1 ጴጥሮስ 3 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

1 ጴጥሮስ 3:1-22

በባልና በሚስት መካከል ሊኖር የሚገባ ግንኙነት

1ሚስቶች ሆይ፤ እናንተም እንደዚሁ ለባሎቻችሁ ተገዙ፤ አንዳንድ ለቃሉ የማይታዘዙ ቢኖሩ፣ ያለ ቃል በሚስቶቻቸው አኗኗር ተማርከው ይመለሳሉ፤ 2ይህም የሚሆነው ንጹሕና ፍጹም አክብሮት የተሞላውን ኑሯችሁን ሲመለከቱ ነው። 3ውበታችሁ በውጫዊ ነገሮች በመሽሞንሞን፣ ይኸውም፣ ሹሩባ በመሠራት፣ በወርቅ በማጌጥና በልብስ አይሁን፤ 4ነገር ግን ውበታችሁ በእግዚአብሔር ፊት ዋጋው እጅግ የከበረ፣ ገርና ጭምት መንፈስ ያለበት፣ ምንጊዜም የማይጠፋ የውስጥ ሰውነት ውበት ይሁን፤ 5ተስፋቸውን በእግዚአብሔር ላይ የጣሉ የቀድሞ ቅዱሳን ሴቶች ራሳቸውን ያስዋቡት በዚህ ዐይነት ለባሎቻቸው በመገዛት ነበርና። 6ሣራም አብርሃምን “ጌታዬ” እያለች ትታዘዘው ነበር፣ እናንተም ምንም ሳትፈሩ መልካም ብታደርጉ የእርሷ ልጆች ናችሁ።

7ባሎች ሆይ፤ እናንተም ደግሞ ጸሎታችሁ እንዳይደናቀፍ በኑሯችሁ ሁሉ ለሚስቶቻችሁ ዐስቡላቸው፤ ደካሞች ስለሆኑና የሕይወትንም በረከት አብረዋችሁ ስለሚወርሱ አክብሯቸው።

መልካም በማድረግ መከራን መቀበል

8በመጨረሻም ሁላችሁ በአንድ ሐሳብ ተስማሙ፤ እርስ በርሳችሁ ተሳሰቡ፤ እንደ ወንድማማቾች ተዋደዱ፤ ርኅሩኆችና ትሑታን ሁኑ። 9ክፉን በክፉ ወይም ስድብን በስድብ ፈንታ አትመልሱ፤ በዚህ ፈንታ ባርኩ፤ ምክንያቱም እናንተ የተጠራችሁት እንደነዚህ ያሉትን ነገሮች እያደረጋችሁ በረከትን ለመውረስ ነው። 10ስለዚህ፣

“ሕይወትን የሚወድድ፣

መልካም ቀኖችን ሊያይ የሚፈልግ፣

ምላሱን ከክፉ፣

ከንፈሮቹንም ተንኰል ከመናገር ይከልክል።

11ከክፉ ይራቅ፤ መልካምንም ያድርግ፤

ሰላምን ይፈልግ፤ ይከተላትም፤

12ምክንያቱም የጌታ ዐይኖች ጻድቃንን ይመለከታሉና፤

ጆሮቹም ጸሎታቸውን ለመስማት የተከፈቱ ናቸው፤

የጌታ ፊት ግን በክፉ አድራጊዎች ላይ ነው።”

