2 ሳሙኤል 11 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

2 ሳሙኤል 11:1-27

ዳዊትና ቤርሳቤህ

1ነገሥታት ለጦርነት በሚወጡበት፣ በጸደይ ወራት ዳዊት ኢዮአብን ከንጉሡ ሰዎችና ከመላው የእስራኤል ሰራዊት ጋር አዘመተው፤ እነርሱም አሞናውያንን አጠፉ፤ ረባት የተባለችውንም ከተማ ከበቡ፤ በዚህ ጊዜ ግን ዳዊት በኢየሩሳሌም ቀርቶ ነበር።

2አንድ ቀን ማታ፣ ዳዊት ከዐልጋው ተነሥቶ በቤተ መንግሥቱ ሰገነት ወዲያና ወዲህ ይመላለስ ነበር፤ ከሰገነቱ ላይ እንዳለም፣ አንዲት ሴት ገላዋን ስትታጠብ አየ፤ ሴቲቱም እጅግ በጣም ውብ ነበረች። 3ዳዊትም ሰው ልኮ ስለ ሴቲቱ አጠያየቀ። ሰውየውም፣ “ይህች የኤልያብ ልጅ፣ የኬጢያዊው የኦርዮ ሚስት ቤርሳቤህ አይደለችምን?” አለ። 4ከዚያም ዳዊት መልእክተኞች ልኮ አስመጣት፤ እርሱ ወዳለበት ገባች፤ አብሯትም ተኛ። በዚህም ጊዜ ወርኃዊ የመንጻት ጊዜዋን ፈጽማ ነበር። ከዚያም ተመልሳ ወደ ቤቷ ሄደች። 5ሴቲቱ ፀነሰች፤ ለዳዊትም፣ “አርግዣለሁ” ብላ ላከችበት።

6ስለዚህም ዳዊት ለኢዮአብ፣ “ኬጢያዊውን ኦርዮን ወደ እኔ ስደደው” ሲል ላከበት፤ ኢዮአብም ወደ ዳዊት ላከው። 7ኦርዮን በመጣ ጊዜም፣ ዳዊት የኢዮአብንና የሰራዊቱን ሁሉ ደኅንነት እንዲሁም ጦርነቱ እንዴት እየተካሄደ እንዳለ ጠየቀው። 8ከዚያም ዳዊት ኦርዮን፣ “በል እንግዲህ ወደ ቤትህ ወርደህ እግርህን ታጠብ” አለው። ኦርዮን ከቤተ መንግሥት ተሰናብቶ ወጣ፤ ንጉሡም ማለፊያ ምግብ አስከትሎ ላከለት። 9ነገር ግን ኦርዮ ከጌታው አገልጋዮች ሁሉ ጋር በቤተ መንግሥቱ ቅጽር በር ተኛ እንጂ፣ ወደ ቤቱ አልወረደም ነበር።

10ዳዊት፣ “ኦርዮን ወደ ቤቱ አልሄደም” መባሉን ሲሰማ ኦርዮን፣ “ከመንገድ ገና አሁን መግባትህ አይደለምን? ወደ ቤትህ ያልሄድኸው ለምንድን ነው?” ሲል ጠየቀው።

11ኦርዮም ዳዊትን፣ “ታቦቱ፣ እስራኤልና ይሁዳ በድንኳን ሆነው፣ ጌታዬ ኢዮአብና የጌታዬም ሰዎች አውላላ ሜዳ ላይ ሰፍረው፣ ለመብላትና ለመጠጣት እንዲሁም ከሚስቴ ጋር ለመተኛት እንዴት ወደ ቤቴ እሄዳለሁ? እንዲህ ያለውን ነገር እንደማላደርገው በነፍስህ እምላለሁ” አለው።

