2 ሳሙኤል 20 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

2 ሳሙኤል 20:1-26

ሳቤዔ በዳዊት ላይ ዐመፀ

1በዚህ ጊዜ የቢክሪ ልጅ ስሙ ሳቤዔ የተባለ አንድ ምናምንቴ ብንያማዊ በዚያ ነበረ፤ እርሱም መለከት ነፍቶ እንዲህ ሲል ጮኸ፤ “እኛ ከዳዊት ድርሻ የለንም፤ ከእሴይም ልጅ ርስት የለንም፤ እስራኤል ሆይ፤ እያንዳንድህ ወደ ድንኳንህ ተመለስ!”

2ስለዚህ የእስራኤል ሰው ሁሉ ዳዊትን ከድቶ የቢክሪን ልጅ ሳቤዔን ተከተለ። የይሁዳ ሰዎች ግን ከዮርዳኖስ አንሥቶ እስከ ኢየሩሳሌም ድረስ ከንጉሣቸው ሳይለዩ አብረውት ሄዱ።

3ዳዊት ኢየሩሳሌም ወዳለው ቤተ መንግሥቱ በተመለሰ ጊዜ፤ ቤተ መንግሥቱን እንዲጠብቁ ትቷቸው የሄደውን ዐሥሩን ቁባቶቹን ወሰደ፤ በአንድ ቤትም ውስጥ እንዲጠበቁ አደረገ። ቀለብ ሰጣቸው፤ ይሁን እንጂ ወደ እነርሱ አልገባም ነበር፤ እነርሱም እስከ ሞቱበት ጊዜ ድረስ መበለት ሆነው፣ ለብቻቸው ተገልለው ተቀመጡ።

4ከዚያም ንጉሡ አሜሳይን፣ “የይሁዳ ሰዎች ሁሉ በሦስት ቀን ውስጥ፣ ወደ እኔ እንዲመጡ ጥራልኝ፤ አንተ ራስህም ተገኝ” አለው። 5አሜሳይ ይሁዳን ለመጥራት ሄደ፤ ነገር ግን ንጉሡ ከወሰነው ጊዜ በላይ ቈየ።

6ዳዊትም አቢሳን፣ “ከአቤሴሎም ይልቅ አሁን የቢክሪ ልጅ ሳቤዔ የበለጠ ጕዳት ሊያደርስብን ስለሆነ የጌታህን ሰዎች ይዘህ አሳድደው፤ አለዚያ የተመሸገ ከተማ አግኝቶ ያመልጠናል” አለው። 7ስለዚህ የኢዮአብ ሰዎች፣ ከሊታውያን፣ ፈሊታውያን እንዲሁም ሌሎች ኀያላን ጦረኞች በሙሉ በአቢሳ አዛዥነት ወጡ፤ ከኢየሩሳሌም የወጡትም የቢክሪ ልጅ ሳቤዔን ለማሳደድ ነበር።

8በገባዖን ከታላቁ ቋጥኝ አጠገብ ሳሉ፣ አሜሳይ ሊገናኛቸው መጣ፤ ኢዮአብ የጦር ሜዳ ልብሱን ለብሶ ሰይፉን ከነሰገባው በወገቡ ላይ ታጥቆ ነበር፤ ወደ ፊት ራመድ እንዳለም ሰይፉ ከሰገባው ወጥቶ ወደቀ።

9ኢዮአብም አሜሳይን፣ “ወንድሜ ሆይ፤ እንደ ምንድን ነህ?” አለው፤ ከዚያም አሜሳይን የሚስም መስሎ በቀኝ እጁ ጢሙን ያዘው። 10አሜሳይ ግን በኢዮአብ እጅ ሰይፍ መኖሩን ልብ ስላላለ ጥንቃቄ አላደረገም፤ ስለዚህ ኢዮአብ ሰይፉን ሆዱ ላይ ሻጠበት፤ አንጀቱም መሬት ላይ ተዘረገፈ፤ ከዚያም ኢዮአብ መድገም ሳያስፈልገው፣ አሜሳይ በዚያው ሞተ። ከዚህ በኋላ ኢዮአብና ወንድሙ አቢሳ፣ የቢክሪን ልጅ ሳቤዔን ማሳደድ ጀመሩ።

