2 ሳሙኤል 2 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

2 ሳሙኤል 2:1-32

ዳዊት የይሁዳ ንጉሥ ሆነ

1ከዚህ በኋላ ዳዊት፣ “ከይሁዳ ከተሞች ወደ አንዲቱ ልውጣን?” ብሎ እግዚአብሔርን ጠየቀ።

እግዚአብሔርም፣ “አዎን ውጣ” አለው።

ዳዊትም፣ “ወደ የትኛዪቱ ልሂድ?” ሲል ጠየቀ።

እግዚአብሔርም፣ “ወደ ኬብሮን” ብሎ መለሰለት።

2ስለዚህ ዳዊት ከሁለቱ ሚስቶቹ ከኢይዝራኤላዊቷ ከአኪናሆምና የቀርሜሎሳዊው የናባል ሚስት ከነበረችው ከአቢግያ ጋር ወደዚያ ወጣ። 3እንዲሁም ዳዊት አብረውት የነበሩትን ሰዎች ከነቤተ ሰቦቻቸው አመጣቸው፤ እነርሱም በኬብሮን ከተሞች ተቀመጡ። 4የይሁዳም ሰዎች ወደ ኬብሮን መጡ፤ በዚያም ዳዊትን ቀብተው በይሁዳ ቤት ላይ አነገሡት።

ሳኦልን የቀበሩት የኢያቢስ ገለዓድ ሰዎች መሆናቸውን ለዳዊት በነገሩት ጊዜ፣ 5እርሱም የኢያቢስ ገለዓድ ሰዎች ይህን እንዲነግሩ መልእክተኞች ላከ፤ “በእንዲህ ዐይነት ሁኔታ ጌታችሁን ሳኦልን በመቅበር በጎነት አሳይታችኋልና እግዚአብሔር ይባርካችሁ፤ 6አሁንም እግዚአብሔር ጽኑ ፍቅሩንና ታማኝነቱን ይግለጥላችሁ፤ እናንተ ይህን ስላደረጋችሁ፣ እኔም እንደዚሁ በጎ ነገር አደርግላችኋለሁ፤ 7እንግዲህ ጠንክሩ፤ በርቱ፤ ጌታችሁ ሳኦል ሞቷልና፤ የይሁዳ ቤትም እኔን ቀብተው በላያቸው አንግሠውኛል።”

በዳዊት ቤትና በሳኦል ቤት መካከል የተደረገ ጦርነት

3፥2-5 ተጓ ምብ – 1ዜና 3፥1-4

8በዚህ ጊዜ የሳኦል ሰራዊት አዛዥ የኔር ልጅ አበኔር፣ የሳኦልን ልጅ ኢያቡስቴን ወስዶ ወደ መሃናይም አሻገረው፤ 9እርሱንም በገለዓድ፣ በአሴር፣ በኢይዝራኤል፣ በኤፍሬምና በብንያም እንዲሁም በእስራኤል ሁሉ ላይ አነገሠው።

10የሳኦል ልጅ ኢያቡስቴ በእስራኤል ላይ በነገሠ ጊዜ ዕድሜው አርባ ዓመት ነበረ፤ ሁለት ዓመትም ገዛ። የይሁዳ ቤት ግን ዳዊትን ተከተለ። 11ዳዊት በኬብሮን ንጉሥ ሆኖ እስራኤልን የገዛው ሰባት ዓመት ከስድስት ወር ነበረ።

12የኔር ልጅ አበኔር፣ ከሳኦል ልጅ ከኢያቡስቴ አገልጋዮች ጋር ሆኖ ከመሃናይም ተነሥተው ወደ ገባዖን ሄዱ። 13እነርሱንም የጽሩያ ልጅ ኢዮአብና የዳዊት ሰዎች ወጥተው በገባዖን ኵሬ አጠገብ ተገናኟቸው፤ አንዱ ወገን በኵሬው ወዲህ ማዶ፣ ሌላው ወገን ደግሞ በኵሬው ወዲያ ማዶ ተቀመጠ።

14ከዚያም አበኔር፣ ኢዮአብን፣ “ከእናንተም ከእኛም ጕልማሶች ይነሡና በፊታችን በጨበጣ ውጊያ ይጋጠሙ” አለው።

ኢዮአብም፣ “ይሁን እሺ ይጋጠሙ” ብሎ መለሰ።

15ስለዚህ ከብንያም ለሳኦል ልጅ ለኢያቡስቴ ዐሥራ ሁለት፣ ለዳዊት ደግሞ ዐሥራ ሁለት ሰዎች ተነሥተው ተቈጠሩ። 16ከዚያም እያንዳንዱ ሰው የባለጋራውን ራስ በመያዝ ሰይፉን በጐኑ እየሻጠበት ተያይዘው ወደቁ። ስለዚህም በገባዖን የሚገኘው ያ ቦታ “የሰይፍ ምድር”2፥16 ዕብራይስጡ፤ ሔልቃዝ ሀዙሪም ይባላል፤ ትርጕሙም፣ የመሻሻጥ ምድር ወይም የጥላቻ ምድር ማለት ነው። ተባለ።