13መልካም ነገር ለማድረግ ብትቀኑ የሚጐዳችሁ ማን ነው? 14ነገር ግን ስለ ጽድቅ እንኳ መከራ ቢደርስባችሁ ብፁዓን ናችሁ፤ “ዛቻቸውን አትፍሩ3፥14 ወይም የሚፈሩትን አትፍሩ፤ አትታወኩም።” 15ክርስቶስን ጌታ አድርጋችሁ በልባችሁ ቀድሱት። እናንተ ስላላችሁ ተስፋ ምክንያትን ለሚጠይቋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ሁልጊዜ የተዘጋጃችሁ ሁኑ፤ ነገር ግን ይህን ሁሉ በትሕትናና በአክብሮት አድርጉት፤ 16በክርስቶስ ያላችሁን መልካም ጠባይ አክፋፍተው የሚናገሩ ሰዎች በሐሜታቸው እንዲያፍሩ በጎ ኅሊና ይኑራችሁ። 17የእግዚአብሔር ፈቃድ እንዲህ ከሆነ፣ ክፉ ሠርቶ መከራ ከመቀበል ይልቅ መልካም አድርጎ መከራ መቀበል ይሻላል፤ 18እንዲሁም ክርስቶስ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ስለ ኀጢአት ሞቷልና፤ ወደ እግዚአብሔር ያቀርባችሁ ዘንድ ጻድቅ የሆነው እርሱ ስለ ዐመፀኞች ሞተ፤ እርሱ በሥጋ ሞተ፤ በመንፈስ ግን ሕያው ሆነ፤ 19በመንፈስም ሄዶ በወህኒ ቤት ለነበሩ ነፍሳት ሰበከላቸው። 20እነዚህ በወህኒ የነበሩት ነፍሳት ቀድሞ በኖኅ ዘመን መርከብ ሲሠራ እግዚአብሔር በትዕግሥት ይጠብቃቸው የነበሩ እንቢተኞች ናቸው፤ በውሃ የዳኑት ጥቂት፣ ይኸውም ስምንት ሰዎች ብቻ ነበሩ። 21ይህም ውሃ አሁን የጥምቀት ምሳሌ ሆኖ ያድናችኋል፤ ይህም የሰውነትን እድፍ በማስወገድ ሳይሆን በንጹሕ ኅሊና በእግዚአብሔር ፊት የሚቀርብ መማፀኛ3፥21 ወይም ምላሽ ነው፤ የሚያድናችሁም በኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ አማካይነት ነው፤ 22እርሱም ወደ ሰማይ ወጥቶ በእግዚአብሔር ቀኝ አለ፤ መላእክትና ሥልጣናት፣ ኀይላትም ተገዝተውለታል።

Thai New Contemporary Bible

1เปโตร 3:1-22

สามีภรรยา

1ในทำนองเดียวกันภรรยาทั้งหลายจงยอมเชื่อฟังสามีของตน เพื่อว่าแม้สามีบางคนไม่เชื่อพระวจนะของพระเจ้า แต่ความประพฤติของภรรยาก็อาจชนะใจเขา ทำให้เขาหันกลับมาเชื่อโดยไม่ต้องเอ่ยปาก 2เมื่อเขาเห็นความบริสุทธิ์และความยำเกรงพระเจ้าในชีวิตของท่าน 3ความงามของท่านไม่ควรมาจากการตกแต่งภายนอกเช่น ถักผม สวมเครื่องทองและเสื้อผ้าสวยงาม 4แต่ให้ออกมาจากตัวตนภายใน คือความงามอันไม่รู้จางหายของจิตใจที่อ่อนโยนและสงบเยือกเย็น ซึ่งจิตใจเช่นนี้ทรงคุณค่ายิ่งนักในสายพระเนตรพระเจ้า 5เพราะนี่เป็นแนวทางที่สตรีผู้บริสุทธิ์ในอดีตซึ่งหวังใจในพระเจ้าเคยทำให้ตนเองงดงาม พวกนางยอมเชื่อฟังสามีของตน 6เหมือนนางซาราห์ผู้เชื่อฟังอับราฮัมและเรียกเขาว่านาย ถ้าท่านทำสิ่งที่ถูกต้องและไม่หวาดหวั่นสิ่งร้ายอันใด ท่านทั้งหลายก็เป็นลูกหลานของนางซาราห์

7ในทำนองเดียวกันสามีทั้งหลายจงอยู่กับภรรยาด้วยความเห็นอกเห็นใจ จงให้เกียรติภรรยาในฐานะเป็นผู้ที่อ่อนแอกว่าและในฐานะทายาทผู้รับชีวิตซึ่งเป็นของประทานอันทรงพระคุณจากพระเจ้าร่วมกับท่าน เพื่อจะไม่มีสิ่งใดขัดขวางคำอธิษฐานของท่านทั้งสอง

ทนทุกข์เพราะการทำดี

8สุดท้ายนี้ท่านทั้งปวงจงเป็นน้ำหนึ่งใจเดียวกัน จงเห็นอกเห็นใจกัน จงรักกันฉันพี่น้อง จงมีใจอ่อนโยนและถ่อมสุภาพ 9อย่าทำชั่วตอบแทนการชั่ว อย่าด่าว่าผู้ที่ด่าว่าท่าน แต่จงให้พรเขาแทนเพราะพระเจ้าได้ทรงเรียกท่านให้ทำเช่นนี้ เพื่อท่านจะได้รับพระพรเป็นมรดก 10เพราะ

