2 ሳሙኤል 22 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

2 ሳሙኤል 22:1-51

የዳዊት የምስጋና መዝሙር

22፥1-51 ተጓ ምብ – መዝ 18፥1-50

1እግዚአብሔር ከጠላቶቹ ሁሉና ከሳኦልም እጅ በታደገው ጊዜ፣ ዳዊት የዚህን መዝሙር ቃል ለእግዚአብሔር ዘመረ፤ 2እንዲህም አለ፤

እግዚአብሔር ዐለቴ ዐምባዬና ታዳጊዬ ነው፤

3አምላኬ፣ የምጠጋበት ዐለቴ፣

ጋሻዬና የድነቴ ቀንድ22፥3 ቀንድ የጥንካሬ ወይም የኀይል ምልክት ነው። ነው።

እርሱም ጠንካራ ምሽጌ፣ መጠጊያና አዳኜ ነው፤

ከኀይለኞች ሰዎች ታድነኛለህ።

4ምስጋና የሚገባውን እግዚአብሔርን እጠራለሁ፤

ከጠላቶቼም እድናለሁ።

5“የሞት ማዕበል ከበበኝ፤

የጥፋትም ጐርፍ አሰጠመኝ።

6የሲኦል ገመድ ተጠመጠመብኝ፤

የሞትም ወጥመድ ተጋረጠብኝ።

7በጨነቀኝ ጊዜ እግዚአብሔርን ጠራሁት፤

ወደ አምላኬም ጮኽሁ።

እርሱም ከመቅደሱ ድምፄን ሰማ፤

ጩኸቴም ከጆሮው ደረሰ።

8ምድር ተንቀጠቀጠች፤ ተናወጠችም፤

የሰማያትም መሠረቶች22፥8 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ ቩልጌትና ሱርስቱ ግን (እንዲሁም መዝ 18፥7 ይመ) ተራሮች ይላሉ። ተናጉ፤

እርሱ ተቈጥቷልና ራዱ።

9ከአፍንጫው የቍጣ ጢስ ወጣ፤

ከአፉ የሚባላ እሳት ነደደ፤

ከውስጡም ፍሙ ጋለ።

10ሰማያትን ሰንጥቆ ወረደ፤

ከእግሩም በታች ጥቅጥቅ ያለ ደመና ነበረ።

11በኪሩቤል ላይ ተቀምጦ በረረ፤

በነፋስም ክንፍ መጠቀ።22፥11 አብዛኞቹ የዕብራይስጥ ቅጆች (እንዲሁም መዝ 18፥10 ይመ) ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ እጅግ ብዙ የሆኑ የዕብራይስጥ ቅጆች ግን፣ ተገለጠ ይላሉ።

12ጨለማው በዙሪያው እንዲከበው፣

ጥቅጥቅ ያለውም የሰማይ ዝናም ደመና እንዲሰውረው አደረገ።

13በእርሱ ፊት ካለው ብርሃን፣

የመብረቅ ብልጭታ ወጣ።

14እግዚአብሔር ከሰማያት አንጐደጐደ፤

የልዑልም ድምፅ አስተጋባ።

15ፍላጻውን ሰድዶ ጠላቶቹን በተናቸው፤

መብረቆቹንም ልኮ አወካቸው።

16ከእግዚአብሔር ተግሣጽ፣ ከአፍንጫው

ከሚወጣው፣ ከእስትንፋሱ ቍጣ የተነሣ፣

የባሕር ሸለቆዎች ታዩ፤ የምድር መሠረቶችም ተገለጡ።

17“ከላይ እጁን ዘርግቶ ያዘኝ፤

ከጥልቅ ውሆችም ውስጥ አወጣኝ።

18ከብርቱ ጠላቶቼ፣

ከማልቋቋማቸውም ባላጋሮቼ ታደገኝ።

19በመከራዬ ቀን መጡብኝ፤

እግዚአብሔር ግን ደገፈኝ።

20ሰፊ ወደ ሆነ ስፍራ አወጣኝ፤

በእኔ ደስ ስለ ተሰኘም አዳነኝ።

21እግዚአብሔር እንደ ጽድቄ መለሰልኝ፤

እንደ እጄም ንጹሕነት ብድራትን ከፈለኝ፤

22የእግዚአብሔርን መንገድ ጠብቄአለሁና፤

ከአምላኬም ዘወር ብዬ ክፉ ነገር አላደረግሁም።

23ሕጉ ሁሉ በፊቴ ነው፤

ከሥርዐቱም ዘወር አላልሁም።

24በፊቱ ያለ ነውር ነበርሁ፤

ራሴንም ከኀጢአት ጠብቄአለሁ።

25እግዚአብሔር እንደ ጽድቄ፣

በፊቱም እንዳለኝ ንጽሕና22፥25 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ የሰብዓ ሊቃናትና የቩልጌት ትርጉሞች (እንዲሁም መዝ 18፥24 ይመ) ግን፣ እንደ እጄም ንጽሕና ይላሉ። ብድራትን ከፈለኝ።

