1 ጢሞቴዎስ 2 – NASV & NVI-PT

New Amharic Standard Version

1 ጢሞቴዎስ 2:1-15

አምልኮን በሚመለከት የተሰጠ መመሪያ

1እንግዲህ ከሁሉ አስቀድሞ ልመናና ጸሎት፣ ምልጃና ምስጋና ለሰዎች ሁሉ፣ ለነገሥታትና ለባለሥልጣናት ሁሉ እንዲደረግ አሳስባለሁ፤ 2ይህም በእውነተኛ መንፈሳዊ ሕይወትና በቅድስና ሁሉ፣ በሰላምና በጸጥታ እንድንኖር ነው። 3ይህ በእግዚአብሔር በአዳኛችን ፊት ደስ የሚያሰኝ ነው፤ 4እርሱ ሰዎች ሁሉ እንዲድኑና እውነትን ወደ ማወቅ እንዲደርሱ ይፈልጋል። 5አንድ እግዚአብሔር አለና፤ ደግሞም በእግዚአብሔርና በሰዎች መካከል አንድ አስታራቂ አለ፤ እርሱም ሰው የሆነው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፤ 6ራሱንም ለሰዎች ሁሉ ቤዛ አድርጎ ሰጠ፤ ይህም በትክክለኛው ጊዜ ተመስክሮለታል። 7እኔም ለዚህ ነገር የምሥራች አብሣሪና ሐዋርያ እንዲሁም ለአሕዛብ የእውነተኛ እምነት አስተማሪ ሆኜ ተሾምሁ፤ እውነቱን እናገራለሁ፤ አልዋሽም።

8እንግዲህ ወንዶች በሁሉም ቦታ ያለ ቍጣና ያለ ክርክር የተቀደሱ እጆቻቸውን ወደ ላይ በማንሣት እንዲጸልዩ እፈልጋለሁ። 9እንዲሁም ሴቶች በጨዋነትና ራስን በመግዛት ተገቢ የሆነ ልብስ ይልበሱ እንጂ በሹሩባ ወይም በዕንወይም ዋጋቸው ውድ በሆኑ ልብሶች አይሽቀርቀሩ፤ 10ነገር ግን እግዚአብሔርን እናመልካለን የሚሉ ሴቶች ሊያደርጉ እንደሚገባ በመልካም ተግባር ይዋቡ።

11ሴት በጸጥታና በሙሉ መገዛት ትማር። 12ሴት ዝም እንድትል እንጂ እንድታስተምር ወይም በወንድ ላይ ሥልጣን እንዲኖራት አልፈቅድም፤ 13ምክንያቱም አዳም ቀድሞ ተፈጥሯል፤ ከዚያም ሔዋን ተፈጠረች። 14ደግሞም የተታለለው አዳም አይደለም፤ የተታለለችውና ኀጢአተኛ የሆነችው ሴቷ ናት። 15ይሁን እንጂ ሴት2፥15 ግሪኩ እርሷ ይላል። በእምነትና በፍቅር፣ በቅድስናም ራሷን እየገዛች ብትጸና ልጅ በመውለድ ትድናለች2፥15 ወይም ትታደሳለች

Nova Versão Internacional

1 Timóteo 2:1-15

Instruções acerca da Adoração

1Antes de tudo, recomendo que se façam súplicas, orações, intercessões e ações de graças por todos os homens; 2pelos reis e por todos os que exercem autoridade, para que tenhamos uma vida tranquila e pacífica, com toda a piedade e dignidade. 3Isso é bom e agradável perante Deus, nosso Salvador, 4que deseja que todos os homens sejam salvos e cheguem ao conhecimento da verdade.

5Pois há um só Deus

e um só mediador entre Deus e os homens:

o homem Cristo Jesus,

6o qual se entregou a si mesmo como resgate por todos.

Esse foi o testemunho dado em seu próprio tempo.

7Para isso fui designado pregador e apóstolo (Digo a verdade, não minto.), mestre da verdadeira fé aos gentios2.7 Isto é, os que não são judeus..

8Quero, pois, que os homens orem em todo lugar, levantando mãos santas, sem ira e sem discussões.

9Da mesma forma, quero que as mulheres se vistam modestamente, com decência e discrição, não se adornando com tranças e com ouro, nem com pérolas ou com roupas caras, 10mas com boas obras, como convém a mulheres que declaram adorar a Deus.

11A mulher deve aprender em silêncio, com toda a sujeição. 12Não permito que a mulher ensine nem que tenha autoridade sobre o homem. Esteja, porém, em silêncio. 13Porque primeiro foi formado Adão e depois Eva. 14E Adão não foi enganado, mas sim a mulher que, tendo sido enganada, se tornou transgressora. 15Entretanto, a mulher2.15 Grego: ela. será salva2.15 Ou restaurada dando à luz filhos—se permanecer na fé, no amor e na santidade, com bom senso.