2 ሳሙኤል 14 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

2 ሳሙኤል 14:1-33

አቤሴሎም ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ

1የጽሩያ ልጅ ኢዮአብ የንጉሡ ልብ አቤሴሎምን እንደ ናፈቀ ተረዳ። 2ስለዚህም ኢዮአብ ወደ ቴቁሔ፤ ሰው ልኮ አንዲት ብልኅ የሆነች ሴት አስመጣ፤ እንዲህም አላት፤ “ሐዘንተኛ በመምሰል የሐዘን ልብስ ልበሺ፤ ዘይት አትቀቢ፤ ለሞተ ሰው ብዙ ጊዜ እንዳዘነች ሴት መስለሽም ታዪ። 3ከዚያም ወደ ንጉሡ ሄደሽ እንዲህ በዪው።” ከዚያም ኢዮአብ የምትናገራቸውን ቃላት ነገራት።

4የቴቁሔዪቱም ሴት ወደ ንጉሡ ገብታ፣14፥4 ብዙ የዕብራይስጥ ቅጆች፣ የሰብዓ ሊቃናት፣ የቩልጌትና የሱርስት ትርጕሞች፣ ሄዳ ይላሉ፤ አብዛኞቹ የዕብራይስጥ ቅጆች ግን፣ ለንጉሡ ተናገረች ይላሉ። በንጉሡ ፊት ወደ መሬት በግምባሯ ተደፍታ እጅ በመንሣት አክብሮቷን ከገለጠች በኋላ፣ “ንጉሥ ሆይ! እርዳኝ” አለች።

5ንጉሡም፣ “ችግርሽ ምንድን ነው?” ብሎ ጠየቃት።

እርሷም እንዲህ አለች፤ “እኔ በርግጥ ባሌ የሞተብኝ መበለት ነኝ፤ 6እኔ አገልጋይህ ሁለት ወንዶች ልጆች ነበሩኝ፤ ሜዳ ላይ እርስ በርሳቸው ተጣሉ፤ ገላጋይም ስላልነበረ፣ አንዱ ሌላውን መትቶ ገደለው። 7እነሆ ቤተ ዘመዱ ሁሉ በባሪያህ ላይ ተነሥተው፣ ‘ወንድሙን ስለ ገደለ እንገድለዋለንና ወንድሙን የገደለውን ሰው አሳልፈሽ ስጪን፣ ከዚያም ወራሽ አልባ ትሆኛለሽ’ ይሉኛል፤ ስለዚህ የቀረኝን አንዱን መብራቴን አጥፍተው፣ ባሌን በምድር ላይ ያለ ስምና ያለ ዘር ሊያስቀሩት ነው።”

8ንጉሡም ሴቲቱን፣ “አንቺ ወደ ቤትሽ ሂጂ፤ ስለ ጕዳይሽ አስፈላጊውን ትእዛዝ እሰጣለሁ” አላት። 9ነገር ግን የቴቁሔዪቱም ሴት፣ “ንጉሥ ጌታዬ፣ በደሉ በእኔና በአባቴ ቤተ ሰብ ላይ ይሁን፤ ንጉሡና ዙፋኑ ከበደል የነጹ ይሁኑ” አለች።

10ንጉሡም፣ “ማንም ሰው አንዳች ነገር ቢናገርሽ እኔ ዘንድ አምጪው፤ ዳግም አያስቸግርሽም” ሲል መለሰላት።

11እርሷም፣ “ደም ተበቃዮቹ ልጄን በማጥፋት የባሰ ጕዳት እንዳያደርሱ፣ ንጉሡ አምላኩን እግዚአብሔርን ይለምን” አለች።

ንጉሡም፣ “ሕያው እግዚአብሔርን! ከልጅሽ ራስ ላይ አንዲት ጠጕር እንኳ አትነካም” አላት።

12ከዚያም ሴቲቱ፣ “እኔ አገልጋይህ ለጌታዬ ለንጉሡ አንዲት ቃል እንድናገር ፍቀድልኝ” አለችው። እርሱም፣ “እሺ ተናገሪ” አላት።