12ከዚያም ዳዊት፣ “እንግዲያውስ ዛሬ እዚህ ዕደርና ነገ አሰናብትሃለሁ” አለው። ስለዚህ ኦርዮን በዚያ ዕለትና በማግስቱም እዚያው ኢየሩሳሌም ቈየ። 13በማግስቱም ዳዊት ራሱ ባለበት ግብዣ አድርጎለት በላ፤ ጠጣ፤ አሰከረውም፤ ሲመሽም ኦርዮን በምንጣፉ ላይ ለመተኛት የጌታው አሽከሮች ወዳሉበት ወጥቶ ሄደ እንጂ ወደ ቤቱ አልወረደም።

14ሲነጋም ዳዊት ለኢዮአብ ደብዳቤ ጽፎ በኦርዮን እጅ ላከለት፤ 15በደብዳቤውም ላይ፣ “ኦርዮ ውጊያው በተፋፋመበት ግንባር መድበው፤ ከዚያም ተወግቶ እንዲሞት ትታችሁት ሽሹ” ብሎ ጻፈ።

16ስለዚህም ኢዮአብ ከተማዪቱን በከበባት ጊዜ፣ እጅግ ጠንካራ ተከላካዮች እንዳሉበት በሚያውቀው ግንባር ኦርዮን መደበው። 17የከተማዪቱም ሰዎች ወጥተው ከኢዮአብ ጋር ጦርነት ገጠሙ፤ ከዳዊት ሰራዊት ውስጥ ጥቂቶቹ ወደቁ፤ እንዲሁም ኬጢያዊው ኦርዮም ሞተ።

18ኢዮአብም በጦርነቱ የሆነውን ሁሉ ለዳዊት ላከ። 19መልእክተኛውንም እንዲህ አለው፤ “ይህን የጦርነቱን ወሬ ለንጉሡ ከነገርኸው በኋላ፣ 20ንጉሡ በቍጣ ቱግ ብሎ ‘ለመዋጋት ስትሉ ይህን ያህል ወደ ከተማዪቱ የተጠጋችሁት ስለ ምንድን ነው? ከግንቡ ቅጥር በላይ ፍላጻ እንደሚሰድዱባችሁ አታውቁም ኖሯል? 21የይሩቤሼትን11፥21 ጌዴዎን፣ ይሩበአል በመባልም ይታወቃል። ልጅ አቤሜሌክን የገደለው ማነው? በቴቤስ ከግንብ ቅጥር የወፍጮ መጅ ለቅቃበት የገደለችው አንዲት ሴት አይደለችምን? ታዲያ እናንተስ ወደ ግንቡ ቅጥር ይህን ያህል የተጠጋችሁት ለምንድን ነው?’ በማለት ቢጠይቅህ፣ አንተም መልሰህ፣ ‘አገልጋይህ ኬጢያዊው ኦርዮም ሞቷል’ ብለህ ንገረው።”

22ስለዚህ መልእክተኛው ተነሥቶ ሄደ፤ እዚያ እንደ ደረሰም፣ ከኢዮአብ የተቀበለውን መልእክት በሙሉ ለዳዊት ነገረው። 23መልእክተኛውም ለዳዊት እንዲህ አለው፤ “ሰዎቹ ዐየሉብን፤ እኛንም ለመውጋት ወጥተው እስከ ሜዳው ድረስ መጡ፤ እኛ ግን እስከ ከተማዪቱ ቅጽር መግቢያ ድረስ አሳድደን መለስናቸው። 24ከዚያም ባለ ፍላጻዎቹ ከግንቡ ላይ ሆነው በእኛ በአገልጋዮችህ ላይ ቀስት ስለ ለቀቁ፣ ከንጉሡ አገልጋዮች ጥቂቶቹን ገደሉ፤ አገልጋይህ ኬጢያዊው ኦርዮም ሞተ።”

25ዳዊትም፣ መልእክተኛውን፣ “እንግዲህ እንዲህ ብለህ ይህን ለኢዮአብ ንገረው፤ ‘መቼም ሰይፍ አንድ ጊዜ ይህን፣ ሌላ ጊዜም ሌላውን ትበላለችና በዚህ አትዘን’ ” አለው።