17የዚያን ዕለቱ ጦርነት እጅግ ከባድ ነበር፤ አበኔርና የእስራኤል ሰዎች በዳዊት ሰዎች ድል ሆኑ።

18ሦስቱ የጽሩያ ወንዶች ልጆች ኢዮአብ፣ አቢሳና አሣሄል እዚያው ነበሩ። አሣሄል እንደ ዱር ሚዳቋ በሩጫ ፈጣን ነበረ፤ 19ወደ ቀኝ ወይም ወደ ግራ ሳይል አበኔርን ተከታተለው። 20አበኔርም ወደ ኋላው ዘወር ብሎ በመመልከት፣ “አሣሄል! አንተ ነህ?” ሲል ጠየቀው።

እርሱም፣ “አዎን እኔ ነኝ” ብሎ መለሰለት።

21ከዚያም አበኔር፣ “ወደ ቀኝህ ወይም ወደ ግራህ ዘወር በልና አንዱን ጕልማሳ ይዘህ መሣሪያውን ንጠቀው” አለው። አሣሄል ግን እርሱን መከታተሉን አልተወም ነበር።

22እንደ ገናም አበኔር፣ “እኔን መከታተል ብትተው ይሻልሃል፤ እኔስ ለምን ከመሬት ጋር ላጣብቅህ? ከዚያስ የወንድምህን የኢዮአብን ፊት ቀና ብዬ እንዴት አያለሁ?” አለው።

23አሣሄል ግን መከታተሉን አልተወም፤ ስለዚህ አበኔር በጦሩ ጫፍ ሆዱን ወጋው፣ ጦሩም በጀርባው ዘልቆ ወጣ፤ አሣሄልም እዚያው ወደቀ፤ ወዲያው ሞተ። እያንዳንዱም አሣሄል ወድቆ ወደ ሞተበት ስፍራ ሲደርስ ይቆም ነበር።

24ኢዮአብና አቢሳ ግን አበኔርን ተከታተሉት፤ እያሳደዱም ወደ ገባዖን ምድረ በዳ በሚወስደው መንገድ ከጋይ አጠገብ ወዳለው ወደ አማ ኰረብታ ሲደርሱ ፀሓይ ጠለቀች። 25ከዚያም የብንያም ሰዎች ወደ አበኔር ተሰብስበው ግንባር በመፍጠር በኰረብታው ጫፍ ላይ ተሰለፉ።

26አበኔር ኢዮአብን ጠርቶ፣ “ይህ ሰይፍ ዘላለም ማጥፋት አለበትን? ውጤቱ መራራ መሆኑን አንተስ ሳታውቀው ቀርተህ ነውን? ሰዎችህ ወንድሞቻቸውን ማሳደዱን እንዲያቆሙ ትእዛዝ የማትሰጣቸውስ እስከ መቼ ድረስ ነው?” አለው።

27ኢዮአብም፣ “ሕያው እግዚአብሔርን! ይህን ባትናገር ኖሮ፣ ሰዎቹ እስኪነጋ ድረስ ወንድሞቻቸውን ማሳደዱን ባላቆሙም ነበር”2፥27 ወይም፣ በዚህ ማለዳ ይህን ብትናገር ኖሮ ሰዎቹ ወንድሞቻቸውን ማሳደዱን ባቆሙ ነበር ወይም፣ ይህን ብትናገር ኖሮ ሰዎቹ እስኪነጋ ድረስ ወንድሞቻቸውን ማሳደዱን ባቆሙ ነበር ብሎ መለሰ።

28ስለዚህ ኢዮአብ ቀንደ መለከቱን ነፋ፤ ከዚያም በኋላ ሰዎቹ በሙሉ እስራኤልን ማሳደዱን ተው፤ ውጊያውም በዚሁ አበቃ።

29አበኔርና ሰዎቹም ሌሊቱን ዓረባን ዐልፈው ሄዱ፤ ከዚያም ዮርዳኖስን በመሻገር ቢትሮንን2፥29 ወይም ማለዳ ወይም ሸለቆ የዕብራይስጡ ቃል ትርጕም በትክክል አይታወቅም። ሁሉ ዐልፈው ወደ መሃናይም መጡ።