13ሴቲቱም መልሳ እንዲህ አለችው፣ “እንዲህ ያለውን ነገር በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይ ያሰብኸው ለምንድን ነው? ንጉሡ ከአገር የተሰደደውን ልጁን አልመለሰውም፤ ታዲያ ይህን ሲናገር በራሱ ላይ መፍረዱ አይደለምን? 14በመሬት ላይ የፈሰሰ ውሃ እንደማይታፈስ ሁሉ፣ እኛም እንደዚሁ እንሞታለን፤ እግዚአብሔር ግን ከአገር የተሰደደ ሰው ከእርሱ እንደ ራቀ በዚያው እንዳይቀር የሚመለስበትን ሁኔታ ያመቻቻል እንጂ ሕይወቱ እንድትጠፋ አይፈቅድም።

15“አሁንም ወደዚህ የመጣሁት ሕዝቡ ስላስፈራኝ ይህንኑ ለንጉሥ ጌታዬ ለመንገር ነው። እኔም አገልጋይህ ይህን አሰብሁ፤ ‘ለንጉሡ እነግረዋለሁ፤ ምናልባትም አገልጋዩ የጠየቀችውን ይፈጽምላት ይሆናል፤ 16እግዚአብሔር ከሰጠን ርስት እኔንም ልጄንም ሊነቅለን ከተነሣው ሰው እጅ ንጉሡ አገልጋዩን ሊታደግ ይፈቅድ ይሆናል።’

17“አሁንም አገልጋይህ፤ ‘ንጉሥ ጌታዬ በጎውንና ክፉውን በመለየት እንደ እግዚአብሔር መልአክ ስለሆነ፣ የጌታዬ የንጉሡ ቃል ያጽናናኝ፤ እግዚአብሔር አምላክህም ካንተው ጋር ይሁን’ ትላለች።”

18ከዚያም ንጉሡ ሴቲቱን፣ “እኔም ለምጠይቅሽ ነገር አንቺም መልሱን አትደብቂኝ” አላት።

ሴቲቱም፣ “ንጉሥ ጌታዬ፤ እሺ ይናገር” አለችው።

19ንጉሡም፣ “በዚህ ሁሉ የኢዮአብ እጅ የለበትምን?” ሲል ጠየቃት።

ሴቲቱም መልሳ እንዲህ አለች፤ “ንጉሥ ጌታዬ ሆይ በሕያው ነፍስህ እምላለሁ፤ ንጉሥ ጌታዬ ከተናገረው ሁሉ ወደ ቀኝም ወደ ግራም የሚል ማንም የለም። አዎን ይህን እንዳደርግ ያዘዘኝና ይህም ሁሉ ቃል በእኔ በአገልጋይህ አንደበት እንዲነገር የላከኝ አገልጋይህ ኢዮአብ ነው። 20አገልጋይህ ኢዮአብ ይህን ያደረገውም ያለውን ሁኔታ ለመለወጥ ሲል ነው፤ ነገር ግን ጌታዬ የእግዚአብሔርን መልአክ ጥበብ የመሰለ ጥበብ ስላለው፣ በምድሪቱ ላይ የሚሆነውን ነገር ሁሉ ያውቃል።”

21ንጉሡም ኢዮአብን፣ “መልካም ነው፤ ፈቅጃለሁ፤ ሂድና ወጣቱን አቤሴሎምን መልሰህ አምጣው” አለው።

22ኢዮአብም አክብሮቱን ለንጉሡ ለመግለጥ ወደ መሬት በግምባሩ ተደፍቶ እጅ ነሣ፤ ንጉሡንም ባረከ፣ ኢዮአብም በመቀጠል፣ “ንጉሡ የአገልጋዩን ልመና ስለ ተቀበለው፣ ባሪያህ በፊትህ ሞገስ ማግኘቱን ዛሬ ለማወቅ ችሏል” አለ። 23ከዚያም ኢዮአብ ወደ ጌሹር ሄዶ አቤሴሎምን ወደ ኢየሩሳሌም መልሶ አመጣው። 24ንጉሡ ግን፣ “እዚያው እቤቱ ይሂድ፤ ዐይኔን ማየት የለበትም” አለ። ስለዚህም አቤሴሎም ወደ ቤቱ ሄደ፤ የንጉሡንም ፊት አላየም።