26የኦርዮን ሚስት ባሏ መሞቱን በሰማች ጊዜ ዐዘነች፤ አለቀሰችለትም። 27የሐዘኑ ጊዜ ካበቃ በኋላም፣ ዳዊት ልኮ ቤርሳቤህን ወደ ቤቱ አስመጣት፤ ሚስቱ ሆነች፤ ወንድ ልጅም ወለደችለት፤ ነገር ግን ዳዊት የሠራው ሥራ እግዚአብሔርን አላስደሰተውም ነበር።

Thai New Contemporary Bible

2ซามูเอล 11:1-27

ดาวิดกับนางบัทเชบา

1ในฤดูใบไม้ผลิอันเป็นช่วงที่กษัตริย์ทั้งหลายมักออกไปรบ ดาวิดทรงส่งโยอาบกับคนของพระองค์และกองทัพอิสราเอลทั้งหมดไปทำลายชาวอัมโมน พวกเขาล้อมเมืองรับบาห์ แต่ดาวิดยังคงประทับอยู่ที่กรุงเยรูซาเล็ม

2เย็นวันหนึ่งดาวิดเสด็จจากแท่นบรรทม ทรงดำเนินไปรอบๆ ดาดฟ้าพระราชวัง จากที่นั่นพระองค์ทรงสังเกตเห็นสตรีงดงามมากผู้หนึ่งกำลังอาบน้ำอยู่ 3ดาวิดทรงใช้คนไปสืบดูว่านางเป็นใคร คนนั้นก็มาทูลว่า “นางคือบัทเชบาบุตรสาวของเอลีอัม เป็นภรรยาของอุรียาห์ชาวฮิตไทต์ไม่ใช่หรือ?” 4ดาวิดจึงให้คนไปตามตัวนางมา และเมื่อนางมาเข้าเฝ้าก็ทรงร่วมหลับนอนกับนาง (นางเพิ่งเสร็จจากการชำระตัวหลังมีมลทิน) แล้ว11:4 หรือกับนาง เมื่อนางได้ชำระตัวจากมลทินแล้วนางก็กลับบ้าน 5เมื่อนางพบว่าตนตั้งครรภ์ก็ส่งข่าวมาถึงดาวิดทูลว่า “หม่อมฉันตั้งครรภ์”

6ดาวิดส่งข้อความไปยังโยอาบว่า “จงส่งตัวอุรียาห์ชาวฮิตไทต์มาพบเรา” โยอาบก็ส่งเขามาเข้าเฝ้าดาวิด 7เมื่ออุรียาห์มาถึง ดาวิดก็ตรัสถามถึงโยอาบและกองทัพว่าเป็นอย่างไรบ้าง สงครามคืบหน้าไปถึงไหน 8แล้วดาวิดตรัสสั่งอุรียาห์ว่า “จงกลับไปบ้านพักผ่อนเถิด” อุรียาห์จึงออกจากพระราชวัง และดาวิดให้คนนำของกำนัลตามหลังเขาไป 9แต่อุรียาห์ไม่ได้กลับบ้าน เขาค้างคืนอยู่ที่ประตูวังร่วมกับข้าราชบริพารคนอื่นๆ

10เมื่อดาวิดทรงทราบว่าอุรียาห์ไม่ได้กลับบ้านก็ตรัสถามเขาว่า “เจ้าเพิ่งกลับมาจากแดนไกลไม่ใช่หรือ? ทำไมจึงไม่กลับบ้าน?”

11อุรียาห์ทูลว่า “หีบพันธสัญญาและอิสราเอลกับยูดาห์ล้วนอยู่ในเต็นท์ ท่านแม่ทัพโยอาบและไพร่พลของฝ่าพระบาทล้วนตั้งค่ายอยู่กลางแจ้ง ควรหรือที่ข้าพระบาทจะกลับบ้าน กินดื่ม และหลับนอนกับภรรยา? ฝ่าพระบาททรงพระชนม์อยู่แน่ฉันใด ข้าพระบาทจะไม่ทำเช่นนั้นเด็ดขาดฉันนั้น!”