30ከዚያም ኢዮአብ አበኔርን ማሳደዱን ትቶ ተመለሰ፤ ሰዎቹንም ሁሉ አንድ ላይ በሰበሰባቸው ጊዜ፣ ከዳዊት ሰዎች አሣሄልን ሳይጨምር፣ ዐሥራ ዘጠኝ ሰዎች መጥፋታቸው ታወቀ። 31የዳዊት ሰዎች ግን ከአበኔር ጋር ከነበሩት ሦስት መቶ ስድሳ ብንያማውያን ገደሉ። 32አሣሄልንም ከወደቀበት አንሥተው በቤተ ልሔም በአባቱ መቃብር ቀበሩት። ከዚያም ኢዮአብና ሰዎቹ ሌሊቱን ሁሉ ሲገሠግሡ ዐድረው፣ ሲነጋ ኬብሮን ደረሱ።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

撒母耳记下 2:1-32

大卫做犹大王

1这事以后,大卫求问耶和华:“我可以回到犹大的城邑吗?”耶和华说:“可以。”大卫又问:“我应该回到哪一座城呢?”耶和华说:“希伯仑。” 2大卫就带着他的两个妻子耶斯列亚希暖迦密拿八的遗孀亚比该,一起上到希伯仑3他还把部下和他们的家属一起带去,住在希伯仑地区的城邑。 4犹大人到希伯仑膏立大卫犹大支派的王。

大卫听说是基列·雅比人埋葬了扫罗5就派人去告诉他们:“你们这样厚待你们的主人扫罗,把他安葬,愿耶和华赐福给你们! 6愿耶和华以慈爱和信实待你们,我也会厚待你们,因为你们做了这事。 7现在你们的主扫罗已经死了,犹大支派已经膏立我做他们的王,你们要刚强勇敢。”

大卫家与扫罗家争战

8那时,扫罗的元帅尼珥的儿子押尼珥带着扫罗的儿子伊施波设过河来到玛哈念9立他为王统治基列亚书利耶斯列以法莲便雅悯以色列其余的地方。 10扫罗的儿子伊施波设四十岁登基,统治以色列两年。犹大支派则跟随大卫11大卫希伯仑做王统治犹大支派七年半。

12有一次,尼珥的儿子押尼珥带领扫罗的儿子伊施波设的军队,从玛哈念前往基遍13洗鲁雅的儿子约押带领大卫的军队出来,在基遍池与他们相遇。一方坐在池这边,一方坐在池那边。 14押尼珥约押说:“让双方的青年起来在我们面前较量一下吧。”约押说:“好啊。” 15于是,双方都选了十二人出来, 16他们各自抓住对方的头发,用刀刺对方的肋旁,同归于尽。于是基遍的那个地方叫“刀田”。 17那天,两军恶战,押尼珥以色列人被大卫的人马杀败。 18当时,洗鲁雅的三个儿子约押亚比筛亚撒黑都在场。亚撒黑跑得飞快如鹿, 19他跟在押尼珥后面,不偏不离,穷追不舍。 20押尼珥回头问道:“你是亚撒黑吗?”亚撒黑说:“正是。” 21押尼珥说:“你去追赶别人,夺取他的兵器吧。”但亚撒黑还是穷追不舍。 22押尼珥又对他说:“快走开吧,非逼我杀你吗?我若杀了你,还有何颜面见你哥哥约押呢?” 23亚撒黑还是不肯罢休。押尼珥就用枪柄刺入他的肚腹,穿透了他的后背,他便倒地身亡。众人赶到那里,都停了下来。

24约押亚比筛却继续追赶押尼珥。太阳落山时,他们追到了基亚附近的亚玛山,通往基遍旷野的路旁。 25便雅悯人在押尼珥的带领下聚集在一个山头上。 26押尼珥约押喊道:“我们非要无休止地杀下去吗?难道你不知道这样下去必有苦果吗?你什么时候才命你的人停止追杀自己的同胞呢?” 27约押说:“我凭永活的上帝起誓,你要是不这样说,我们会一直追到天亮。” 28于是,约押吹响号角,所有的人便停止了战斗,不再追赶以色列的军队。

29押尼珥和随从连夜赶路,穿过了亚拉巴,过了约旦河,第二天又马不停蹄地走了一个上午,回到玛哈念30约押追赶押尼珥回来后细点人数,发现除亚撒黑外还损失了十九个人。 31大卫的军队杀了三百六十个跟随押尼珥便雅悯人。 32约押和他的随从把亚撒黑送到伯利恒,葬在他父亲的坟墓里。然后,他们整夜赶路,黎明的时候回到了希伯仑