25መቼም በመልኩ ማማር አቤሴሎምን የሚያህል አንድም ሰው በመላው እስራኤል አልነበረም፤ ከራስ ጠጕሩ እስከ እግር ጥፍሩ የሚወጣለት እንከን አልነበረም። 26የራስ ጠጕሩ ሲከብደው በዓመት አንድ ጊዜ ይቈርጠው ነበር፤ የተቈረጠውን በሚመዝነው ጊዜ ክብደቱ በቤተ መንግሥቱ ሚዛን ሁለት መቶ ሰቅል14፥26 2.3 ኪሎ ግራም ያህል ነው። ይሆን ነበር።

27አቤሴሎም ሦስት ወንዶች ልጆችና ትዕማር የተባለች አንዲት ሴት ልጅ ተወለዱለት፤ ሴት ልጁም በጣም ውብ ነበረች።

28አቤሴሎም የንጉሡን ዐይን ሳያይ ሁለት ዓመት በኢየሩሳሌም ኖረ። 29ከዚያም አቤሴሎም ወደ ንጉሡ እንዲሄድለት ኢዮአብን አስጠራው፤ ኢዮአብ ግን ወደ እርሱ መምጣት አልፈለገም፤ ለሁለተኛ ጊዜም ላከበት፤ ኢዮአብ አሁንም መምጣት አልፈለገም። 30ከዚያም አቤሴሎም ለአገልጋዮቹ “ተመልከቱ የኢዮአብ ዕርሻ የሚገኘው ከእኔ ዕርሻ አጠገብ ነው፤ በዕርሻው ላይ የገብስ አዝመራ አለው፤ ሄዳችሁም እሳት ልቀቁበት” አላቸው። ስለዚህ የአቤሴሎም አገልጋዮች ሄደው የኢዮአብን ዕርሻ በእሳት አቃጠሉት።

31ከዚያም ኢዮአብ ወደ አቤሴሎም ቤት ሄደ፣ “አገልጋዮችህ ለምንድን ነው ዕርሻዬን ያቃጠሉት?” ብሎ ጠየቀው።

32አቤሴሎምም፣ ኢዮአብን፣ “ከጌሹር ለምን መጣሁ? ‘ለእኔ እስካሁንም እዚያው ብሆን ይሻለኝ ነበር ብሏል ብለህ እንድትነግርልኝ ወደ ንጉሡ እልክህ ዘንድ ወደ እኔ ና’ ብዬ አስጠራሁህ፤ አሁንም ቢሆን፤ የንጉሡን ዐይን ማየት እፈልጋለሁ፤ ምንም ዐይነት በደል ከተገኘብኝ ይግደለኝ” አለው።

33ኢዮአብም ወደ ንጉሡ ሄዶ ይህንኑ ነገረው። ከዚያም ንጉሡ አቤሴሎምን አስጠራው፤ እርሱም መጥቶ በንጉሡ ፊት በግምባሩ ተደፍቶ እጅ ነሣ፤ ንጉሡም አቤሴሎምን ሳመው።

Thai New Contemporary Bible

2ซามูเอล 14:1-33

อับซาโลมกลับมาเยรูซาเล็ม

1ครั้นโยอาบบุตรนางเศรุยาห์ทราบว่ากษัตริย์ทรงคิดถึงอับซาโลมมาก 2เขาจึงใช้คนไปตามตัวหญิงฉลาดคนหนึ่งจากเทโคอาให้มาพบและกล่าวกับนางว่า “จงแกล้งทำเป็นว่าเจ้าไว้ทุกข์อยู่ สวมเสื้อผ้าไว้ทุกข์ ไม่ใช้เครื่องประทินโฉม ทำทีว่าเจ้าเศร้าโศกเสียใจอย่างหนักมาหลายวันเพราะคนตาย 3แล้วไปเข้าเฝ้ากษัตริย์ กราบทูลตามที่เราสั่ง” แล้วโยอาบก็สอนคำพูดให้หญิงนั้น

4เมื่อหญิงจากเทโคอามาเข้าเฝ้าดาวิด ก็หมอบซบลงที่พื้นถวายคำนับและทูลว่า “ข้าแต่กษัตริย์โปรดทรงช่วยหม่อมฉันด้วยเถิด”

5กษัตริย์ตรัสถามว่า “เจ้ามีเรื่องทุกข์ร้อนอะไรหรือ?”

