2 ሳሙኤል 1 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

2 ሳሙኤል 1:1-27

ዳዊት የሳኦልን ሞት ሰማ

1፥4-12 ተጓ ምብ – 1ሳሙ 31፥1-131ዜና 10፥1-12

1ሳኦል ከሞተ በኋላ፣ ዳዊት አማሌቃውያንን ድል አድርጎ በመመለስ፣ በጺቅላግ ሁለት ቀን ቈየ። 2በሦስተኛውም ቀን የተቀደደ ልብስ የለበሰ፣ በራሱም ላይ ትቢያ የነሰነሰ አንድ ሰው ከሳኦል ሰፈር መጣ። ወደ ዳዊት እንደ ደረሰም፣ ወደ መሬት ለጥ ብሎ በአክብሮት እጅ ነሣ።

3ዳዊትም፣ “ከወዴት መጣህ?” ሲል ጠየቀው።

እርሱም፣ “ከእስራኤላውያን ሰፈር ሸሽቼ መምጣቴ ነው” በማለት መለሰለት።

4ዳዊትም፣ “ምን ነገር ተፈጠረ?” ሲል ጠየቀው።

እርሱም፣ “ሰዎቹ ከጦርነቱ ሸሽተዋል፤ ብዙዎቹ ወድቀዋል፤ ሞተዋል፤ ሳኦልና ልጁ ዮናታንም ሞተዋል” አለ።

5ከዚያም ዳዊት ወሬውን የነገረውን ወጣት፣ “ሳኦልና ልጁ ዮናታን መሞታቸውን እንዴት ዐወቅህ?” ሲል ጠየቀው።

6ወሬ ነጋሪው ወጣትም እንዲህ አለ፤ “ድንገት ወደ ጊልቦዓ ተራራ ወጥቼ ነበር፤ እዚያም ሳኦል ጦሩን ተደግፎ ሳለ፣ ሠረገሎችና ፈረሰኞች ተከታትለው ደረሱበት። 7ወደ ኋላውም ዞር ሲል እኔን ስላየ ጠራኝ፤ እኔም፣ ‘ምን ልታዘዝ’ አልሁ።

8“እርሱም፣ ‘አንተ ማን ነህ?’ ሲል ጠየቀኝ፤

“እኔም ‘አማሌቃዊ ነኝ’ ብዬ መለስሁለት።

9“ከዚያም፣ ‘እኔ በሞት ጣር ውስጥ እገኛለሁ፤ ነፍሴ ግን አልወጣችም፤ እባክህ በላዬ ቆመህ ግደለኝ’ አለኝ።

10“መቼም ከወደቀ በኋላ እንደማይተርፍ ስላወቅሁ፣ በላዩ ቆሜ ገደልሁት፤ በራሱ ላይ የነበረውን ዘውድና የክንዱን አንባር ወስጄ እነሆ፤ ለጌታዬ አምጥቻለሁ።”

11ከዚያም ዳዊትና አብረውት የነበሩት ሰዎች ሁሉ ልብሳቸውን ቀደዱ። 12ለሳኦልና ለልጁ ለዮናታን፣ ለእግዚአብሔር ሰራዊትና ለእስራኤል ቤት ዐዘኑ፤ አለቀሱ፤ እስከ ማታም ድረስ ጾሙ፤ የወደቁት በሰይፍ ነበርና።

13ዳዊትም ወሬውን ያመጣለትን ወጣት፣ “ከየት ነው የመጣኸው?” ብሎ ጠየቀው።

እርሱም፣ “እኔ የአንድ መጻተኛ አማሌቃዊ ልጅ ነኝ” ብሎ መለሰ።

14ዳዊትም፣ “ታዲያ እግዚአብሔር የቀባውን ለማጥፋት እጅህን ስታነሣ እንዴት አልፈራህም?” ሲል ጠየቀው።

15ዳዊትም ከጕልማሶቹ አንዱን ጠርቶ፣ “በል ቅረብና ውደቅበት” አለው። እርሱም መታው፤ ሞተም። 16ዳዊትም፣ “ ‘እግዚአብሔር የቀባውን ገድያለሁ’ ስትል የገዛ አፍህ መስክሮብሃልና፣ ደምህ በራስህ ላይ ይሁን” አለው።

ዳዊት ለሳኦልና ለዮናታን የተቀኘው የሐዘን እንጕርጕሮ

17ዳዊትም በሳኦልና በልጁ በዮናታን ሞት ምክንያት ይህን የሐዘን እንጕርጕሮ እየተቀኘ አለቀሰ፤ 18እንዲሁም የቀስት እንጕርጕሮ የተባለውን ለይሁዳ ሕዝብ እንዲያስተምሩ አዘዘ፤ ይህም በያሻር መጽሐፍ ተጽፏል።

19“እስራኤል ሆይ፤ ክብርህ በኰረብቶችህ ላይ ተወግቶ ሞቷል፤

ኀያላኑ እንዴት እንደዚህ ይውደቁ!

