1 ጢሞቴዎስ 3 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

1 ጢሞቴዎስ 3:1-16

እረኞችና ዲያቆናት

1“ማንም ኤጲስቆጶስነትን3፥1 ወይም ተመልካች፣ ጠባቂዎች ቢፈልግ፣ መልካም ሥራን ይመኛል” የሚለው ቃል የታመነ ነው። 2እንግዲህ የቤተ ክርስቲያን ኤጲስቆጶስ የማይነቀፍ፣ የአንዲት ሚስት ባል፣ ልከኛ፣ ራሱን የሚገዛ፣ በሥርዐት የሚኖር፣ እንግዳ ተቀባይ፣ ማስተማር የሚችል፣ 3የማይሰክር፣ የማይጣላ ግን ጨዋ የሆነ፣ የማይጨቃጨቅ፣ ገንዘብንም የማይወድ ሊሆን ይገባዋል። 4ልጆቹን ታዛዥና አክባሪ አድርጎ በማሳደግ የገዛ ቤተ ሰቡን በአግባቡ የሚያስተዳድር ሊሆን ይገባል። 5አንድ ሰው የራሱን ቤት ማስተዳደር ካላወቀበት፣ የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን እንዴት ሊጠብቅ ይችላል? 6በትዕቢት ተነፍቶ ዲያብሎስ በወደቀበት ፍርድ እንዳይወድቅ አዲስ ክርስቲያን አይሁን። 7ደግሞም ስሙ እንዳይነቀፍና በዲያብሎስ ወጥመድ ውስጥ እንዳይወድቅ፣ በውጭ ባሉት ዘንድ መልካም ምስክርነት ሊኖረው ይገባል።

8ዲያቆናትም እንደዚሁ የተከበሩ፣ ቃላቸውን የማይለዋውጡ፣ ለብዙ ወይን ጠጅ የማይጐመጁ፣ ያለ አግባብ የሚገኝ ጥቅምንም የማያሳድዱ ሰዎች መሆን ይገባቸዋል፤ 9የእምነትንም ጥልቅ ምስጢር በንጹሕ ኅሊና መጠበቅ አለባቸው። 10እነርሱም አስቀድመው ይፈተኑ፤ ከዚያም፣ አንዳች ነቀፋ ካልተገኘባቸው በዲቁና ያገልግሉ።

11እንዲሁ ሴቶችም3፥11 ወይም ሚስቶቻቸው ወይም ዲያቆናውያት የተከበሩ፣ ሐሜተኞች ያልሆኑ ነገር ግን ልከኞችና በነገር ሁሉ የታመኑ ሊሆኑ ይገባል።

12ዲያቆናት የአንዲት ሚስት ባል መሆን ይገባቸዋል፤ ደግሞም ልጆቻቸውንና ቤተ ሰቦቻቸውን በአግባቡ የሚያስተዳድሩ መሆን አለባቸው። 13በአግባቡ ያገለገሉ ለራሳቸው ትልቅ ክብርን፣ በክርስቶስ ኢየሱስም ባላቸው እምነት ብዙ ድፍረትን ያገኛሉ።

14ወደ አንተ ቶሎ ለመምጣት ተስፋ ባደርግም ይህን ትእዛዝ እጽፍልሃለሁ፤ 15ይህንም የምጽፍልህ ብዘገይ እንኳ ሰዎች በእግዚአብሔር ቤት እንዴት መኖር እንዳለባቸው እንድታውቅ ነው፤ ቤቱም የሕያው እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን፣ ይኸውም የእውነት ዐምድና መሠረት ነው። 16የእውነተኛ መንፈሳዊ ሕይወት ምስጢር ያለ ጥርጥር ታላቅ ነው፤