12ดาวิดตรัสว่า “เอาล่ะ คืนนี้ค้างเสียที่นี่เถิด แล้วพรุ่งนี้เราจะส่งเจ้ากลับไป” ฉะนั้นอุรียาห์จึงค้างอยู่ที่กรุงเยรูซาเล็มในวันนั้นและวันต่อมา 13ดาวิดเรียกให้เขาร่วมโต๊ะเสวยและทรงมอมเหล้าเขา แต่เย็นวันนั้นอุรียาห์ก็ออกไปนอนบนเสื่อท่ามกลางข้าราชบริพารอื่นๆ ไม่ได้กลับบ้าน

14เช้าวันรุ่งขึ้นดาวิดทรงส่งสาส์นถึงโยอาบ มอบให้อุรียาห์เป็นผู้ถือไป 15ในสาส์นนั้นพระองค์ทรงเขียนว่า “จงส่งตัวอุรียาห์ออกไปที่ด้านหน้าของแนวรบที่อันตรายที่สุด แล้วถอยทัพปล่อยให้เขาถูกฆ่าตาย”

16ขณะล้อมเมืองอยู่ โยอาบจึงมอบหมายให้อุรียาห์ไปยังตำแหน่งที่รู้ว่าศัตรูเข้มแข็งที่สุด 17ชาวเมืองนั้นก็ออกมาสู้รบกับโยอาบ แล้วอุรียาห์ชาวฮิตไทต์ก็ถูกฆ่าตายพร้อมกับทหารบางคนของดาวิด

18เมื่อโยอาบส่งรายงานการสู้รบมาทูลดาวิด 19เขากำชับผู้สื่อสารว่า “เมื่อเจ้าทูลรายงานจบแล้ว 20กษัตริย์อาจจะกริ้วและตรัสถามว่า ‘ทำไมพวกทหารถึงเข้าไปประชิดเมืองมากนักล่ะ? ไม่รู้หรือว่าอาจจะถูกธนูยิงมาจากกำแพง? 21อาบีเมเลคบุตรเยรุบเบเชท11:21 เป็นที่รู้จักในอีกชื่อหนึ่งว่าเยรุบบาอัล(คือ กิเดโอน)ก็ถูกฆ่าตายมาแล้วที่เธเบศโดยน้ำมือผู้หญิงที่ทุ่มหินโม่ลงมาจากกำแพงไม่ใช่หรือ? แล้วทำไมพวกเจ้าจึงเข้าไปชิดกำแพงมากนักเล่า?’ ถ้าพระองค์ตรัสถามเช่นนี้ ก็จงทูลว่า ‘อุรียาห์ชาวฮิตไทต์คนรับใช้ของฝ่าพระบาทถูกฆ่าตายแล้ว’”

22ผู้สื่อสารจึงเดินทางมาเข้าเฝ้า และกราบทูลดาวิดตามที่โยอาบสั่งทุกอย่าง 23เขาทูลดาวิดว่า “ข้าศึกมีกำลังเหนือกว่าเราและออกมาสู้กับเราที่นอกเมือง แต่เรารุกไล่เขากลับไปที่ทางเข้าประตูเมือง 24คนบนกำแพงยิงธนูเข้าใส่เรา ฝ่ายเราถูกฆ่าตายไปบ้าง แล้วอุรียาห์ชาวฮิตไทต์ก็ตายด้วย”

25ดาวิดตรัสกับผู้สื่อสารว่า “บอกโยอาบว่า ‘อย่าท้อใจในเรื่องนี้ ดาบฆ่าคนไม่เลือกหน้า จงโจมตีเมืองนั้นต่อไปและทำลายเสีย’ จงพูดอย่างนี้เพื่อให้กำลังใจโยอาบด้วย”

26เมื่อภรรยาของอุรียาห์ได้ยินว่าสามีตายแล้ว นางก็ไว้ทุกข์ให้เขา 27และเมื่อครบกำหนดไว้ทุกข์ ดาวิดก็ส่งคนไปรับตัวนางมาเป็นมเหสี พระนางประสูติโอรสองค์หนึ่ง แต่องค์พระผู้เป็นเจ้าไม่พอพระทัยการกระทำของดาวิด