1 ጴጥሮስ 5 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

1 ጴጥሮስ 5:1-14

ለሽማግሌዎችና ለጕልማሶች የተሰጠ ምክር

1እንግዲህ ከእነርሱ ጋር እኔም ሽማግሌና የክርስቶስ መከራ ምስክር የሆንሁ፣ እንዲሁም ወደ ፊት የሚገለጠው ክብር ተካፋይ የምሆን፣ በመካከላችሁ ያሉትን ሽማግሌዎች እመክራቸዋለሁ፤ 2በእናንተ ኀላፊነት ሥር ያለውን የእግዚአብሔርን መንጋ ጠብቁ፤ የምትጠብቁትም ከእግዚአብሔር እንደሚጠበቅባችሁ በግድ ሳይሆን በፈቃደኝነት፣ ለጥቅም በመስገብገብ ሳይሆን ለማገልገል ባላችሁ ጽኑ ፍላጎት ይሁን፤ 3እንዲሁም በዐደራ ለተሰጣችሁ መንጋ መልካም ምሳሌ በመሆን እንጂ በላያቸው በመሠልጠን አይሁን። 4የእረኞች አለቃ በሚገለጥበት ጊዜ የማይጠፋውን አክሊል ትቀበላላችሁ።

5ጕልማሶች ሆይ፤ እናንተም እንዲሁ ለሽማግሌዎች ተገዙ፤ ሁላችሁም እርስ በርስ በመከባበር ትሕትናን ልበሱ፤ ምክንያቱም፣

“እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፤

ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል።”

6ስለዚህ እርሱ በወሰነው ጊዜ ከፍ እንዲያደርጋችሁ ከእግዚአብሔር ብርቱ እጅ በታች ራሳችሁን ዝቅ አድርጉ፤ 7እርሱ ስለ እናንተ ስለሚያስብ የሚያስጨንቃችሁን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣሉት።

8ራሳችሁን የምትገዙ ሁኑ፣ ንቁም፤ ጠላታችሁ ዲያብሎስ የሚውጠውን በመፈለግ እንደሚያገሣ አንበሳ ወዲያ ወዲህ ይዞራልና። 9በዓለም ዙሪያ ያሉት ወንድሞቻችሁ ተመሳሳይ መከራ እንደሚቀበሉ ዐውቃችሁ በእምነት ጸንታችሁ ተቃወሙት።

10በክርስቶስ ወደ ዘላለም ክብሩ የጠራችሁ የጸጋ ሁሉ አምላክ፣ ለጥቂት ጊዜ መከራ ከተቀበላችሁ በኋላ እርሱ ራሱ መልሶ ያበረታችኋል፤ አጽንቶም ያቆማችኋል። 11ኀይል ከዘላለም እስከ ዘላለም ለእርሱ ይሁን፤ አሜን።

የስንብት ሰላምታ

12እንደ ታማኝ ወንድም በምቈጥረው በስልዋኑስ5፥12 ወይም ሲላስ አማካይነት ይህን ዐጭር መልእክት ጽፌላችኋለሁ፤ የጻፍሁላችሁም ልመክራችሁና ይህ እውነተኛ የእግዚአብሔር ጸጋ መሆኑን ልመሰክርላችሁ ብዬ ነው። በዚህ ጸጋ ጸንታችሁ ቁሙ።

13ከእናንተ ጋር የተመረጠችው፣ በባቢሎን የምትገኘው5፥13 በአንዳንድ ጥንታዊ ቅጆች ላይ በባቢሎን የምትገኘው ቤተ ክርስቲያን ይላሉ። ሰላምታ ታቀርብላችኋለች፤ እንዲሁም ልጄ ማርቆስ ሰላምታ ያቀርብላችኋል።