11በአሜሳይ ሬሳ አጠገብ ከቆሙት ከኢዮአብ ሰዎች አንዱ፤ “ኢዮአብን የሚወድድ፣ የዳዊትም የሆነ ሁሉ ኢዮአብን ይከተል!” አለ። 12በዚህን ጊዜ የአሜሳይ ሬሳ በደም ተጨማልቆ በመንገዱ መካከል ወድቆ ነበር፤ በዚያ የሚያልፈው ሰራዊት ሁሉ መቆሙን ያ ሰው አየ፤ ወደ ሬሳው የደረሰው ሰራዊት ሁሉ መቆሙን በተረዳ ጊዜም፣ የአሜሳይን ሬሳ ከመንገድ ወደ ዕርሻ ፈቀቅ አድርጎ ልብስ ጣል አደረገበት። 13የአሜሳይ ሬሳ ከመንገድ ላይ ከተነሣ በኋላ ሕዝቡ ሁሉ ኢዮአብን ተከትሎ የቢክሪን ልጅ ሳቤዔን ሊያሳድድ ሄደ።

14ሳቤዔም በእስራኤል ነገዶች ሁሉ መካከል ዐልፎ ወደ አቤል ቤትማዓካና ወደ መላው የቢክሪያውያን ግዛት መጣ፤ የቢክሪ ሰዎችም ተሰብስበው ተከተሉት። 15ከኢዮአብ ጋር ያለውም ሰራዊት መጥቶ፣ ሳቤዔን በአቤል ቤትመዓካ በኩል ከበበው፤ በስተ ውጭም እስከ ከተማዪቱ ግንብ ጫፍ ድረስ ዙሪያውን የዐፈር ድልድል ሠሩ፤ ግንቡን ለመናድ በኀይል በሚደበድቡበት ጊዜ፣ 16አንዲት ብልኅ ሴት ድምፅዋን ከፍ አድርጋ፣ “ስሙ! ስሙ! ለኢዮአብ የምነግረው ነገር ስላለ ወደዚህ እንዲመጣ ንገሩት” አለቻቸው። 17ኢዮአብ ወደ እርሷ ሄደ፤ እርሷም፣ “ኢዮአብ አንተ ነህ?” ስትል ጠየቀችው።

እርሱም፣ “አዎን እኔ ነኝ” ብሎ መለሰላት።

እርሷም፣ “እንግዲህ አገልጋይህ የምትለውን አድምጥ” አለችው።

እርሱም፣ “እሺ፣ አደምጣለሁ” አላት።

18ከዚያ በመቀጠልም እንዲህ አለች፤ “በቀድሞው ጊዜ ሰዎች፣ ‘ምክርን ከአቤል ጠይቁ’ ይሉ ነበር፤ ታዲያ እንዳሉትም ይፈጸም ነበር፤ 19በእስራኤል ሰላማዊና ታማኝ ከሆኑ ሰዎች መካከል አንዷ እኔ ነኝ፤ አንተ በእስራኤል እናት የሆነችውን ከተማ ለማጥፋት ትሻለህ፤ የእግዚአብሔርን ርስት ለመዋጥ የፈለግኸው ለምንድን ነው?”

20ኢዮአብም እንዲህ ሲል መለሰ፤ “ይህስ ከእኔ ይራቅ! መዋጡና ማጥፋቱ አሁንም ከእኔ ይራቅ! 21ነገሩስ እንዲህ አይደለም፤ የኰረብታማው የኤፍሬሙ አገር ሰው፣ የቢክሪ ልጅ ሳቤዔ እጁን በንጉሡ በዳዊት ላይ አንሥቷል፤ እናንተ ይህን ሰው ብቻ ስጡኝ እንጂ እኔ ከተማዪቱን ትቼ እሄዳለሁ” አላት።

ሴቲቱም ኢዮአብን፣ “የሰውየው ራስ ተቈርጦ በግንቡ ላይ ይወረወርልሃል” አለችው።

22ከዚህም በኋላ ሴቲቱ ብልኅነት የተሞላበት ምክሯን ይዛ ወደ ሕዝቡ ሁሉ ሄደች፤ እነርሱም የቢክሪን ልጅ የሳቤዔን ራስ ቈርጠው ለኢዮአብ ወረወሩለት፤ ስለዚህ ኢዮአብ መለከቱን ነፋ፤ ሰዎቹም ከከተማዪቱ ርቀው በየአቅጣጫው ተበታተኑ፤ እያንዳንዳቸውም ወደየቤታቸው ሄዱ፤ ኢዮአብም ወደ ንጉሡ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ።

