exploits, tua deux puissants héros moabites. C’est lui aussi qui, un jour de neige, descendit au fond d’une citerne pour y tuer un lion. 21C’est encore lui qui tua un Egyptien de taille impressionnante armé d’un javelot. Il bondit sur lui, armé d’un simple bâton, et lui arracha son javelot dont il se servit pour le tuer. 22Tels furent les exploits de Benaya, fils de Yehoyada, qui se fit une renommée parmi le second groupe des trois. 23Il fut le plus estimé parmi les trente, mais sans égaler ceux du premier groupe des trois. David lui confia le commandement de sa garde personnelle.

24Le groupe des trente comprenait aussi Asaël, frère de Joab, Elhanân, fils de Dodo de Bethléhem, 25Shamma et Eliqa, tous deux de Harod, 26Hélets de Péleth, Ira, fils d’Iqqesh de Teqoa, 27Abiézer d’Anatoth, Mebounnaï de Housha, 28Tsalmôn, d’Ahoah, Maharaï, de Netopha, 29Héleb23.29 Certains manuscrits hébreux, la Vulgate et 1 Ch 11.30 ont : Héled., fils de Baana, de Netopha, Ittaï, fils de Ribaï, de Guibéa en Benjamin, 30Benaya, de Piratôn, Hiddaï23.30 Certains manuscrits de l’ancienne version grecque et 1 Ch 11.32 ont : Houraï., de Nahalé-Gaash, 31Abi-Albôn, de la vallée du Jourdain23.31 Ou : de Beth-Arba., Azmaveth, de Barhoum, 32Eliahba de Shaalbôn, Bené-Yashên, Jonathan, 33Shamma23.33 L’ancienne version grecque et 1 Ch 11.34 ont : fils de Shamma., de Harar, Ahiam, fils de Sharar23.33 Certains manuscrits de l’ancienne version grecque et 1 Ch 11.35 ont : Sakar., d’Arar, 34Eliphéleth, fils de Ahasbaï, fils d’un Maakathien, Eliam, fils d’Ahitophel, de Guilo, 35Hetsraï, de Karmel, Paaraï, d’Arab, 36Yiguéal, fils de Nathan, de Tsoba, Bani de Gad23.36 Certains manuscrits de l’ancienne version grecque et 1 Ch 11.38 ont : fils d’Hagri., 37Tséleq, l’Ammonite, Nahraï, de Beéroth, qui portait les armes de Joab, fils de Tserouya, 38Ira et Gareb, tous deux de Yéter, 39et Urie, le Hittite23.39 Voir 11.3-27.. Au total, ils étaient trente-sept.