26“ለታማኝ ሰው አንተም ታማኝ መሆንህን፣

ለቅን ሰው አንተም ቅን መሆንህን ታሳያለህ።

27ለንጹሕ ሰው አንተም ንጹሕ መሆንህን፣

ለጠማማ ሰው ግን አንተም ጠማማ መሆንህን ታሳያለህ።

28አንተ የተጠቃውን ሕዝብ ታድናለህ፤

ዐይንህ ግን ያዋርዳቸው ዘንድ፣ ትዕቢተኞችን ይመለከታል።

29እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ መብራቴ ነህ፤

እግዚአብሔርም ጨለማዬን ያበራል።

30በአንተ ርዳታ በጠላት ሰራዊት ላይ ወደ ፊት ገፍቼ እሄዳለሁ22፥30 ወይም በጋሬጣዎች ውስጥ እሮጣለሁ

በአምላኬም ኀይል ቅጥሩን እዘላለሁ።

31“የአምላክ መንገዱ ፍጹም ነው፤

የእግዚአብሔርም ቃል የነጠረ ነው፤

ለሚታመኑበትም ሁሉ ጋሻ ነው፤

32ከእግዚአብሔር በቀር አምላክ ማን አለና፤

ከአምላካችንስ በቀር ዐለት ማን ነው?

33ኀይልን የሚያስታጥቀኝ22፥33 የሙት ባሕር ጥቅልል፣ አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች፣ የቩልጌትና የሱርስት ቅጆች (እንዲሁም መዝ 18፥32 ይመ) ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ የማሶሬቱ ቅጅ ግን፣ ጠንካራ መሸሸጊያ የሚሆነኝ ይላል።

መንገዴንም የሚያቀና እርሱ አምላኬ ነው።

34እግሮቼን እንደ ብሆር እግሮች ያበረታል፤

በከፍታዎችም ላይ አጽንቶ ያቆመኛል።

35እጆቼን ለጦርነት ያሠለጥናል፤

ክንዶቼም የናስ ቀስት ይገትራሉ።

36የማዳንህን ጋሻ ሰጥተኸኛል፤

ድጋፍህ ታላቅ አድርጎኛል።

37ርምጃዬን አሰፋህ፤

እግሮቼም አልተሰነካከሉም።

38“ጠላቶቼን አሳደድሁ፤ አጠፋኋቸውም፤

እስኪደመሰሱም ድረስ ወደ ኋላ አልተመለስሁም።

39ፈጽሜ አጠፋኋቸው፤ ተመልሰውም መቆም አልቻሉም፤

ከእግሬም ሥር ወድቀዋል።

40ለጦርነት ኀይልን አስታጠቅኸኝ፣

ተቃዋሚዎቼንም ከእግሬ ሥር አንበረከክሃቸው።

41ጠላቶቼ ፊታቸውን አዙረው እንዲሸሹ አደረግሃቸው።

ባላንጣዎቼንም ደመሰስኋቸው።

42ለርዳታ ጮኹ፤ ያዳናቸው ግን አልነበረም፤ ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፤ እርሱ ግን

አልመለሰላቸውም።

43በምድር ላይ እንዳለ ትቢያ አድቅቄ ፈጨኋቸው፤

በመንገድም ላይ እንዳለ ጭቃ ወቀጥኋቸው፤ ረገጥኋቸውም።

44“በሕዝቤ ከተቃጣብኝ አደጋ አዳንኸኝ፤

የመንግሥታትም ራስ አደረግኸኝ።

የማላውቀው ሕዝብ ተገዛልኝ፤

45ባዕዳን ሊለማመጡኝ መጡ፤

እንደ ሰሙኝም ወዲያውኑ ይታዘዙኛል።

46ባዕዳን ፈሩ፤

ከምሽጋቸውም እየተንቀጠቀጡ ወጡ22፥46 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞችና የቩልጌቱ ቅጅ (እንዲሁም መዝ 18፥32 ይመ) ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ማሶሬቱ ግን ራሳቸውን ጐዱ ይላል።

47እግዚአብሔር ሕያው ነው፤ ዐለቴ የተባረከ ይሁን፤

የድነቴ ዐለት አምላኬ ከፍ ከፍ ይበል።

48የሚበቀልልኝ አምላክ፣

መንግሥታትንም ከሥሬ የሚያስገዛልኝ እርሱ ነው፤

49እርሱ ከጠላቶቼ እጅ ነጻ ያወጣኛል።

አንተ ከጠላቶቼ በላይ ከፍ ከፍ አደረግኸኝ፤

ከጨካኝ ሰዎችም እጅ ታደግኸኝ።

50ስለዚህ እግዚአብሔር ሆይ፤

በመንግሥታት መካከል አመሰግንሃለሁ፤ ለስምህም ምስጋና እዘምራለሁ።

51“ለንጉሡ ታላቅ ድል ይሰጠዋል፤

ለቀባው ለዳዊትና ለዘሩ፣

ለዘላለም የማይለወጥ ፍቅሩን ያሳየዋል።”

New International Reader’s Version

2 Samuel 22:1-51

David’s Song of Praise

1David sang the words of this song to the Lord. He sang them when the Lord saved him from the power of all his enemies and of Saul. 2He said,

“The Lord is my rock and my fort. He is the God who saves me.