นางทูลว่า “หม่อมฉันเป็นม่าย สามีตายไปแล้ว 6มีลูกชายสองคน เขาทะเลาะกันที่กลางทุ่ง เนื่องจากไม่มีคนคอยห้ามเขา คนหนึ่งก็เลยถูกฆ่าตาย 7ตอนนี้ญาติพี่น้องทั้งหมดเรียกร้องให้หม่อมฉันมอบตัวลูกชายเพื่อนำตัวไปประหารโทษฐานฆ่าคน จะได้กำจัดทายาทไป พวกเขาจะดับถ่านไฟก้อนเดียวที่หม่อมฉันเหลืออยู่ เห็นทีสามีหม่อมฉันจะไร้ผู้สืบสกุลเป็นแน่”

8ดาวิดตรัสกับหญิงนั้นว่า “จงกลับไปบ้าน เราจะสั่งการให้เจ้า”

9แต่หญิงจากเทโคอาทูลว่า “ข้าแต่กษัตริย์ เจ้านายของหม่อมฉันขอให้คำตำหนิตกอยู่ที่หม่อมฉันและครอบครัวของบิดาของหม่อมฉัน ส่วนกษัตริย์และราชบัลลังก์ขอให้พ้นมลทินทั้งปวง”

10ดาวิดตรัสว่า “หากผู้ใดกล่าวอะไรกับเจ้า จงนำตัวเขามาพบเรา เขาจะไม่มากวนใจเจ้าอีกเลย”

11นางทูลว่า “ขอฝ่าพระบาทตรัสในพระนามพระยาห์เวห์พระเจ้าของเขา อย่าให้มีการสูญเสียเลือดเนื้ออีกนอกเหนือจากที่ได้สูญเสียไปแล้ว ลูกชายของหม่อมฉันจะได้ไม่ต้องเสียชีวิต”

ดาวิดตรัสว่า “องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงพระชนม์อยู่แน่ฉันใด ผมสักเส้นบนหัวลูกชายของเจ้า เราก็จะไม่ยอมให้ตกถึงดินฉันนั้น”

12นางทูลว่า “โปรดทรงอนุญาตให้หม่อมฉันทูลสักคำ”

ดาวิดตรัสตอบว่า “พูดมาเถิด”

13หญิงนั้นทูลว่า “ก็แล้วทำไมฝ่าพระบาททรงทำเช่นนี้ต่อประชากรของพระเจ้า? เมื่อฝ่าพระบาทตรัสเช่นนี้ เท่ากับตัดสินว่าฝ่าพระบาทเองเป็นฝ่ายผิด เพราะฝ่าพระบาทไม่ทรงยอมให้ราชโอรสที่ถูกเนรเทศไปนั้นกลับมา 14คนเราล้วนต้องตายไปเหมือนน้ำหกรดแผ่นดิน จะรวบรวมคืนมาอีกไม่ได้ แต่พระเจ้าไม่ได้ทรงริบเอาชีวิตไป แต่ทรงคิดหาหนทางไม่ให้คนที่ถูกเนรเทศไปต้องถูกตัดขาดจากพระองค์

15“ที่หม่อมฉันมาทูลฝ่าพระบาทก็เพราะมีคนมาข่มขู่ หม่อมฉันบอกตัวเองว่า ‘หม่อมฉันจะทูลกษัตริย์ บางทีพระองค์อาจจะทำตามที่ผู้รับใช้ทูลขอ 16บางทีกษัตริย์อาจจะทรงเห็นชอบที่จะช่วยผู้รับใช้ของพระองค์ให้พ้นจากมือของคนที่พยายามตัดหม่อมฉันกับลูกจากมรดกที่พระเจ้าประทานแก่พวกหม่อมฉัน’

17“และบัดนี้ผู้รับใช้ของฝ่าพระบาทขอทูลว่า ‘พระดำรัสของฝ่าพระบาททำให้หม่อมฉันสบายใจ เพราะฝ่าพระบาทเป็นเสมือนทูตของพระเจ้าที่แยกแยะความดีจากความชั่ว ขอพระยาห์เวห์พระเจ้าของฝ่าพระบาทสถิตกับฝ่าพระบาทเถิด’ ”

18แล้วกษัตริย์ตรัสกับหญิงนั้นว่า “อย่าปิดบัง เราจะถามอะไรเจ้าสักอย่างหนึ่ง”

นางทูลว่า “โปรดตรัสเถิด”

19ดาวิดตรัสว่า “ทั้งหมดนี้โยอาบเป็นผู้หนุนหลังเจ้าใช่หรือไม่?”