እርሱ3፥16 አንዳንድ ቅጆች አምላክ ይላሉ። በሥጋ3፥16 ወይም በአካል ተገለጠ፤

በመንፈስ ጸደቀ፤

በመላእክት ታየ፤

በአሕዛብ ዘንድ ተሰበከ፤

በዓለም ባሉት ታመነ፤

በክብር ዐረገ።

Thai New Contemporary Bible

1ทิโมธี 3:1-16

ผู้ปกครองและมัคนายก

1นี่เป็นคำกล่าวที่น่าเชื่อถือ คือถ้าผู้ใดมุ่งมั่นที่จะเป็นผู้ปกครอง3:1 โดยปกติแปลว่าบิชอปเช่นเดียวกับข้อ 2 ในคริสตจักร ผู้นั้นก็ปรารถนางานอันมีเกียรติ 2ส่วนผู้ปกครองในคริสตจักรนั้นต้องปราศจากที่ติ เป็นสามีของภรรยาคนเดียว รู้จักประมาณตน รู้จักควบคุมตนเอง น่านับถือ มีน้ำใจรับรองแขก สามารถที่จะสอนคนอื่นได้ 3ไม่ดื่มสุราเมามาย ไม่ก้าวร้าวแต่สุภาพอ่อนโยน ไม่ชอบทะเลาะวิวาท ไม่เป็นคนรักเงิน 4เขาต้องดูแลจัดการครอบครัวของตนได้ดี อบรมบุตรหลานให้เชื่อฟังและเคารพเขาอย่างที่ควร 5(ถ้าใครไม่รู้วิธีดูแลจัดการครอบครัวของตนเอง เขาจะมาดูแลคริสตจักรของพระเจ้าได้อย่างไร?) 6เขาต้องไม่เป็นผู้ที่เพิ่งกลับใจมาเชื่อ มิฉะนั้นอาจจะจองหองลืมตัวและต้องรับโทษเหมือนมารนั้น 7เขาต้องมีชื่อเสียงดีในหมู่คนภายนอก เพื่อว่าเขาจะได้ไม่ตกในความเสื่อมเสียและตกในกับดักของมาร

8ฝ่ายมัคนายกก็เช่นกัน ควรเป็นคนที่น่านับถือ จริงใจ ไม่ขี้เหล้าเมายา ไม่หาประโยชน์ในทางที่ไม่ซื่อ 9เขาต้องยึดมั่นในความจริงอันลึกซึ้งของความเชื่อด้วยจิตสำนึกว่าตนชอบ 10จงตรวจสอบคนเหล่านี้ดูก่อน เมื่อเห็นว่าไม่มีข้อบกพร่องจึงให้ทำหน้าที่มัคนายกได้

11ในทำนองเดียวกันภรรยาของพวกเขา3:11 หรือมัคนายิกาต้องเป็นสตรีที่น่านับถือ ไม่พูดว่าร้ายคนอื่น แต่รู้จักประมาณตน และเชื่อถือได้ในทุกเรื่อง

12มัคนายกต้องเป็นสามีของภรรยาคนเดียว และต้องดูแลบุตรหลานและครัวเรือนได้เป็นอย่างดี 13ผู้ที่ปรนนิบัติได้อย่างดีก็ได้รับเกียรติมากและมีความมั่นใจอย่างมากในความเชื่อของเขาในพระเยซูคริสต์

14แม้ว่าข้าพเจ้าหวังจะมาหาท่านในไม่ช้า แต่ข้าพเจ้าก็เขียนคำสั่งสอนเหล่านี้มา เพื่อว่า 15หากข้าพเจ้าล่าช้า ท่านก็จะได้รู้ว่าคนทั้งหลายควรทำตัวอย่างไรในครอบครัวของพระเจ้า คือคริสตจักรของพระเจ้าผู้ทรงพระชนม์อยู่อันเป็นเสาหลักและรากฐานแห่งความจริง 16ข้อล้ำลึกแห่งทางพระเจ้านั้นยิ่งใหญ่เหนือข้อข้องใจทั้งมวล นั่นคือ

พระองค์3:16 สำเนาต้นฉบับบางสำเนาว่าพระเจ้าได้ทรงปรากฏในกายมนุษย์3:16 หรือ ในเนื้อหนัง

พระวิญญาณได้ทรงพิสูจน์แล้ว

เหล่าทูตสวรรค์ได้เห็น

มีผู้ประกาศพระองค์ท่ามกลางประชาชาติ

ชาวโลกเชื่อในพระองค์

พระเจ้าทรงรับพระองค์ขึ้นสู่พระเกียรติสิริ