20“ይህን በጌት አትናገሩ፤

በአስቀሎናም መንገዶች አታውጁት፤

የፍልስጥኤም ቈነጃጅት አይደሰቱ፤

ያልተገረዙት ሴቶች ልጆች እልል አይበሉ።

21“እናንተ የጊልቦዓ ተራሮች ሆይ፤

ጠል አያረስርሳችሁ፤

ዝናብም አይውረድባችሁ፤

የቍርባን እህል የሚያበቅሉም ዕርሻዎች አይኑራቸው፤

በዚያ የኀያሉ ሰው ጋሻ ረክሷልና፤ የሳኦል ጋሻ ከእንግዲህ በዘይት አይወለወልም።

22“ከሞቱት ሰዎች ደም፣

ከኀያላኑም ሥብ፣

የዮናታን ቀስት ተመልሳ አልመጣችም፤

የሳኦልም ሰይፍ በከንቱ አልተመለሰችም።

23ሳኦልና ዮናታን በሕይወት እያሉ፣

የሚዋደዱና የሚስማሙ ነበሩ፤

ሲሞቱም አልተለያዩም፤

ከንስርም ይልቅ ፈጣኖች፣

ከአንበሳም ይልቅ ብርቱዎች ነበሩ።

24“እናንት የእስራኤል ቈነጃጅት ሆይ፤

ሐምራዊ ቀሚስና ቀጭን ፈትል ላለበሳችሁ፣

ልብሶቻችሁንም በወርቀ ዘቦ ላስጌጠላችሁ፣

ለሳኦል አልቅሱለት።

25“ኀያላን እንዴት እንዲህ በጦርነት ወደቁ!

ዮናታን በኰረብቶችህ ላይ ተወግቶ ሞቷል።

26ወንድሜ ዮናታን ሆይ፤ እኔ ስለ አንተ ዐዘንሁ፤

አንተ ለእኔ እጅግ ውድ ነበርህ፤

ፍቅርህ ለእኔ ድንቅ ነበረ፤

ከሴት ፍቅርም ይልቅ ግሩም ነበር።

27“ኀያላኑ እንዴት ወደቁ!

የጦር መሣሪያዎቹስ እንዴት ከንቱ ይሁኑ!”

New International Version – UK

2 Samuel 1:1-27

David hears of Saul’s death

1After the death of Saul, David returned from striking down the Amalekites and stayed in Ziklag two days. 2On the third day a man arrived from Saul’s camp with his clothes torn and dust on his head. When he came to David, he fell to the ground to pay him honour.

3‘Where have you come from?’ David asked him.

He answered, ‘I have escaped from the Israelite camp.’

4‘What happened?’ David asked. ‘Tell me.’

‘The men fled from the battle,’ he replied. ‘Many of them fell and died. And Saul and his son Jonathan are dead.’

5Then David said to the young man who brought him the report, ‘How do you know that Saul and his son Jonathan are dead?’

6‘I happened to be on Mount Gilboa,’ the young man said, ‘and there was Saul, leaning on his spear, with the chariots and their drivers in hot pursuit. 7When he turned round and saw me, he called out to me, and I said, “What can I do?”

8‘He asked me, “Who are you?”

‘ “An Amalekite,” I answered.

9‘Then he said to me, “Stand here by me and kill me! I’m in the throes of death, but I’m still alive.”

10‘So I stood beside him and killed him, because I knew that after he had fallen he could not survive. And I took the crown that was on his head and the band on his arm and have brought them here to my lord.’

11Then David and all the men with him took hold of their clothes and tore them. 12They mourned and wept and fasted till evening for Saul and his son Jonathan, and for the army of the Lord and for the nation of Israel, because they had fallen by the sword.

13David said to the young man who brought him the report, ‘Where are you from?’

‘I am the son of a foreigner, an Amalekite,’ he answered.

14David asked him, ‘Why weren’t you afraid to lift your hand to destroy the Lord’s anointed?’

15Then David called one of his men and said, ‘Go, strike him down!’ So he struck him down, and he died. 16For David had said to him, ‘Your blood be on your own head. Your own mouth testified against you when you said, “I killed the Lord’s anointed.” ’

David’s lament for Saul and Jonathan

17David took up this lament concerning Saul and his son Jonathan, 18and he ordered that the people of Judah be taught this lament of the bow (it is written in the Book of Jashar):

19‘A gazelle1:19 Gazelle here symbolises a human dignitary. lies slain on your heights, Israel.

How the mighty have fallen!

20‘Tell it not in Gath,

proclaim it not in the streets of Ashkelon,

lest the daughters of the Philistines be glad,

lest the daughters of the uncircumcised rejoice.

21‘Mountains of Gilboa,

may you have neither dew nor rain,

may no showers fall on your terraced fields.1:21 Or / nor fields that yield grain for offerings

For there the shield of the mighty was despised,

the shield of Saul – no longer rubbed with oil.

22‘From the blood of the slain,

from the flesh of the mighty,

the bow of Jonathan did not turn back,

the sword of Saul did not return unsatisfied.

23Saul and Jonathan –

in life they were loved and admired,

and in death they were not parted.

They were swifter than eagles,

they were stronger than lions.

24‘Daughters of Israel,

weep for Saul,

who clothed you in scarlet and finery,

who adorned your garments with ornaments of gold.

25‘How the mighty have fallen in battle!

Jonathan lies slain on your heights.

26I grieve for you, Jonathan my brother;

you were very dear to me.

Your love for me was wonderful,

more wonderful than that of women.

27‘How the mighty have fallen!

The weapons of war have perished!’