3My God is my rock. I go to him for safety.

He is like a shield to me. He’s the power that saves me.

He’s my place of safety. I go to him for help. He’s my Savior.

He saves me from those who want to hurt me.

4I called out to the Lord. He is worthy of praise.

He saved me from my enemies.

5“The waves of death were all around me.

A destroying flood swept over me.

6The ropes of the grave were tight around me.

Death set its trap in front of me.

7When I was in trouble I called out to the Lord.

I called out to my God.

From his temple he heard my voice.

My cry for help reached his ears.

8“The earth trembled and shook.

The pillars of the heavens rocked back and forth.

They trembled because the Lord was angry.

9Smoke came out of his nose.

Flames of fire came out of his mouth.

Burning coals blazed out of it.

10He opened the heavens and came down.

Dark clouds were under his feet.

11He got on the cherubim and flew.

The wings of the wind lifted him up.

12He covered himself with darkness.

The dark rain clouds of the sky were like a tent around him.

13From the brightness all around him

flashes of lightning blazed out.

14The Lord thundered from heaven.

The voice of the Most High God was heard.

15He shot his arrows and scattered the enemy.

He sent flashes of lightning and chased them away.

16The bottom of the sea could be seen.

The foundations of the earth were uncovered.

It happened when the Lord’s anger blazed out.

It came like a blast of breath from his nose.

17“He reached down from heaven. He took hold of me.

He lifted me out of deep waters.

18He saved me from my powerful enemies.

He set me free from those who were too strong for me.

19They stood up to me when I was in trouble.

But the Lord helped me.

20He brought me out into a wide and safe place.

He saved me because he was pleased with me.

21“The Lord has been good to me because I do what is right.

He has rewarded me because I lead a pure life.

22I have lived the way the Lord wanted me to.

I’m not guilty of turning away from my God.

23I keep all his laws in mind.

I haven’t turned away from his commands.

24He knows that I am without blame.

He knows I’ve kept myself from sinning.

25The Lord has rewarded me for doing what is right.

He has rewarded me because I haven’t done anything wrong.

26Lord, to those who are faithful you show that you are faithful.

To those who are without blame you show that you are without blame.

27To those who are pure you show that you are pure.

But to those whose paths are crooked you show that you are clever.

28You save those who aren’t proud.

But you watch the proud to bring them down.

29Lord, you are my lamp.

You bring light into my darkness.

30With your help I can attack a troop of soldiers.

With the help of my God I can climb over a wall.

31“God’s way is perfect.

The Lord’s word doesn’t have any flaws.

He protects like a shield

all who go to him for safety.

32Who is God except the Lord?

Who is the Rock except our God?

33God gives me strength for the battle.

He keeps my way secure.

34He makes my feet like the feet of a deer.

He causes me to stand on the highest places.

35He trains my hands to fight every battle.

My arms can bend a bow of bronze.

36Lord, you shield me with your saving help.

Your help has made me great.

37You give me a wide path to walk in

so that I don’t twist my ankles.

38“I chased my enemies and crushed them.

I didn’t turn back until they were destroyed.

39I crushed them completely so that they couldn’t get up.

They fell under my feet.

40Lord, you gave me strength to fight the battle.

You caused my enemies to be humble in front of me.

41You made them turn their backs and run away.

So I destroyed my enemies.

42They cried out for help. But there was no one to save them.

They called out to the Lord. But he didn’t answer them.

43I beat them as fine as the dust of the earth.

I pounded them and walked on them like mud in the streets.

44“You saved me when people attacked me.

You have kept me as the ruler over nations.

People I didn’t know serve me now.

45People from other lands bow down to me in fear.

As soon as they hear about me, they obey me.

46All of them give up hope.

They come trembling out of their hiding places.

47“The Lord lives! Give praise to my Rock!

Give honor to my God, the Rock! He is my Savior!

48He is the God who pays back my enemies.

He brings the nations under my control.

49He sets me free from my enemies.

You have honored me more than them.

You have saved me from a man who wanted to hurt me.

50Lord, I will praise you among the nations.

I will sing your praise.

51He gives his king great victories.

He shows his faithful love to his anointed king.

He shows it to David and his family forever.”