หญิงนั้นทูลว่า “ข้าแต่กษัตริย์ เจ้านายของหม่อมฉัน ฝ่าพระบาททรงพระชนม์อยู่แน่ฉันใด ไม่มีใครสามารถพลิกซ้ายหันขวาจากสิ่งใดๆ ที่ฝ่าพระบาทตรัสได้ฉันนั้น ถูกแล้วโยอาบผู้รับใช้ของฝ่าพระบาทคือผู้สอนให้หม่อมฉันทำตามนี้ และแนะนำทุกถ้อยคำที่ออกจากปากของหม่อมฉัน 20โยอาบผู้รับใช้ของฝ่าพระบาททำเช่นนี้เพื่อพลิกสถานการณ์ ฝ่าพระบาททรงพระปรีชาเสมือนทูตของพระเจ้า และทรงทราบเหตุการณ์ทุกอย่างในแผ่นดิน”

21กษัตริย์จึงตรัสกับโยอาบว่า “ดีมาก เราจะทำตามนั้น จงไปรับตัวอับซาโลมชายหนุ่มคนนั้นกลับมาเถิด”

22โยอาบก็หมอบกราบซบหน้าลงกับพื้นถวายคำนับ ถวายพระพรและทูลว่า “บัดนี้ข้าพระบาททราบแล้วว่า ฝ่าพระบาททรงกรุณาข้าพระบาท เพราะทรงให้ตามที่ข้าพระบาททูลขอ”

23โยอาบจึงไปยังเกชูร์และรับตัวอับซาโลมกลับมายังเยรูซาเล็ม 24แต่กษัตริย์ตรัสว่า “ให้เขาไปอยู่ที่ตำหนักของเขา อย่ามาให้เราเห็นหน้า” อับซาโลมจึงไปพำนักที่ตำหนักของตนและไม่ได้เข้าเฝ้ากษัตริย์

25ทั่วอิสราเอลไม่มีใครได้รับคำชมว่าเป็นชายชาตรีรูปงามเท่าอับซาโลม ตั้งแต่เส้นผมจดปลายเท้าไม่มีตำหนิเลยแม้แต่น้อย 26เมื่อใดที่ผมของเขาหนักมาก เขาก็จะตัดออกมาชั่งดู ผมนั้นหนักประมาณ 2.3 กิโลกรัม14:26 ภาษาฮีบรูว่า200 เชเขลตามพิกัดหลวง

27อับซาโลมมีบุตรชายสามคนและมีบุตรสาวหนึ่งคนชื่อว่าทามาร์ นางมีรูปโฉมงดงามยิ่งนัก

28ตลอดสองปีที่อับซาโลมอยู่ในเยรูซาเล็ม เขาไม่ได้เข้าเฝ้ากษัตริย์เลย 29อับซาโลมจึงให้คนไปตามตัวโยอาบมาเพื่อให้เข้าเฝ้ากษัตริย์แทน แต่โยอาบไม่ยอมมา แม้อับซาโลมให้คนไปตามอีก เขาก็ยังคงไม่มา 30อับซาโลมจึงสั่งบริวารว่า “ไปจุดไฟเผานาข้าวบาร์เลย์ของโยอาบที่อยู่ถัดจากเราไป” เขาก็ปฏิบัติตาม

31โยอาบจึงมาพบอับซาโลมที่ตำหนัก และเรียนว่า “เหตุใดบริวารของท่านไปจุดไฟเผานาของข้าพเจ้า?”

32อับซาโลมกล่าวกับโยอาบว่า “เราส่งคนไปหาท่านและกล่าวว่า ‘มาที่นี่เถิด จะได้ให้ท่านช่วยไปทูลถามกษัตริย์ว่า “ทรงรับตัวอับซาโลมกลับมาจากเกชูร์ทำไม เขาอยู่ที่นั่นยังดีเสียกว่า!” ’ เราต้องการเข้าเฝ้ากษัตริย์สักครั้ง หากเราผิดด้วยเรื่องใดก็ให้พระองค์ประหารเราเถิด”

33โยอาบจึงไปกราบทูลกษัตริย์ตามนี้ ดาวิดจึงทรงเรียกตัวอับซาโลมมาเข้าเฝ้า อับซาโลมเข้ามาหมอบกราบซบหน้าลงถึงพื้นต่อหน้ากษัตริย์และกษัตริย์ทรงจูบอับซาโลม