14በፍቅር አሳሳም እርስ በርሳችሁ ሰላምታ ተሰጣጡ።

በክርስቶስ ላላችሁ ለሁላችሁ ሰላም ይሁን።

Thai New Contemporary Bible

1เปโตร 5:1-14

ผู้อาวุโสและผู้อ่อนอาวุโส

1ถึงผู้อาวุโส5:1 หรือผู้ปกครองทั้งหลายในหมู่พวกท่าน ข้าพเจ้าขอร้องท่านในฐานะที่เป็นเพื่อนผู้อาวุโส เป็นพยานคนหนึ่งในเรื่องการทนทุกข์ของพระคริสต์ และเป็นผู้หนึ่งที่จะร่วมในพระเกียรติสิริซึ่งจะทรงสำแดงนั้นว่า 2จงเลี้ยงดูฝูงแกะของพระเจ้าซึ่งอยู่ในความดูแลรับผิดชอบของท่าน พวกท่านรับใช้ในฐานะผู้ปกครองดูแล ไม่ใช่เพราะท่านต้องทำแต่เพราะท่านเต็มใจทำตามที่พระเจ้าทรงประสงค์ให้ท่านเป็น ไม่ใช่โลภเงินทองแต่กระตือรือร้นที่จะรับใช้ 3ไม่ใช่วางอำนาจเหนือบรรดาผู้ที่ทรงมอบหมายแก่ท่าน แต่เป็นแบบอย่างแก่ฝูงแกะนั้น 4และเมื่อหัวหน้าของผู้เลี้ยงทั้งปวงทรงปรากฏท่านทั้งหลายจะได้รับมงกุฎแห่งศักดิ์ศรีซึ่งไม่มีวันเสื่อมสลาย

5ในทำนองเดียวกันท่านผู้อ่อนอาวุโส จงยอมเชื่อฟังบรรดาผู้ที่อาวุโสกว่า อันที่จริงให้ท่านทุกคนถ่อมใจต่อกันและกัน เพราะว่า

“พระเจ้าทรงต่อสู้ผู้ที่หยิ่งจองหอง

แต่ประทานพระคุณแก่คนที่ถ่อมใจ”5:5 สภษ. 3:34

6เพราะฉะนั้นพวกท่านจงถ่อมใจลงภายใต้พระหัตถ์อันทรงฤทธิ์ของพระเจ้าเพื่อพระองค์จะทรงยกท่านขึ้นเมื่อถึงเวลาอันควร 7จงละความกังวลทั้งสิ้นของท่านไว้กับพระองค์เพราะพระองค์ทรงห่วงใยท่าน

8จงรู้จักบังคับตนเองและตื่นตัวอยู่เสมอ เพราะมารผู้เป็นศัตรูของท่านวนเวียนอยู่รอบๆ ดุจสิงห์คำราม เที่ยวหาเหยื่อเพื่อขย้ำกิน 9จงต่อต้านมาร ยืนหยัดมั่นคงในความเชื่อ ด้วยรู้ว่าพี่น้องทั่วโลกกำลังเผชิญความทุกข์ยากแบบเดียวกัน

10และหลังจากพวกท่านทนทุกข์อยู่ชั่วขณะหนึ่ง พระเจ้าแห่งพระคุณทั้งปวงผู้ทรงเรียกท่านมาสู่พระเกียรติสิรินิรันดร์ของพระองค์ในพระคริสต์ พระองค์เองจะทรงให้พวกท่านกลับคืนสู่สภาพดีและให้ท่านเข้มแข็ง มั่นคง และแน่วแน่ 11ขอเดชานุภาพมีแด่พระองค์สืบๆ ไปเป็นนิตย์ อาเมน

คำลงท้าย

12ข้าพเจ้าเขียนมาถึงท่านสั้นๆ ด้วยความช่วยเหลือของสิลาส5:12 หรือสิลวานัส ผู้ซึ่งข้าพเจ้าถือว่าเป็นพี่น้องที่สัตย์ซื่อ ข้าพเจ้าเขียนมาให้กำลังใจท่านและเป็นพยานว่าทั้งหมดนี้คือพระคุณที่แท้จริงของพระเจ้า จงยืนหยัดมั่นคงในพระคุณนี้

13คริสตจักรที่เมืองบาบิโลนผู้ได้รับการเลือกสรรด้วยกันกับท่านฝากความคิดถึงมายังท่าน และมาระโกบุตรของข้าพเจ้าก็ฝากความคิดถึงมายังท่านด้วย 14จงทักทายกันด้วยจุมพิตแห่งความรัก

ขอสันติสุขมีแด่พวกท่านทุกคนผู้อยู่ในพระคริสต์