1 ጴጥሮስ 5 – NASV & HHH

New Amharic Standard Version

1 ጴጥሮስ 5:1-14

ለሽማግሌዎችና ለጕልማሶች የተሰጠ ምክር

1እንግዲህ ከእነርሱ ጋር እኔም ሽማግሌና የክርስቶስ መከራ ምስክር የሆንሁ፣ እንዲሁም ወደ ፊት የሚገለጠው ክብር ተካፋይ የምሆን፣ በመካከላችሁ ያሉትን ሽማግሌዎች እመክራቸዋለሁ፤ 2በእናንተ ኀላፊነት ሥር ያለውን የእግዚአብሔርን መንጋ ጠብቁ፤ የምትጠብቁትም ከእግዚአብሔር እንደሚጠበቅባችሁ በግድ ሳይሆን በፈቃደኝነት፣ ለጥቅም በመስገብገብ ሳይሆን ለማገልገል ባላችሁ ጽኑ ፍላጎት ይሁን፤ 3እንዲሁም በዐደራ ለተሰጣችሁ መንጋ መልካም ምሳሌ በመሆን እንጂ በላያቸው በመሠልጠን አይሁን። 4የእረኞች አለቃ በሚገለጥበት ጊዜ የማይጠፋውን አክሊል ትቀበላላችሁ።

5ጕልማሶች ሆይ፤ እናንተም እንዲሁ ለሽማግሌዎች ተገዙ፤ ሁላችሁም እርስ በርስ በመከባበር ትሕትናን ልበሱ፤ ምክንያቱም፣

“እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፤

ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል።”

6ስለዚህ እርሱ በወሰነው ጊዜ ከፍ እንዲያደርጋችሁ ከእግዚአብሔር ብርቱ እጅ በታች ራሳችሁን ዝቅ አድርጉ፤ 7እርሱ ስለ እናንተ ስለሚያስብ የሚያስጨንቃችሁን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣሉት።

8ራሳችሁን የምትገዙ ሁኑ፣ ንቁም፤ ጠላታችሁ ዲያብሎስ የሚውጠውን በመፈለግ እንደሚያገሣ አንበሳ ወዲያ ወዲህ ይዞራልና። 9በዓለም ዙሪያ ያሉት ወንድሞቻችሁ ተመሳሳይ መከራ እንደሚቀበሉ ዐውቃችሁ በእምነት ጸንታችሁ ተቃወሙት።

10በክርስቶስ ወደ ዘላለም ክብሩ የጠራችሁ የጸጋ ሁሉ አምላክ፣ ለጥቂት ጊዜ መከራ ከተቀበላችሁ በኋላ እርሱ ራሱ መልሶ ያበረታችኋል፤ አጽንቶም ያቆማችኋል። 11ኀይል ከዘላለም እስከ ዘላለም ለእርሱ ይሁን፤ አሜን።

የስንብት ሰላምታ

12እንደ ታማኝ ወንድም በምቈጥረው በስልዋኑስ5፥12 ወይም ሲላስ አማካይነት ይህን ዐጭር መልእክት ጽፌላችኋለሁ፤ የጻፍሁላችሁም ልመክራችሁና ይህ እውነተኛ የእግዚአብሔር ጸጋ መሆኑን ልመሰክርላችሁ ብዬ ነው። በዚህ ጸጋ ጸንታችሁ ቁሙ።

13ከእናንተ ጋር የተመረጠችው፣ በባቢሎን የምትገኘው5፥13 በአንዳንድ ጥንታዊ ቅጆች ላይ በባቢሎን የምትገኘው ቤተ ክርስቲያን ይላሉ። ሰላምታ ታቀርብላችኋለች፤ እንዲሁም ልጄ ማርቆስ ሰላምታ ያቀርብላችኋል።

14በፍቅር አሳሳም እርስ በርሳችሁ ሰላምታ ተሰጣጡ።

በክርስቶስ ላላችሁ ለሁላችሁ ሰላም ይሁን።

Habrit Hakhadasha/Haderekh

אגרתו הראשונה של פטרוס השליח 5:1-14

1אני מזהיר את זקני הקהילה שביניכם, כזקן קהילה, כמי שראה במו עיניו את סבל המשיח, וכמי שיחד אתכם ייקח חלק בכבודו והדרו כשישוב אלינו: 2רעו את צאנו של אלוהים; דאגו להן והשגיחו עליהן ברצון ולא מתוך אונס. אל תעשו שיקולי כדאיות, אלא עשו את המוטל עליכם מתוך רצון כן לשרת את אלוהים. 3אל תשלטו בהן בעריצות; הנהיגו אותן באהבה ושמשו להן דוגמה אישית. 4וכאשר יבוא שר הרועים, הוא יעניק לכם את כתר הכבוד שלא יבול לעולם.

5צעירים, עליכם להישמע לזקני הקהילה. על כולכם לשרת איש את אחיו בענווה ולהיכנע איש לפני רעהו, כי אלוהים מתנגד לגאים ולענוים יתן חן. 6השפילו את עצמכם תחת יד אלוהים החזקה, הוא ירומם אתכם בבוא העת. 7הפקידו את כל הצרות, הפחדים והחששות שלכם ביד אלוהים, שהרי הוא תמיד דואג ועוזר לכם. 8היזהרו והישמרו מפני השטן אויבכם, כי הוא מתהלך סביבכם כאריה שואג שמחפש טרף. 9החזיקו מעמד נגד התקפותיו; ביטחו באלוהים, וזכרו שמאמינים רבים בכל העולם מתנסים כמוכם בסבל דומה.

10לאחר שתסבלו זמן קצר יעניק לכם אלוהינו רב־החסד את כבודו הנצחי דרך המשיח, ואלוהים עצמו ישלים, יבנה ויחזק אתכם. 11לאלוהים הכבוד והגבורה לעולם ועד. – אמן.

12אני שולח לכם מכתב קצר זה באמצעות סילוונוס (שאותו אני מכיר כאח נאמן), כדי לעודד אתכם ולהבטיח לכם שהכתוב לעיל הוא דבר אמת מאת האלוהים. קחו את הדברים לתשומת לבכם וקיימו אותם.

13הקהילה כאן ברומא,5‏.13 ה 13 כלשונו: חברתכם אשר בבבל, הנבחרה אתכם. אחותכם באמונה, מוסרת לכם דרישת שלום. גם מרקוס בני מוסר לכם דרישת שלום. 14ברכו איש את רעהו לשלום בנשיקת אהבה. שלום לכל אלה מכם המאמינים במשיח.