23ኢዮአብ በእስራኤል ሰራዊት ሁሉ ላይ የበላይ ሆነ፤

የዮዳሄ ልጅ በናያስ ደግሞ በከሊታውያንና በፈሊያታውያን ላይ አለቃ ሆነ።

24አዶኒራም20፥24 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ቅጆች (እንዲሁም 1ነገ 4፥6 እና 5፥14 ይመ) ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ዕብራይስጡ ግን፣ አይራም ይላል። በግዳጅ ሥራ ላይ ለተሰማሩት ሰዎች አለቃ ሆነ፤

የአሒሉድ ልጅ ኢዮሣፍጥ ደግሞ ታሪክ ጸሓፊ ሆነ፤

25ሱሳ ጸሓፊ፣

ሳዶቅና አብያታር ካህናት ነበሩ፤

26እንዲሁም የኢያዕር ሰው ዒራስ የዳዊት አማካሪ ነበር።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

撒母耳记下 20:1-26

示巴反叛大卫

1有一个无赖名叫示巴,是便雅悯比基利的儿子,当时刚好在吉甲。他吹响号角,大喊:“我们与大卫毫无关系,耶西儿子的产业没有我们的份。以色列人啊,各自回家去吧!” 2于是,以色列人都离开了大卫,跟随了比基利的儿子示巴。但犹大人仍然紧紧跟随他们的王,从约旦河一直来到耶路撒冷3大卫回到耶路撒冷的宫里,把从前留下来看守王宫的十个妃嫔关进冷宫,供养她们,却不再和她们同房。她们像寡妇一样在软禁中度过余生。

4王对亚玛撒说:“你要在三天内招聚犹大人,跟他们一起来见我。” 5亚玛撒就去招聚犹大人,但他超过了王所定的期限。 6大卫亚比筛说:“现在比基利的儿子示巴对我们带来的危害恐怕比押沙龙还要大。你带领我的部下去捉拿他,免得他占据了坚固的城池,得以逃脱。”

7于是,约押的部下和基利提人、比利提人以及所有的勇士都跟随亚比筛离开耶路撒冷,去追赶比基利的儿子示巴8他们来到基遍的巨石旁,见亚玛撒迎面而来。约押当时身穿战袍,腰间佩刀,他迎上去的时候,刀从鞘中滑落出来。 9约押亚玛撒说:“兄弟,你好吗?”他用右手抓住亚玛撒的胡子,亲吻他。 10亚玛撒毫无防备,被约押一刀刺入肚子,肚破肠流而死。然后,约押和他兄弟亚比筛继续追赶比基利的儿子示巴

11约押的一个部下站在亚玛撒的尸体旁边说:“拥护约押大卫的人来跟随约押吧!” 12亚玛撒的尸体倒在路中间的血泊中。那人见众人驻足围观,便把尸体从路上拖到田里,扔了一件衣服盖上。 13尸体搬走以后,大家都跟随约押去追比基利的儿子示巴

14示巴走遍以色列各支派,一直到伯·玛迦亚比拉城。他的本族比利人都聚集起来跟随他。 15约押率大军来到伯·玛迦,把示巴围困在亚比拉城内,他们修筑攻城的高台,撞击城墙。 16有一个聪明的妇人从城上喊:“请听我说!请听我说!请约押到这边来,我有话要对他说。” 17约押就走上前去,那妇人问道:“你是约押吗?”约押答道:“我就是。”妇人说:“请听婢女说几句。”约押说:“你说吧!” 18妇人说:“古时候人们常说,‘有事到亚比拉去请教,问题都会解决。’ 19我们这座城的人在以色列素来热爱和平、忠心耿耿,你却要毁灭这座大城。你为什么要吞掉耶和华的产业?” 20约押答道:“我根本不想吞掉或毁灭这城。 21以法莲山区比基利的儿子示巴背叛大卫王,你们只要把他交出来,我就撤退。”那妇人说:“我们一定把他的首级从城上抛下来给你。” 22妇人把自己的良策告诉众人,他们便把比基利的儿子示巴的头割下来,抛给约押约押就吹响号角令军队各自回家,自己回耶路撒冷见王。

23约押负责统率以色列全军;耶何耶大的儿子比拿雅统辖基利提人和比利提人; 24亚多兰管理服劳役的;亚希律的儿子约沙法担任史官; 25示法做书记;撒督亚比亚他任祭司; 26雅珥以拉大卫的祭司。