“ผู้ใดรักชีวิต

และปรารถนาจะเห็นวันคืนอันผาสุก

ต้องรักษาลิ้นให้พ้นจากความชั่ว

รักษาริมฝีปากให้พ้นจากคำพูดหลอกลวง

11เขาต้องหันจากความชั่วร้ายและทำความดี

เขาต้องใฝ่หาสันติภาพและมุ่งมั่นเพื่อให้ได้มา

12เพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงเฝ้าดูคนชอบธรรม

และทรงเงี่ยพระกรรณฟังคำอธิษฐานของพวกเขา

แต่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงหันพระพักตร์เข้าต่อต้านคนที่กระทำชั่ว”3:10-12 สดด.34:12-16

13ถ้าท่านมุ่งมั่นทำดี ใครจะมาทำร้ายท่าน? 14แต่ถึงแม้ท่านต้องทนทุกข์ทั้งๆ ที่ทำสิ่งที่ถูกต้อง ท่านก็ได้รับพระพร “อย่ากลัวสิ่งที่พวกเขากลัว3:14 หรืออย่ากลัวการข่มขู่ของเขา อย่าตกใจกลัวเลย”3:14 อสย.8:12 15แต่ในใจของท่านจงเทิดทูนพระคริสต์เป็นองค์พระผู้เป็นเจ้า จงเตรียมพร้อมเสมอที่จะตอบทุกคนซึ่งถามถึงเหตุผลที่ท่านมีความหวังใจเช่นนี้ แต่จงตอบอย่างสุภาพอ่อนโยนและให้เกียรติ 16จงรักษาจิตสำนึกให้บริสุทธิ์ เพื่อผู้ที่กล่าวร้ายความประพฤติดีของท่านในพระคริสต์จะได้ละอายใจที่มาใส่ร้ายท่าน 17เพราะหากเป็นพระประสงค์ของพระเจ้าให้ท่านทนทุกข์เนื่องจากการทำดีก็ดีกว่าทนทุกข์เนื่องจากทำชั่ว 18เพราะพระคริสต์สิ้นพระชนม์เพื่อลบล้างบาปเพียงครั้งเดียวเป็นพอ คือคนชอบธรรมตายเพื่อคนอธรรมเพื่อนำเราทั้งหลายไปถึงพระเจ้า พระองค์ทรงถูกประหารทางกาย แต่พระองค์ทรงเป็นขึ้นในพระวิญญาณ 19ในสภาวะนั้น3:18-19 หรือแต่พระองค์ทรงเป็นขึ้นในวิญญาณ 19โดยทางวิญญาณนั้น พระองค์ยังได้เสด็จไปประกาศแก่วิญญาณทั้งหลายที่ถูกจองจำอยู่ด้วย 20วิญญาณซึ่งในอดีตไม่เชื่อฟังเมื่อครั้งพระเจ้าทรงอดทนรอคอยในสมัยของโนอาห์ขณะที่เขาต่อเรือ ในเรือนี้มีคนเพียงไม่กี่คนคือแปดคนเท่านั้นที่พระเจ้าทรงใช้น้ำช่วยพวกเขาให้รอดชีวิต3:20 หรือพระเจ้าทรงช่วยพวกเขาให้รอดชีวิตจากน้ำ 21น้ำนี้เล็งถึงบัพติศมาซึ่งบัดนี้ช่วยท่านทั้งหลายให้รอดเช่นกัน บัพติศมาไม่ใช่เป็นการขจัดสิ่งสกปรกออกจากร่างกาย แต่เป็นการปฏิญาณต่อพระเจ้าว่าจะรักษาจิตสำนึกที่ดี บัพติศมาช่วยท่านให้รอดโดยการเป็นขึ้นจากตายของพระเยซูคริสต์ 22ผู้ได้เสด็จขึ้นสู่สวรรค์และบัดนี้ประทับที่เบื้องขวาพระหัตถ์ของพระเจ้าโดยมีเหล่าทูตสวรรค์ ผู้ทรงอำนาจ และผู้ทรงเดชานุภาพอยู่ใต้อำนาจของพระองค์